የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል Addis Ababa Muslim Youth Council

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል Addis Ababa Muslim Youth Council

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል Addis Ababa Muslim Youth Council የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ጥር 03 ቀን 2018 ተመሰረተ

የአዲስ አበባ መጅሊስ ሀገራዊ ተሳትፎ ቀጥሏል፤ ክፍለ ከተሞችም በከተማቸው ንቅናቄ ላይ በልዩ ሁኔታ እየተሳተፉ ነው።ዛሬ በተጀመረው የአንድ ጀምበር የ800 ሚሊየን ችግኝ ተከላ ላይ የተለያዩ ...
03/08/2026

የአዲስ አበባ መጅሊስ ሀገራዊ ተሳትፎ ቀጥሏል፤ ክፍለ ከተሞችም በከተማቸው ንቅናቄ ላይ በልዩ ሁኔታ እየተሳተፉ ነው።

ዛሬ በተጀመረው የአንድ ጀምበር የ800 ሚሊየን ችግኝ ተከላ ላይ የተለያዩ አካባቢዎችና ተቋማት ተግባሩን በስፋት እያከናወኑ ይገኛሉ። ሁሉም የክፍለ ከተማ መጅሊሶች የዚህ ንቅናቄ አካል በመሆን በንቃት እየተሳተፉ ሲሆኑ በኮልፌ ክፍለ ከተማ በነበረው መርሃ ግብር ላይ የአዲስ አበባ መጅሊስ አመራሮችና ስራ አስፈጻሚዎች፤ የከተማው፤ የፌደራል እና የሁሉም ክልል ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል አመራሮች፣ የኮልፌ መጅሊስ ስራ አስፈጻሚዎችና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።

ለህፃናት በተደረገ የችግኝ ማበርከት ስነ ስርዓት የተጀመረው ችግኝ ተከላው ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች በተዘጋጀው ቦታ ላይ ተተክሏል።

በዚህ መድረክ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ሼህ ሱልጣን ሐጂ አማን ኤባ የአረንጓዴ አሻራ ተግባር የተጀመረው ለመጪው ትውልድ ምቹ፣ ውብና አረንጓዴ የለበሰች ሀገር ለማስረከብ በማሰብ መሆኑን ተናግረዋል።

ተግባሩ የአፈር መሸርሸርን ብቻ ለመከላከል ሳይሆን፣ የውሃ ሃብታችንን ለመጠበቅ፤ የዓለም አየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም ጭምር መሆኑን ፕሬዝደንቱ ሼህ ሱልጣን አማን ገልፀዋል።

ተግባሩ በዲናችን የታዘዝንበት በመሆኑ የአዲስ አበባ መጅሊስ እንደቀደመው ሁሉ የዘንድሮውን የክረምት መርሃ ግብር ከሐምሌ 15/2018 ጀምሮ በተለያየ ዘርፍ አጠናክሮ ቀጥሏል ያሉት ሼህ ሱልጣን አማን ሀገራችንን ማልማት፤ ሠላሟን ማስጠበቅና ለሀገራችን ጥሪ ምላሽ መስጠት ቀዳሚ ኃላፊነታችን ነው በማለት ተናግረዋል።

ችግኝ ስንተክል፤ ትውልድን መትከል፤ ሀገራችንን ማልማት ነውና በተግባሩ ላይ በንቃት መሳተፍ ያስፈልጋል በማለት አሳስበዋል።

ችግኝ መትከል ምድርን መጠበቅ መሆኑን ያስታወሰው የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ፕሬዝደንት ኡስታዝ ሐይደር ከድር ሲሆን ችግኝ ተከላው ተፈጥሮን ንፁህ ማድረግና ትልቅ ተግባር መሆኑን ገልጿል። ዓለምን እያስጨነቀ ያለው የአየር ንብረት ለውጥን ተፅዕኖ ለመቋቋምና ተፈጥሮን ለመጠበቅ ችግኝ ተከላ ወሳኙ መፍትሔ መሆኑንም አንስቷል።

የአዲስ አበባ መጅሊስ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝደንት ሼህ ሙሐመድ ሸሪፍ ችግኝ ስንተክል ሰላምንና አብሮነትን መትከል ያስፈልጋል ብለዋል።

