Ethiopian Orthodox Tewahdo Youth page_የኢኦተቤክ ወጣቶች ፔጅ

  • Home
  • Ethiopia
  • Alamat'a
  • Ethiopian Orthodox Tewahdo Youth page_የኢኦተቤክ ወጣቶች ፔጅ

Ethiopian Orthodox Tewahdo Youth page_የኢኦተቤክ ወጣቶች ፔጅ «ነዋ ወንጌለ መንግሥት »
እርስ በርስ በተቀደሰ ሰላምታ ሰላም ተባባሉ!!

የዛሬ ግንቦት 21 ዓመታዊ ክብረ በዓል በደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ቤተክርስቲያን በምስል🙏🙏🙏⛪️       የዓመት ሰው ይበለን🙏🙏🙏
29/05/2026

የዛሬ ግንቦት 21 ዓመታዊ ክብረ በዓል በደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ቤተክርስቲያን በምስል🙏🙏🙏⛪️
የዓመት ሰው ይበለን🙏🙏🙏

 !!!!!፨.እነዚህ 5 አገልጋዮች ከአንድ እናትና አባት የተወለዱ ወንድማማቾች ናቸው ብላችሁ ታምናላችሁ?፨.እነዚህ የሚታዩዋቸዉ 5 አገልጋዮች የአንድ ማህፀን ፍሬዎች፣የቅድስት ቤተክርስቲያን ...
28/05/2026

!!!!!

፨.እነዚህ 5 አገልጋዮች ከአንድ እናትና አባት የተወለዱ ወንድማማቾች ናቸው ብላችሁ ታምናላችሁ?

፨.እነዚህ የሚታዩዋቸዉ 5 አገልጋዮች የአንድ ማህፀን ፍሬዎች፣የቅድስት ቤተክርስቲያን አገልጋዮች ናቸው።
​ከአንድ እናትና አባት ተወልዶ እንዲህ በአንድነት ለእግዚአብሔር ቤት መቆም እንዴት መታደል ነው።
እግዚአብሔር የአገልግሎት እድሜአችሁን ያርዝምላችሁ 🤲❤
via:- Gamo Arbaminch

በድንጋይ ላይ መፃፍ ✍!​ሁለት እጅግ የሚዋደዱ ጓደኛሞች በረሃ ውስጥ እየተጓዙ እያሉ ድንገት አለመግባባት ተፈጠረና አንደኛው ጓደኛ ሌላኛውን በጥፊ ይመታዋል የተመታው ጥፊው ቢያመውም ምንም ሳ...
27/05/2026

በድንጋይ ላይ መፃፍ ✍!

ሁለት እጅግ የሚዋደዱ ጓደኛሞች በረሃ ውስጥ እየተጓዙ እያሉ ድንገት አለመግባባት ተፈጠረና አንደኛው ጓደኛ ሌላኛውን በጥፊ ይመታዋል የተመታው ጥፊው ቢያመውም ምንም ሳይናገር ዝም አለና አሸዋው ላይ " " ብሎ ፃፈ።
ከዛም እየተጓዙ እያሉ ትልቅ ባህር ያለበት ወንዝ ያገኙና መታጠብ ፈልገው ይገባሉ እየዋኙ እያሉ ያ በጥፊ የተመታው ልጅ ድንገት አዳልጦት ወድቆ ይሰምጣል በዚህ ስዓት ጓደኛው እንደምንም ብሎ ሂወቱን ያተርፈዋል ከሞት የተረፈው ልጅ ቋጥኝ ድንጋይ ፈልጎ ድንጋዩ ላይ እየፈለፈለ " " ብሎ ፃፈ። ጓደኛውም ገርሞት ቅድም በጥፊ ስመታህ አሸዋ ላይ ፃፍክ አሁን ከሞት ሳተርፍህ ደግሞ እድንጋይ ላይ ለምን እንደዚህ አደረክ አለው... ጓደኛውም እንዲህ አለው "የምንወዳቸው ሰወች ሲበድሉን በደላችንን የይቅርታ እና የምህረት ንፋስ እንዲያጠፋው አሸዋ ላይ መፃፍ አለብን መልካም ነገር ሲያደርጉልን ግን ውለታቸውን እንዳንረሳ ሁሌም እንድናስታውሰው ድንጋይ ላይ መፃፍ አለብን አለው!!"

