የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል Addis Ababa Muslim Youth Council

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል Addis Ababa Muslim Youth Council

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል Addis Ababa Muslim Youth Council የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ጥር 03 ቀን 2018 ተመሰረተ

23/05/2026

የሐጅ አደራረግ በሸኽ ኢልያስ አህመድ ከመካ ሀያ ሆቴል

በአዲስ አበባ በቤተል ተቅዋ መስጂድ ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ተካሄደሚያዝያ 25/2018በዛሬውእለት እሁድ ሚያዝያ 25 ቀን በአዲስ አበባ ከተማ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ቤቴል ተቅዋ መስጂድ...
03/05/2026

በአዲስ አበባ

በቤተል ተቅዋ መስጂድ ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ተካሄደ

ሚያዝያ 25/2018

በዛሬውእለት እሁድ ሚያዝያ 25 ቀን በአዲስ አበባ ከተማ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ቤቴል ተቅዋ መስጂድ በአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከ/ም/ቤት ስር የኮልፌ ቀራኒዮ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል አዘጋጅነት ታላቅ የዳእዋ ፕሮግራም ተካሄደ።
በክፍለ ከተማው ወጣቶች ካውንስል የተዘጋጀው ይኸው የዳእዋ ፕሮግራም በዋናነት ተቅዋ በሚል ርዕስ በኡስታዝ ሙሀመድ ሃሰን ማሜ የተደረገ መሳጭ ዳእዋ እና አራያችን ማን ነው ? በሚል ርዕስ በኡስታዝ ካሚል ጣሀ የተዘጋጀ ሁለት ሙሃደራ ያካተተ ሲሆን ፕሮግራሙ በቁርአን ተከፍቶ በአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ፀሀፊ ኡስታዝ አብዱል አዚዝ አወል ንግግር የተጀመረ ፕሮግራም ነበር።
ፕሮግራሙን በርካታ ምእመናን የተሳተፉበት ሲሆን የታዳሚው ጆሮ ሰጥቶ የማዳመጥ ሁኔታው መሰል ፕሮግራሞች መበራከት እንዳለባቸው ጠቋሚ ነው።

03/05/2026

በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች
በክፍለ ከተማው ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የተዘጋጀ የሙሀደራ ፕሮግራም

በቤተል ተቅዋ መስጂድ

ኡስታዝ ሙሐመድ ሀሰን ማሜ እና
ኡስታዝ ካሚል ጣሀ

በአዲስ አበባ ደረጃ ሲካሄድ የነበረው የቁርአን ውድድር የዑምራ ሽልማት በማበርከት ተጠናቀቀ።ዜና፣መጅሊስ፣የካቲት 23/2018 ዓ.ል. አ.አ.በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተካሂዶ ለዛሬው የፍፃሜ ውድድ...
02/03/2026

በአዲስ አበባ ደረጃ ሲካሄድ የነበረው የቁርአን ውድድር የዑምራ ሽልማት በማበርከት ተጠናቀቀ።

ዜና፣መጅሊስ፣የካቲት 23/2018 ዓ.ል. አ.አ.

በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተካሂዶ ለዛሬው የፍፃሜ ውድድር የደረሰው ይህ የቁርአን ውድድር በሁለቱም ፆታ የተከናወነ ሲሆን ወጣቶችና ታዳጊዎች ከቁርአን ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንደሚያጠናክሩ የማድረግ ዓላማ ይዞ ተከናውኗል።

በመድረኩ ላይ የወጣት ካውንስሉ ምክትል ፕሬዝደንት ወጣት አሚር ሻፊ እንደተናገረው ክፍለ ከተሞች በሁለቱም ፆታ አወዳድረው 20 ዕጩዎችን ለአዲስ አበባ መላካቸውን አብራርቷል።

የውድድሩ ዓላማ ወጣቶችና ታዳጊዎች ከቁርአን ጋር ያለንን ግንኙነት ለማጠናከር የተዘጋጀ መሆኑን የተናገረው ወጣት አሚር በቀጣይ ሰፊ ጊዜ እና ትኩረት ተሰጥቶት የሚሠራ ይሆናል ብሏል።

ለዚህ ተግባር የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል በዋነኛነት ድጋፍ ያደርጋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የአዲስ አበባ መጅሊስ ዋና ፀሐፊ ኡስታዝ ሺሐቡዲን ሼህኑራ ቁርአንን በተለምዶ ማንበብ ብቻ ሳይሆን በዘወትር ሕይወታችን ላይ ተፅዕኖ ማሳደር መቻል አለበት ብለዋል። ዋና ፀሐፊው ኡስታዝ ሺሐቡዲን ቁርአን በሚያናግረን ጊዜ የሚያዘንን ተረድተን በዛው መሠረት መሥራትና ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።

ቁርአንን የምናይበት መንገድ መስተካከል አለበት፤ ሊመራንና ሊያዘን የመጣ መሆኑን አውቀን ትስስራችንን ማጠንከር አለብን ሲሉ ዋና ፀሐፊው ተናግረዋል።