የአዲስ አበባ መጅሊስ አስተዳደራዊ ጉዳዮች እና ተቋማዊ ልህቀት ምክትል ፕሬዝደንት ኡስታዝ ሺሐቡዲን ሼህ ኑራ ተፈጥሮን መንከባከብ ከዲነል ኢስላም አንፃር ሲታይ ተሻጋሪ መሆኑንና ቀጣዩን ትውልድ እንዲጠቅም መደረግ ላይ ማተኮርና ልብ ማለት ያስፈልጋል ብሏል።

ኡስታዝ ሺሐቡዲን ሼህ ኑራ ወጣቶች ከዚህ ኢስላማዊ ትዕዛዝና ተግባር መማር ያለባቸው፤ የሚሠሯቸው ስራዎች ለሌሎች ሰዎች የሚጥቅሙ መሆናቸውን ማረጋገጥና ቀጣይነቱን ማሰላሰል ያስፈልጋል ብለዋል።

ተቋም ስንገነባ እኔ ባልኖር እንዴት ለሌሎች ጠቃሚ መሆን ይችላል የሚለውን ጥያቄ በተገቢው መመርመርና ሂደቱንም በንቃት መከታተል ይገባል ያሉት ኡስታዝ ሺሐቡዲን ችግኝ ተከላውንም በዚህ የተሻጋሪ እሳቤ መስራት ያስፈልጋል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የኮልፌ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ስራ አስፈጻሚ ኡስታዝ ሐሺም ሺፋ የዛሬው ተግባር በቀረበው ብሔራዊ ጥሪ መሠረት ነብያዊ አስተምህሮን መነሻ አድርገን፤ ተፈጥሮን ስለመንከባከብ ለትውልድ አስተምረንበት የሚያልፍ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል።

ይህ መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት በዘመቻ መልኩ የሚከናወን ቢሆንም በዲናዊና ትዕዛዝነቱ ምክንያት በመጅሊስ በኩል ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።

ስፖርት የወጣቶችን አካላዊና አእምሯዊ ግንባታ ለማድረግ ወሳኝ ነው።ዜና አዲስ አበባ ሙስሊም ወጣት ካዉንስል ሐምሌ 24/2018ዓ.ል የቦሌ ክፍለ ከተማ ወጣቶች ካውንስል የክረምት በጎ ፈቃድ ን...
31/07/2026

ስፖርት የወጣቶችን አካላዊና አእምሯዊ ግንባታ ለማድረግ ወሳኝ ነው።

ዜና አዲስ አበባ ሙስሊም ወጣት ካዉንስል ሐምሌ 24/2018ዓ.ል


የቦሌ ክፍለ ከተማ ወጣቶች ካውንስል የክረምት በጎ ፈቃድ ንቅናቄ አካል የሆነውን የእግር ኳስ ውድድር አስጀመረ።

በአዲስ አበባ ከተማ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የክረምት በጎ አድራጎት መርሀግብር ላይ ክፍለ ከተሞች የእግር ኳስ ውድድር እና የተለያዩ የበጎ አድራጎት ተግባራትን እያከናወኑ ይገኛሉ።

ከእነዚህ አንዱ ስፖርታዊ ውድድር ሲሆን ክፍለ ከተሞች በወረዳዎች መሀከል የእግር ኳስ ውድድር አካሂደው በከተማ ደረጃ ለሚደረገው ውድድር ተወካዮቻቸውን እያዘጋጁ ይገኛሉ::

በዛሬው የእግር ኳስ ማስጀመሪያ መርሀግብር ላይ የቦሌ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት አመራሮች፤ የአዲስ አበባና የቦሌ ክፍለ ከተማ ወጣት ካውንስል አመራሮች ተገኝተዋል።

በዉድድሩ መክፈቻ ላይ ተገኝተዉ ንግግር ያደረጉት የከተማዉ ወጣት የማህበራዊዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ ተጠሪ የሆኑት ወጣት ፉአድ ሁሴን እንደተናገሩት "ዛሬ በምናስጀምረው በዚህ ውድድር ላይ አሸናፊው ዋንጫ የሚያነሳው ቡድን ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም ስፖርታዊ ጨዋነትን ያሳየ፣ ወንድሙን ያከበረ እና የእስልምናን መልካም እሴቶች በሜዳ ላይ ያስመሰከረው እያንዳንዱ ወጣት ነው"።
ሙሉ ውድድሩን በወንድማማችነት ስሜት፣ በፍቅር እና በደስታ ማጠናቀቅ ከሁላችንም ይጠበቃል ሲሉ መልክታቸዉን አስተላልፈዋል