የዕለቱ መልእክት 🗨️
የምህረት ሰው መሆን ብዙ ነገር ያተርፋል:እንኳንስ ያልበደለህ ወንድምህ ይቅርና የበደለህ ሰውም ይቅርታ/ምህረት/ማድረግን የብልህነት መገለጫ ነው፤ምክንያቱም የነገ መንገድህ ነውና እያስተካከልክ ያለኸው።




የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ፓትርያርክ አቀባበል 1951ዓ.ም                     [ #አዲስ አበባ_ኢትዮጵያ ]፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ...
26/05/2026

የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ፓትርያርክ አቀባበል 1951ዓ.ም
[ #አዲስ አበባ_ኢትዮጵያ ]
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ፓትሪያርክ ሆነው በታህሳስ ወር 1951 ዓ.ም ተሹመው፣ በጥር ወር 1951 ዓ.ም በክብር መንበራቸው ላይ ተቀምጠዋል።

ታሪካዊው የአቀባበል ስነ-ስርዓት ዋና ዋና ክንውኖች የሚከተሉት ነበሩ፡

የጉዞው መደምደሚያ: አቡነ ባስልዮስ ከግብጽ (እስክንድርያ) መንበረ ፓትርያርክ የቅብብሎሽ (የአውቶሴፋሊ) ደብዳቤ ይዘው በአውሮፕላን አዲስ አበባ ገቡ።

የአዲስ አበባ አቀባበል: አፄ ኃይለሥላሴ፣ የካቢኔ ሚኒስትሮች፣ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ አእላፍ ህዝብና የክብር ዘበኛ ሰራዊት በተገኙበት በታላቅ ድምቀት በአውሮፕላን ማረፊያው ታላቅ አቀባበል ተደረገላቸው።

የንግስና ስነ-ስርዓት: ከመንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ጀምሮ እስከ መንበረ ፓትርያርክ (በአሁኑ አራዳ አካባቢ) በተደረገው ታላቅ የህዝብ ሰልፍና የሆታ አቀባበል አባቱ ወደ መንበራቸው ገቡ።

✍️ተጻፈ በመ/ር በአማን ነጸረ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨በስመ፡ አብ፡ ወወልድ፡ ወመንፈስ፡ ቅዱስ፡ ፩ዱ፡ አምላክ፡ አሜን። ዛቲ ፡ጦማር፡ ተፈነወት ፡ እምነ፡ ደባትረ፡ ...
22/05/2026

✍️ተጻፈ በመ/ር በአማን ነጸረ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በስመ፡ አብ፡ ወወልድ፡ ወመንፈስ፡ ቅዱስ፡ ፩ዱ፡ አምላክ፡ አሜን።

ዛቲ ፡ጦማር፡ ተፈነወት ፡ እምነ፡ ደባትረ፡ አሐዱ፡ በምግባር፡ ድኩም፡ ባሕቱ፡ በሃይማኖቱ፡ ርቱዕ ፡ ትብጻሕ፡ ኀበ ወኲሎን አድያሚሃ።

ፍቁራን ሊቃውንት ዘምድረ አግኣዚ፥ ለጤናችሁ እንደምን አላችሁ፦

እንደ ዘበት የሚል መስሎኝ ያለፍኩት ልጥፍ መሆኑ ዘግይቶ ገባኝና የግራ ቀኝ ምልልሱን ባየው ነገሩ ሌላ ነው።
--
ሊቃውንተ ትግራይ፦

አስተዳደሩ ላይ እናወራበታለን። ካለን ተመክሮ አንጻር በአንዳንድ ዘመዶቻችን በዚያ አካባቢ የምናየው ቅኝት የ1990ዎቹን የተሐድሶ ቀለም እያስታወሰን ያስተክዘናል። ርእዩ (ተመልከቱ)፣ አንድም ረዓዩ (ጠብቁ)። "ሸዋ"፣ "ማኅበረ ቅዱሳን"፣ "ዘርዐ ያዕቆብ" የሚሉ ብሔርተኝነትን ከሃይማኖት የቀላቀሉ አካሔዶች የአመፃ መሸፈኛ ሲሆኑ እናያለን። ቢቻል ይኽ የ prejudice ተቀጽላ የፍረጃ አጠራር የቅድመ አብዮት ብሉይ (primitive ያላልነው ለጨዋነት ነው) ሥዕለ ሕሊና የተጠናወተው በመሆኑ ተሻገሩት። ካልሆነም እምነቱን ከብሔርተኝነት መለያ አበጁለት።
--
ስለ Icon እና ነገረ ማርያም አጀንዳ የመጣው ከዘርዐ ያዕቆብ ወዲህ አስመስሎ "ብዙሕ ዘመን ተደናጊርና ኢየሱስ ጥራህ" የሚል አደናጋሪ የ Liberation Theology ቅኝት አያያዙ ደስ አይልም። ካለን የቀሳጥያንን ጉዞ የመገምገም ልምድ አንጻር መዳረሻው አይጠፋንም። በእልህ ለኢ-ማርያማውያን "የማርያም መንገድ" ሲከፈት ኢታርምሙ፣ ተናገሩ። ከማዕከል ያለውን በ "exceptionalism" የታቀኘ ግትልትልኤል ወ "የዓለሙ መፋረጃ" ስንታገል በወዲያ በኩል የምታሳዩት የተጋነነ ecclesiastical nationalism እያስቀየመን እንደሆነ አንደብቃችሁም። የተሳሳተ አስተምህሮ በብሔርተኝነት ለመደበቅ ሲሞክር ከለላ አትስጡ፣ ገሥጹ። ሉተርም ሲጀማምረው በጀርመን ብሔርተኝነት ይታከክ እንደ ነበረ ታሪኩን የሰሙት አሰምውተናል። እና... ሊቃውንት ዘምድረ ትግራይ፥ ነገሩ በጊዜ መስመር እንዲይዝ ብትደክሙበት ምኞታችን ነው።
--
ከክርስቶስ ሰላም ጋራ።
ተጽሕፈት እምለሚ ኩራ ደወለ አ.አ።
አመ ፲ወ፬ ለግንቦት ፳፻ወ፲፰ እምልደተ ክርስቶስ