ዋና ፀሐፊው ለሑፋዞች ባስተላለፉት መልዕክት ቁርአንን መሃፈዝ የመጨረሻው ግብ አለመሆኑን በመረዳት ሂፍዛችሁን ዘላቂ ማድረግ እና በውድድር ጊዜም ንያን ማስተካከል ይገባል ብለዋል።

ቁርአን ከአላህ ጋር መነጋገሪያ መንገዳችን በመሆኑ ቁርኝታችንን የበለጠ ማሳደግ፤ ስነ ምግባራችንን ማሳመርና በቁርአኑ ሰርቶ የበለጠ ማስረፅ ተገቢ እንደሆነ አፅንኦት ሰጥተው አሳስበዋል።

የአዲስ አበባ መጅሊስ ምክትል ፕሬዝደንት ሼህ ሙሐመድ ሸሪፍ መጅሊስ ከሚሠራቸው ስራዎች ውስጥ ወጣቶችን ማደራጀት ሲሆን የመደራጀቱን አስፈላጊነትም እያሣየን ነው ብለዋል።

ወጣቶችን ያላሳተፈ ስራ ውጤታማ አይሆንም ያሉት ምክትል ፕሬዝደንቱ ሼህ ሙሐመድ ይህንን ዓይነት የቁርአን ውድድር ማጠናከር እንደሚገባ ገልፀዋል። ለዚህም የተጀመረውን የወጣቶች የአምስት ሚሊየን አባልነት ምዝገባ በትብብር ማጠናቀቅ እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።

ከቁርአን ጋር ያለንን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ታዳጊዎች ላይ መስራት እንደሚያስፈልግ ምክትል ፕሬዝደንቱ አሳስበዋል።

በዛሬው የማጠቃለያ ውድድር በወንዶች፦

1ኛ. ቃሪዕ ኑዓይም ጃቢር ከለሚኩራ ክፍለ ከተማ

2ኛ. ቃሪዕ ኻሊድ አሕመድ ከኮልፌ ክ/ከተማ

3ኛ. ቃሪዕ አብዱልመናን ሙሐመድ ከኮልፌ ክፍለ ከተማ ሆነው ያጠናቀቁ ሲሆን በሴቶች ደግሞ

1ኛ. ኢንቲሳር ጀማል ከልደታ ክፍለ ከተማ

2ኛ. ጦይባ ሙደሲር ከኮልፌ ክፍለ ከተማ እና

3ኛ. ራሕመት አብዱልቃድር ከልደታ ክፍለ ከተማ ሆነው አጠናቀዋል። ይህ ወጣቶችን የበለጠ ከቁርአን ጋር ያላቸውን ቁርኝት ያጠናክራል የተባለው የቁርአን ውድድር ቀጣይነት እንደሚኖረው ተገልጿል።

በአዲስ አበባ ከተማ ክፍለ ከተሞች ሲካሄድ የነበረው ከተማ አቀፍ የቁርአን ውድድር የፍፃሜ ውድድር በዛሬው እለት እየተካሄደ ይገኛል።የወንድ ተወዳዳሪዎች በጦር ሀይሎች ረያን መስጂድና በሴቶች ...
02/03/2026

በአዲስ አበባ ከተማ ክፍለ ከተሞች ሲካሄድ የነበረው ከተማ አቀፍ የቁርአን ውድድር የፍፃሜ ውድድር በዛሬው እለት እየተካሄደ ይገኛል።

የወንድ ተወዳዳሪዎች በጦር ሀይሎች ረያን መስጂድና በሴቶች ደግሞ አ/አበባ መጅሊስ መሰብሰቢያ አዳራሽ እየተካሄደ የሚገኘው የቁርአን ውድድር በውድድሩ በሁለቱም ፆታ 1ኛ የወጡ ተወዳዳሪዎች የዑምራ ሽልማት የሚሸለሙ ሲሆን 2ኛና 3ኛ ለወጡ ደግሞ ለእያንዳንዳቸው የ50ሺ ብር እና የ30ሺ ብር ሽልማት የሚሸለሙ ይሆናል!

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የ ቁርአን ሂፍዝ ውድድር የመጨረሻ የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር በጦር ሀይሎች ረያን መስጂድ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
02/03/2026

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የ ቁርአን ሂፍዝ ውድድር የመጨረሻ የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር በጦር ሀይሎች ረያን መስጂድ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

ከተማ አቀፉ የቁርአን ማጣሪያ ውድድር የመጨረሻ ዕጩዎችን በማሳወቅ ተጠናቀቀ።ዜና፣መጅሊስ፣የካቲት 22/2018 ዓ.ል. አ.አ.በአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የአዶስ አ...
01/03/2026

ከተማ አቀፉ የቁርአን ማጣሪያ ውድድር የመጨረሻ ዕጩዎችን በማሳወቅ ተጠናቀቀ።

ዜና፣መጅሊስ፣የካቲት 22/2018 ዓ.ል. አ.አ.

በአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የአዶስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ያዘጋጀው የረመዳን ወር የቁርአን ውድድር ነገ በታላቅ ድምቀት ይጠናቀቃል። ለዚህ የመጨረሻ ዙር ለመድረስ ከየክፍለ ከተሞቹ ተወክለው የነበሩ ሐፊዞች ዛሬ የመጨረሻውን የማጣሪያ ውድድር አድርገዋል።

ውድድሩ በወንድም በሴትም የተከናወነ ሲሆን በአዲስ አበባ መጅሊስ ትልቁ አዳራሽ የተከናወነውን የወንዶች ውድድር ውጤት ዳኞች ይፋ አድርገዋል።

በዚህም መሠረት በወንዶች፦

1ኛ. ቃሪዕ ኻሊድ አሕመድ ኮልፌ
2ኛ. ኑዓይም ጃቢር ለሚኩራ

3ኛ. አሕመድ ኢማም የካ
4ኛ. አብዱልመናን ሙሐመድ ኮልፌ

5ኛ. ጁነይድ ሰዒድ ጉለሌ
6ኛ. ሱሀይብ ከቢር ቃሊቲ ሆነው አጠናቀዋል።

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ያዘጋጀው የቁርአን ውድድር ነገ በረያን መስጂድ ፍፃሜውን የሚያገኝ ይሆናል።

በነገው መድረክ ላይ ከአንድ እስከ ሶስት የሚወጡ ልዩ ሽልማት የሚበረከትላቸው ይሆናል።

ዑምራ የሚያሸልመው ውድድር ነገ ይካሄዳልበተከበረዉ የረመዳን ወር ታላቅ የቁርአን ዉድድር ጦርሀይሎች ረያን መስጂድበሁለቱም ፆታዎች በክፍለ ከተማ ደረጃ በሚገኙ መስጂዶች ሲደረግ የነበረዉ የቁር...
01/03/2026

ዑምራ የሚያሸልመው ውድድር ነገ ይካሄዳል

በተከበረዉ የረመዳን ወር ታላቅ የቁርአን ዉድድር ጦርሀይሎች ረያን መስጂድ

በሁለቱም ፆታዎች በክፍለ ከተማ ደረጃ በሚገኙ መስጂዶች ሲደረግ የነበረዉ የቁርአን ሂፍዝ ዉድድር በነገዉ እለት ፍፃሜዉን ሲያደርግ በሁለቱም ፆታ በአንደኝነት ለሚያጠናቅቁ ተወዳዳሪዎች የኡምራ ፓኬጅ ሽልማት ሲበረከትላቸዉ ሁለተኛ ለሚወጡ 50ሺ ሶስተኛ ለሚወጡ ተወዳዳሪዎች ደሞ የ30ሺ ብር ሽልማት ይበረከትላቸዋል

የወንዶቹን ዉድድር በወንድ ዳኞች በረያን መስጂድ ሲያከናዉን የሴቶቹ የፍፃሜ ዉድድር ደሞ በሴት ዳኞች አዲስ አበባ መጅሊስ ጊቢ 5ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘዉ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይደረጋል

ሁላቹም ቦታዉ ድረስ መታቹ እንድትታደሙ በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን

ሰአት ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ

በአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል አዘጋጅነት በተለያዩ ክፍለ ከተማዎች ሲካሄድ የቆየው የቁርአን ውድድር በአዲስ አበባ በከተማ ደረጃ የአሸናፊዎች አሸናፊ የማጣሪያ ውድድር በአዲስ አበባ ...
01/03/2026

በአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል አዘጋጅነት በተለያዩ ክፍለ ከተማዎች ሲካሄድ የቆየው የቁርአን ውድድር በአዲስ አበባ በከተማ ደረጃ የአሸናፊዎች አሸናፊ የማጣሪያ ውድድር በአዲስ አበባ መጅሊስ መሰብሰቢያ አዳራሽ እየተካሄደ ይገኛል

የውድድሩ አሸናፊዎች በነገው እለት በጦር ሀይሎች ረያን መስጂድ በይፋ የሚከናወን ሲሆን በሁለቱም ፆታዎች 1ኛ ለሚውጡ ተወዳዳሪዎች ለእያንዳንዳቸው የዑምራ ሽልማት የሚሸለሙ ይሆናል።

የዑምራ ሽልማት የሚያስገኘው በአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የተዘጋጀው የቁርአን ሂፍዝ ውድድር በሁለቱም ፆታ መካሄድ ጀምሯል።
01/03/2026

የዑምራ ሽልማት የሚያስገኘው በአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የተዘጋጀው የቁርአን ሂፍዝ ውድድር በሁለቱም ፆታ መካሄድ ጀምሯል።

Address

Tor Hailoch
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል Addis Ababa Muslim Youth Council posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share