ወጣቶች ከአላስፈላጊ ቦታዎች ራሳቸውን እንዲቆጥቡ ይህን መሰል የስፖርት ውድድር ጥቅሙ የጎላ መሆኑን የክፍለ ከተማው መጅሊስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሐጂ መብራቱ ሱሩር ተናግረዋል። ስፖርት የወጣቶችን አካላዊና አእምሯዊ ግንባታ ለማድረግ ወሳኝ መሆኑን ገልፀው በዚህ የበለፀገ ወጣት ለሀገሩ ጠቃሚ ስራ ያወናውናል ሲሉ ተናግረዋል።

ሀጅ መብራቱ እንዳሉት ስፖርት ለሀገር የተለያዩ ጥቅሞችን የሚያመጣ እንደመሆኑ መጠን ወጣቶች ራሳቸውን በስፖርት መጠበቃቸው አስፈላጊ ነው ሲሉ ገልፀዋል::

የከተማው ካውንስልም ይህን የእግር ኳስ ውድድር ማዘጋጀቱ ለወጣቶቹ መልካም ነገር ያመጣልና ሊመሰገን ይገባዋል በማለት ገልፀው እንደ ክፍለ ከተማ መጅሊስም ይህን ውድድር የተሻለ ሆኖ እንዲከናወን በተለያየ መልኩ እንደግፈዋለን ብለዋል::

በዚህ ክረምት በካውንስሉ አዘጋጅነት እየተደረገ የሚገኘው የእግር ኳስ ውድድር ዋነኛ ዓላማ የወጣቶችን ወንድድማማችነት ለማጠናከር ታስቦ እንደሆነ ገልጿል::

በዘንድሮ የክረምት የበጎ ፈቃድ ንቅናቄ ወጣቶችን በደም ልገሳ፣ በአረጋውያን ቤት እድሳት፣ በችግኝ ተከላ እያሳተፈ የሚገኘው ወጣት ካውንስል የእግር ኳስ ውድድርም የዚህ የክረምት በጎ ፈቃድ ንቅናቄ አካል እንደሆነ ገልጿል::

የቦሌ ክፍለ ከተማ ወጣት ካውንስል ምክትል ሰብሳቢ ወጣት ቲጃኒ አህመድ በስፖርቱ ዘርፍ ወንድማማችነትን የምናጠናክርበት በመሆኑ በታላቅ ተነሳሽነት የምናከናውነው ውድድር ነው ሲል ገልጿል::

በዛሬው እለት የተጀመረው ውድድር በሚቀጥሉት ቀናትም የተለያዩ የማጣሪያ ጨዋታዎችን በማድረግ በከተማ ደረጃ ለሚደረግ ውድድር ቦሌ ክፍለ ከተማን ወክለው የሚወዳደሩ ቡድኖችን በማሳወቅ ይጠናቀቃል::

የአዲስ ከተማ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የበጎ ፈቃድ የደም ልገሳ መርሃ ግብርን በተሳካ ሁኔታ አካሄደEMYC | ሐምሌ 23፣2018 ዓ.ል (ሰፈር 16፣ 1448 ዓ.ሂ)በአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣ...
30/07/2026

የአዲስ ከተማ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የበጎ ፈቃድ የደም ልገሳ መርሃ ግብርን በተሳካ ሁኔታ አካሄደ

EMYC | ሐምሌ 23፣2018 ዓ.ል (ሰፈር 16፣ 1448 ዓ.ሂ)

በአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል፣ ከክፍለ ከተማው ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት የሰላም እሴት ግንባታና የሀይማኖት ጉዳዮች ዘርፍ ጋር በመተባበር የ2018 ዓ.ል የክረምት የበጎ ፈቃድ ንቅናቄ አካል የሆነ የደም ልገሳ መርሃ ግብርን አካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የካውንስሉ አባላት፣ የወረዳ ወጣቶች፣ የእግር ኳስ ተጫዋቾችና ሌሎች ተሳታፊዎች ተሳትፈው ደማቸውን በመለገስ የሕይወት ማዳን ባህልን በተግባር አሳይተዋል። መርሃ ግብሩም ወጣቶች ለሀገራቸውና ለማህበረሰባቸው ያላቸውን ቁርጠኝነት፣ አጋርነትና ሰብአዊ እሴት በግልጽ ያሳየ ተግባር ሆኗል።