❝ወእንዘ ይባርኮሙ ተረኃቆሙ ወዓርገ ሰማየ❞              ❤🙏🙏🙏🙏🙏❤ሾሟቸው የርቀት ያይደለ የርኅቀት ተሰውሯቸው ወደ ሰማይ ዓረገ። ሉቃ.24:51 ,፳፬÷፶፩        ‟እንኳን ለዕር...
21/05/2026

❝ወእንዘ ይባርኮሙ ተረኃቆሙ ወዓርገ ሰማየ❞
❤🙏🙏🙏🙏🙏❤
ሾሟቸው የርቀት ያይደለ የርኅቀት ተሰውሯቸው ወደ ሰማይ ዓረገ። ሉቃ.24:51 ,፳፬÷፶፩

‟እንኳን ለዕርገተ ክርስቶስ አደረሳችሁ”!!!

" "               «ከአንቺ ጋር የመከረ ለራሱ መከረ» እንዳለ ደራሲው፤ከነፍሳቸው ጋር የመከሩ፣ደጉ ሰው ደግነታቸው እንደቀጠለ ነው፣በቅርቡ በመሬታቸው ቤተክርስቲያን ሰርተው የሰጡ የ...
17/05/2026

" "
«ከአንቺ ጋር የመከረ ለራሱ መከረ»
እንዳለ ደራሲው፤ከነፍሳቸው ጋር የመከሩ፣ደጉ ሰው ደግነታቸው እንደቀጠለ ነው፣በቅርቡ በመሬታቸው ቤተክርስቲያን ሰርተው የሰጡ የመንግሥት ሚኒስቴሩ ደግነት እና የቤተክርስቲያን ፍቅር ቀጥሏል።

◉.የፖለቲካው ገመድ አሥሮ ያላስቀራቸው የክርስቶስና የቤተክርስቲያን ወዳጅ ሚኒስትሩ 🙏🙏
በክብር እና በአገልግሎት ስማቸው ሊቀ ሂሩያን ዲ/ን ተክለወልድ አጥናፉ የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እና በአሁኑ ወቅት የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማክሮ ኢኮኖሚ አማካሪ በደግነታቸው ብዙዎችን እያነጋገሩ ይገኛሉ።

በወላይታ ዞን በዳሞት ጋሌ ወረዳ ቤተክህነት ቦዲቲ ከተማ አዲስ #በመጠናቀቅ ላይ ላለችው ለቦዲቲ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን መስርያ የሚሆን ብር ገቢ አድርገዋል እግዚአብሔር ይስጥልን።

እግዚአብሔር ይጠብቅልን በነፍስ በስጋም።

እንዲህ ያሉትን አስተዋይና ደጋግ ሰዎች እግዚአብሔር ደያብዛልን በእውነት 🙏👏
Via Andualem Andualem Degefu

◉.የሳዑዲ አረቢያ ባለሥልጣናት ሞት ለተፈረደባቸው ኢትዮጵያውያን “ምሕረትን እንዲያደርጉ፣ ቅጣቱንም ወደ እስራት እንዲቀይሩ” የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ፓትርያርክ አባ ማት...
13/05/2026

◉.የሳዑዲ አረቢያ ባለሥልጣናት ሞት ለተፈረደባቸው ኢትዮጵያውያን “ምሕረትን እንዲያደርጉ፣ ቅጣቱንም ወደ እስራት እንዲቀይሩ” የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ፓትርያርክ አባ ማትያስ ጥሪ አቀረቡ። የኢትዮጵያ መንግሥት በከፍተኛ ደረጃ ከሚገኙ ከሳዑዲ አረቢያ ባለሥልጣናት ጋር በመነጋገር በዜጎቹ ላይ የተላለፈው “የሞት ፍርድ እንዲነሳላቸውና ወደ ሀገራቸው የሚመለሱበት መንገድ ይመቻች ዘንድ የተጀመሩ ሥራዎች ልዩ ትኩረት እንዲሰጥባቸው” አሳስበዋል።
አባ ማትያስ ኢትዮጵያውያኑ “በቋንቋ እጥረት እና በሕግ አማካሪ እጦት ለሞት እንዳይዳረጉ” ያሳሰቡት ትላንት ማክሰኞ ባስተላለፉት መልዕክት ነው። በመልክታቸው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች “በማያውቁት ቋንቋ እንዲሁም ባልተረዱት የሕግ ሂደት ሞት የተፈረደባቸውን ወገኖች ሥቃይ ተመልክተው የፍትሕ መዛባትን እንዲቃወሙ እና የንጹሐንን ነፍስ እንዲታደጉ” ጥሪ አቅርበዋል።
በሳዑዲ አረቢያ ከአደንዛዥ ዕጽ ጋር በተያያዙ ክሶች ቢያንስ 65 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በሞት ሊቀጡ እንደሚችሉ ሒውማን ራይትስ ዎች ባለፈው ሚያዝያ 20 ቀን 2018 አስታውቆ ነበር። የሳዑዲ አረቢያ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ሦስት ኢትዮጵያውያን ወደ ሳዑዲ አረቢያ በሕገ-ወጥ መንገድ “ሐሺሽ በማስገባት ውስጥ ተሳትፈዋል” በሚል ክስ በሞት መቀጣታቸውን ባለፈው ሚያዝያ 13 ቀን 2018 እንዳስታወቀ ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ይፋ አድርጓል።

ሞት ከተፈረደባቸው ኢትዮጵያውያን መካከል መካከል ከጥቅምት 2013 እስከ ጥቅምት 2015 በትግራይ ክልል ከተካሔደው ጦርነት የሸሹ ሦስት ኢትዮጵያውያን በሳዑዲ አረቢያ አሲር ግዛት ኻሚስ ሙሻይት በተባለ እስር ቤት ውስጥ እንደሚገኙ የዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ያወጣው ሪፖርት ይጠቁማል። ሦስቱ ኢትዮጵያውያን ሥራ ፍለጋ በአደን ባሕረ ሰላጤ እና የመንን በሚያቋርጠው አደገኛ የፍልሰት መስመር ተጉዘው ሳዑዲ አረቢያ የገቡ ናቸው።
📷.credited via:- DW Amharic

«ዓለም ለማይችለው አምላክ ማኅጸኗን ዓለም አድርጋ የወሰነች ከዓለም የሰፋች ፣ከዓለም የተለየች አማናዊት ሀገር እመብርሃን በዓለም የተገኘችበት ክብርት ዕለት ግንቦት ፩❤              ...
09/05/2026

«ዓለም ለማይችለው አምላክ ማኅጸኗን ዓለም አድርጋ የወሰነች ከዓለም የሰፋች ፣ከዓለም የተለየች አማናዊት ሀገር እመብርሃን በዓለም የተገኘችበት ክብርት ዕለት ግንቦት ፩❤
« እንኳን አደረሳችሁ🙏🙏🙏»

እግዚአብሔር ይመሰገን ወንድማችን ተፈቷል🙏🙏🙏  በማድረግ ለተጨነቁት ወዳጆች ሁሉ ብሥራትን እናሰማ!!
06/05/2026

እግዚአብሔር ይመሰገን ወንድማችን ተፈቷል🙏🙏🙏
በማድረግ ለተጨነቁት ወዳጆች ሁሉ ብሥራትን እናሰማ!!

‟አመ ይመጽእ ወልድኪ መድኃኔዓለም ክፍልኒ ድንግል እቊም በየማን”🎶🎶         🎶🎶🎶🎶‟መድኃኔዓለም በያላችሁበት ከክፉ ነገር ሁሉ ይጠብቃችሁ”!
05/05/2026

‟አመ ይመጽእ ወልድኪ መድኃኔዓለም
ክፍልኒ ድንግል እቊም በየማን”🎶🎶
🎶🎶🎶🎶
‟መድኃኔዓለም በያላችሁበት ከክፉ ነገር ሁሉ ይጠብቃችሁ”!

Address

Main Road
Alamat'a

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Orthodox Tewahdo Youth page_የኢኦተቤክ ወጣቶች ፔጅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Ethiopian Orthodox Tewahdo Youth page_የኢኦተቤክ ወጣቶች ፔጅ:

Share