በዝግጅቱ ላይ የተገኙ ኃላፊዎች እንደገለጹት፣ ይህ የደም ልገሳ መርሃ ግብር የአንድ ቀን እንቅስቃሴ ብቻ ሳይሆን በክፍለ ከተማው በሚገኙ መስጂዶችና በተለያዩ ማህበረሰብ መድረኮች በቀጣይነት የሚስፋፋ ሰብአዊ ንቅናቄ መሆኑን ገልጸዋል።

በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የእግር ኳስ የማጣሪያ ውድድር በይፋ ተጀመረAAMYC | ሐምሌ 18፣ 2018 ዓ.ል የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል በመላ ሀገሪቱ እ...
25/07/2026

በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የእግር ኳስ የማጣሪያ ውድድር በይፋ ተጀመረ

AAMYC | ሐምሌ 18፣ 2018 ዓ.ል

የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል በመላ ሀገሪቱ እያካሄደ ያለው የክረምት የወጣቶች ንቅናቄ መርሃ ግብር በተለያዩ መዋቅሮች በተጠናከረ ሁኔታ በመቀጠል ላይ ሲሆን፣ በአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ያዘጋጀው የ11 ወረዳዎች የክረምት የእግር ኳስ የማጣሪያ ውድድር በኮልፌ መብራት ኃይል አካባቢ በሚገኘው "መላጣ ሜዳ" በይፋ ተጀምሯል።

በመክፈቻ መርሃ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ፕሬዝዳንት ወጣት መንሱር ከድር፣ የኮልፌ ቀራኒዮ እስልምና ጉዳዮች ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኡስታዝ ሀሺም ሽፋ፣ የክፍለ ከተማው የሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ሰብሳቢ ወጣት አብዱልአዚዝ አወል፣ ዑለሞች፣ ዱዓቶች፣ የመጅሊስ አመራሮች፣ እና ሌሎች እንግዶች በመገኘት ውድድሩን በይፋ ከፍተዋል።

በመድረኩ መልዕክት ያስተላለፉ አመራሮች፣ ስፖርት ከውድድር ባሻገር ወጣቶችን የሚያቀራርብ፣ ወንድማማችነትንና አንድነትን የሚያጠናክር፣ ጤናማ አኗኗርን የሚያበረታታ እንዲሁም ወጣቶችን ከመስጂድ እና ከማህበረሰባቸው ጋር የሚያስተሳስር ጠቃሚ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል።

የማጣሪያ ውድድሩ 11 ወረዳዎችን የሚያሳትፍ ሲሆን፣ በመጨረሻም ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማን ወክለው በአዲስ አበባ ከተማ አቀፍ የእግር ኳስ ውድድር የሚሳተፉ 4 ቡድኖች ይለያሉ።

ይህ የእግር ኳስ ውድድር የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የክረምት የወጣቶች ንቅናቄ መርሃ ግብር አካል ሲሆን፣ ወጣቶች በስፖርት አማካኝነት እንዲተዋወቁ፣ እንዲተሳሰሩ እና ለሀገርና ለማህበረሰብ የሚጠቅሙ እሴቶችን እንዲያጎለብቱ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

የመዲናዋ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል «ንቁ ወጣት ለተሻለ ነገ» በሚል መሪ ቃል የ2018 የክረምት የበጎ ፈቃድ ንቅናቄን በይፋ አስጀመረየአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል «ንቁ ወጣት ለተሻ...
22/07/2026

የመዲናዋ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል «ንቁ ወጣት ለተሻለ ነገ» በሚል መሪ ቃል የ2018 የክረምት የበጎ ፈቃድ ንቅናቄን በይፋ አስጀመረ

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል «ንቁ ወጣት ለተሻለ ነገ!» በሚል መሪ ቃል በከተማ አቀፍ ደረጃ የሚካሄደውን የ2018 የክረምት በጎ ፈቃድ ንቅናቄ መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት (ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም) በሰጠው መግለጫ በይፋ አስጀምሯል።
የካውንስሉ ፕሬዝዳንት አቶ መንሱር ኸድር እንደገለጹት፤ ንቅናቄው ወጣቶች የዕረፍት ጊዜያቸውን በማህበራዊ አገልግሎት፣ በአካባቢ ጥበቃ እና በሰብዓዊ ድጋፎች ላይ እንዲያሳልፉ ለማስቻል የተዘጋጀ ነው። ይህም የወጣቶችን የበጎ ፈቃደኝነት፣ የአንድነት እና የመረዳዳት ባህል ለማጠናከር ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተጠቅሷል።
ካውንስሉ ከዚህ ቀደምም በበጎ ፈቃድ ሥራዎች ላይ በመሳተፍ የቁሳቁስ፣ የገንዘብ፣ የጊዜና የጉልበት አስተዋፅኦ ሲያደርግ መቆየቱን ያስታወሱት ፕሬዝዳንቱ፤ የዘንድሮው መርሃ ግብር በተለይም ወጣቶችን እና ድጋፍ የሚሹ የማኅበረሰብ ክፍሎችን ማዕከል አድርጎ እንደሚሠራ አብራርተዋል።
በክረምት ንቅናቄው የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፡
የደም ልገሳ፡ በሕክምና ላይ የሚገኙ ወገኖችን ሕይወት ለማዳን የታለመ የደም ልገሳ ዘመቻ።
የአረንጓዴ አሻራ፡ የአካባቢ ጥበቃን ያገናዘበ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር።
የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ፡ አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች ለቀጣይ የትምህርት ዘመን የሚሆኑ ቁሳቁሶችን ማቅረብ።
የመኖሪያ ቤት እድሳት፡ ለአቅመ ደካማ አረጋውያን እና ወገኖች የመኖሪያ ቤት ጣሪያ እና ግድግዳ ጥገና ማካሄድ።
የስፖርት ውድድሮች፡ ወጣቶችን ከአሉታዊ ተጽዕኖዎች ለመጠበቅ እና ወንድማማችነትን ለማጠናከር የሚረዱ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች።

ካውንስሉ በሁሉም የከተማዋ ክፍለ ከተሞች በሚከናወኑት በእነዚህ ሁለገብ ሥራዎች ማህበረሰቡን የሚበጅ ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል እምነቱን ገልጿል።
እነዚህን በጎ አድራጎቶች እውን ለማድረግም የመንግስት ተቋማት፣ የግል ድርጅቶች፣ ባለሃብቶች፣ የሃይማኖት ተቋማት እና ማንኛውም በጎ አሳቢ ዜጋ ከካውንስሉ ጎን በመቆም የንቅናቄው አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርቧል።

በአዲስ አበባ በቤተል ተቅዋ መስጂድ ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ተካሄደሚያዝያ 25/2018በዛሬውእለት እሁድ ሚያዝያ 25 ቀን በአዲስ አበባ ከተማ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ቤቴል ተቅዋ መስጂድ...
03/05/2026

በአዲስ አበባ

በቤተል ተቅዋ መስጂድ ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ተካሄደ

ሚያዝያ 25/2018

በዛሬውእለት እሁድ ሚያዝያ 25 ቀን በአዲስ አበባ ከተማ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ቤቴል ተቅዋ መስጂድ በአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከ/ም/ቤት ስር የኮልፌ ቀራኒዮ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል አዘጋጅነት ታላቅ የዳእዋ ፕሮግራም ተካሄደ።
በክፍለ ከተማው ወጣቶች ካውንስል የተዘጋጀው ይኸው የዳእዋ ፕሮግራም በዋናነት ተቅዋ በሚል ርዕስ በኡስታዝ ሙሀመድ ሃሰን ማሜ የተደረገ መሳጭ ዳእዋ እና አራያችን ማን ነው ? በሚል ርዕስ በኡስታዝ ካሚል ጣሀ የተዘጋጀ ሁለት ሙሃደራ ያካተተ ሲሆን ፕሮግራሙ በቁርአን ተከፍቶ በአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ፀሀፊ ኡስታዝ አብዱል አዚዝ አወል ንግግር የተጀመረ ፕሮግራም ነበር።
ፕሮግራሙን በርካታ ምእመናን የተሳተፉበት ሲሆን የታዳሚው ጆሮ ሰጥቶ የማዳመጥ ሁኔታው መሰል ፕሮግራሞች መበራከት እንዳለባቸው ጠቋሚ ነው።

በአዲስ አበባ ደረጃ ሲካሄድ የነበረው የቁርአን ውድድር የዑምራ ሽልማት በማበርከት ተጠናቀቀ።ዜና፣መጅሊስ፣የካቲት 23/2018 ዓ.ል. አ.አ.በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተካሂዶ ለዛሬው የፍፃሜ ውድድ...
02/03/2026

በአዲስ አበባ ደረጃ ሲካሄድ የነበረው የቁርአን ውድድር የዑምራ ሽልማት በማበርከት ተጠናቀቀ።

ዜና፣መጅሊስ፣የካቲት 23/2018 ዓ.ል. አ.አ.

በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተካሂዶ ለዛሬው የፍፃሜ ውድድር የደረሰው ይህ የቁርአን ውድድር በሁለቱም ፆታ የተከናወነ ሲሆን ወጣቶችና ታዳጊዎች ከቁርአን ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንደሚያጠናክሩ የማድረግ ዓላማ ይዞ ተከናውኗል።

በመድረኩ ላይ የወጣት ካውንስሉ ምክትል ፕሬዝደንት ወጣት አሚር ሻፊ እንደተናገረው ክፍለ ከተሞች በሁለቱም ፆታ አወዳድረው 20 ዕጩዎችን ለአዲስ አበባ መላካቸውን አብራርቷል።

የውድድሩ ዓላማ ወጣቶችና ታዳጊዎች ከቁርአን ጋር ያለንን ግንኙነት ለማጠናከር የተዘጋጀ መሆኑን የተናገረው ወጣት አሚር በቀጣይ ሰፊ ጊዜ እና ትኩረት ተሰጥቶት የሚሠራ ይሆናል ብሏል።

ለዚህ ተግባር የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል በዋነኛነት ድጋፍ ያደርጋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የአዲስ አበባ መጅሊስ ዋና ፀሐፊ ኡስታዝ ሺሐቡዲን ሼህኑራ ቁርአንን በተለምዶ ማንበብ ብቻ ሳይሆን በዘወትር ሕይወታችን ላይ ተፅዕኖ ማሳደር መቻል አለበት ብለዋል። ዋና ፀሐፊው ኡስታዝ ሺሐቡዲን ቁርአን በሚያናግረን ጊዜ የሚያዘንን ተረድተን በዛው መሠረት መሥራትና ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።

ቁርአንን የምናይበት መንገድ መስተካከል አለበት፤ ሊመራንና ሊያዘን የመጣ መሆኑን አውቀን ትስስራችንን ማጠንከር አለብን ሲሉ ዋና ፀሐፊው ተናግረዋል።

ዋና ፀሐፊው ለሑፋዞች ባስተላለፉት መልዕክት ቁርአንን መሃፈዝ የመጨረሻው ግብ አለመሆኑን በመረዳት ሂፍዛችሁን ዘላቂ ማድረግ እና በውድድር ጊዜም ንያን ማስተካከል ይገባል ብለዋል።

ቁርአን ከአላህ ጋር መነጋገሪያ መንገዳችን በመሆኑ ቁርኝታችንን የበለጠ ማሳደግ፤ ስነ ምግባራችንን ማሳመርና በቁርአኑ ሰርቶ የበለጠ ማስረፅ ተገቢ እንደሆነ አፅንኦት ሰጥተው አሳስበዋል።

የአዲስ አበባ መጅሊስ ምክትል ፕሬዝደንት ሼህ ሙሐመድ ሸሪፍ መጅሊስ ከሚሠራቸው ስራዎች ውስጥ ወጣቶችን ማደራጀት ሲሆን የመደራጀቱን አስፈላጊነትም እያሣየን ነው ብለዋል።

ወጣቶችን ያላሳተፈ ስራ ውጤታማ አይሆንም ያሉት ምክትል ፕሬዝደንቱ ሼህ ሙሐመድ ይህንን ዓይነት የቁርአን ውድድር ማጠናከር እንደሚገባ ገልፀዋል። ለዚህም የተጀመረውን የወጣቶች የአምስት ሚሊየን አባልነት ምዝገባ በትብብር ማጠናቀቅ እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።

ከቁርአን ጋር ያለንን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ታዳጊዎች ላይ መስራት እንደሚያስፈልግ ምክትል ፕሬዝደንቱ አሳስበዋል።

በዛሬው የማጠቃለያ ውድድር በወንዶች፦

1ኛ. ቃሪዕ ኑዓይም ጃቢር ከለሚኩራ ክፍለ ከተማ

2ኛ. ቃሪዕ ኻሊድ አሕመድ ከኮልፌ ክ/ከተማ

3ኛ. ቃሪዕ አብዱልመናን ሙሐመድ ከኮልፌ ክፍለ ከተማ ሆነው ያጠናቀቁ ሲሆን በሴቶች ደግሞ

1ኛ. ኢንቲሳር ጀማል ከልደታ ክፍለ ከተማ

2ኛ. ጦይባ ሙደሲር ከኮልፌ ክፍለ ከተማ እና

3ኛ. ራሕመት አብዱልቃድር ከልደታ ክፍለ ከተማ ሆነው አጠናቀዋል። ይህ ወጣቶችን የበለጠ ከቁርአን ጋር ያላቸውን ቁርኝት ያጠናክራል የተባለው የቁርአን ውድድር ቀጣይነት እንደሚኖረው ተገልጿል።

በአዲስ አበባ ከተማ ክፍለ ከተሞች ሲካሄድ የነበረው ከተማ አቀፍ የቁርአን ውድድር የፍፃሜ ውድድር በዛሬው እለት እየተካሄደ ይገኛል።የወንድ ተወዳዳሪዎች በጦር ሀይሎች ረያን መስጂድና በሴቶች ...
02/03/2026

በአዲስ አበባ ከተማ ክፍለ ከተሞች ሲካሄድ የነበረው ከተማ አቀፍ የቁርአን ውድድር የፍፃሜ ውድድር በዛሬው እለት እየተካሄደ ይገኛል።

የወንድ ተወዳዳሪዎች በጦር ሀይሎች ረያን መስጂድና በሴቶች ደግሞ አ/አበባ መጅሊስ መሰብሰቢያ አዳራሽ እየተካሄደ የሚገኘው የቁርአን ውድድር በውድድሩ በሁለቱም ፆታ 1ኛ የወጡ ተወዳዳሪዎች የዑምራ ሽልማት የሚሸለሙ ሲሆን 2ኛና 3ኛ ለወጡ ደግሞ ለእያንዳንዳቸው የ50ሺ ብር እና የ30ሺ ብር ሽልማት የሚሸለሙ ይሆናል!

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የ ቁርአን ሂፍዝ ውድድር የመጨረሻ የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር በጦር ሀይሎች ረያን መስጂድ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
02/03/2026

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የ ቁርአን ሂፍዝ ውድድር የመጨረሻ የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር በጦር ሀይሎች ረያን መስጂድ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

ከተማ አቀፉ የቁርአን ማጣሪያ ውድድር የመጨረሻ ዕጩዎችን በማሳወቅ ተጠናቀቀ።ዜና፣መጅሊስ፣የካቲት 22/2018 ዓ.ል. አ.አ.በአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የአዶስ አ...
01/03/2026

ከተማ አቀፉ የቁርአን ማጣሪያ ውድድር የመጨረሻ ዕጩዎችን በማሳወቅ ተጠናቀቀ።

ዜና፣መጅሊስ፣የካቲት 22/2018 ዓ.ል. አ.አ.

በአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የአዶስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ያዘጋጀው የረመዳን ወር የቁርአን ውድድር ነገ በታላቅ ድምቀት ይጠናቀቃል። ለዚህ የመጨረሻ ዙር ለመድረስ ከየክፍለ ከተሞቹ ተወክለው የነበሩ ሐፊዞች ዛሬ የመጨረሻውን የማጣሪያ ውድድር አድርገዋል።

ውድድሩ በወንድም በሴትም የተከናወነ ሲሆን በአዲስ አበባ መጅሊስ ትልቁ አዳራሽ የተከናወነውን የወንዶች ውድድር ውጤት ዳኞች ይፋ አድርገዋል።

በዚህም መሠረት በወንዶች፦

1ኛ. ቃሪዕ ኻሊድ አሕመድ ኮልፌ
2ኛ. ኑዓይም ጃቢር ለሚኩራ

3ኛ. አሕመድ ኢማም የካ
4ኛ. አብዱልመናን ሙሐመድ ኮልፌ

5ኛ. ጁነይድ ሰዒድ ጉለሌ
6ኛ. ሱሀይብ ከቢር ቃሊቲ ሆነው አጠናቀዋል።

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ያዘጋጀው የቁርአን ውድድር ነገ በረያን መስጂድ ፍፃሜውን የሚያገኝ ይሆናል።

በነገው መድረክ ላይ ከአንድ እስከ ሶስት የሚወጡ ልዩ ሽልማት የሚበረከትላቸው ይሆናል።

Address

Tor Hailoch
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል Addis Ababa Muslim Youth Council posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share