Mekanisa Addis Kidan Baptist Church

Mekanisa Addis Kidan Baptist Church Mekansia Addis Kidan Baptist Church is dedicated to leading people to faith in Jesus Christ and nurturing them into faithful disciples. Our mission is to guid

We are rooted in biblical teaching and committed to building genuine fellowship among believers.

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን​📅 እሁድ ግንቦት 16, 2018 ዓ.ም📌 እውነተኛና መጽሐፍ ቅዱሳዊ እምነት ምንድነው?  በመጋቢ ፍቃዱ እንዳለ​🔍 የእምነት ምንነትና መሠረት​⁠የክ...
24/05/2026

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን

​📅 እሁድ ግንቦት 16, 2018 ዓ.ም
📌 እውነተኛና መጽሐፍ ቅዱሳዊ እምነት ምንድነው?
በመጋቢ ፍቃዱ እንዳለ

​🔍 የእምነት ምንነትና መሠረት

​⁠የክርስትና መሠረት፦ እምነት የክርስትና ሕይወታችን አንዱ ክፍል ብቻ ሳይሆን፤ ያለ እሱ ክርስትና የማይታሰብበት ዋናው መሠረታችን ነው።
​⁠የእምነታችን መከታ፦ እምነታችን ሙሉ በሙሉ የተገነባው በኢየሱስ ክርስቶስ ማንነትና በሰራው የማዳን ሥራ ላይ ነው።
​የእምነት ምንጭ፦ የእውነተኛ እምነት መገኛና ጀማሪ እራሱ እግዚአብሔር ነው።

​🛡️ የእምነት አባቶች ምሳሌነት

​⁠ጽናት በፈተና፦ የቀደሙ አባቶች በእምነታቸው ምክንያት መከራ፣ ስደት፣ የሀብት መጥፋትና ሞት ቢገጥማቸውም እስከመጨረሻው የጸኑ ነበሩ።
​የጻድቅ መታወቂያ፦ በመከራና በፈተና ውስጥ በእምነቱ በርትቶ የሚቆም ሰው በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ ነው።

​📖 አራቱ የመጽሐፍ ቅዱስ የእምነት ዓይነቶች

​እግዚአብሔር በቃሉ የገለጠልን አራት ዓይነት እምነቶች አሉ፦

​ሀ. የድነት (የደኅንነት) እምነት
​ለ. የጸጋ ስጦታ እምነት
​ሐ. የዕለት ተዕለት የምንኖርበት እምነት
​መ. የሐሰት እምነት

​💡 ማጠቃለያ
​⁠ልክ እንደ እምነት አባቶቻችን፣ በማንኛውም መከራና ማዕበል ውስጥ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ እምነት ሊኖረን ይገባል።
​⁠እውነተኛ እምነት በተግባር ይገለጣል፤ እሱም ታላቁን ተልዕኮ፣ ታላቁን ትእዛዝ እና ታላቁን የርኅራኄ አገልግሎት በመፈጸም ይታያል።

​✨ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ! ✨

​📍 መካኒሳ አዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን
📖 «እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ...።» — 1ኛ ቆሮንቶስ 1:23
​📍 Mekanisa Addis Kidan Baptist Church
📖 “but we preach Christ crucified...” — 1 Corinthians 1:23

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን       እሁድ ግንቦት 09, 2018 ዓ.ም         📌 የማይታየው መሠረት         የማቴዎስ ወንጌል 7 ፥ 24 - 29    እውነተኛ ክ...
17/05/2026

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን

እሁድ ግንቦት 09, 2018 ዓ.ም
📌 የማይታየው መሠረት
የማቴዎስ ወንጌል 7 ፥ 24 - 29


እውነተኛ ክርስትና ከማዕበል የመለየት ሕይወት ሳይሆን፣ በማዕበል ውስጥ የመጽናት ሕይወት ነው! ቤታችን የሚጸናው ውጫዊ ውበቱ ሲያምር ሳይሆን፣ በማይታየው መሠረታችን ጥንካሬ ነው።
🔍 ዋና ዋና ነጥቦች
መስማት እና ማድረግ (ያዕ 1፥22-26)፦ እውነተኛ ደቀ መዝሙር ለመሆን ቃሉን መስማት ብቻ ሳይሆን በተግባር መግለጥ ያስፈልጋል። ከመደነቅ ያለፈ በተግባር የተገለጠ ሕይወት ይፈለግብናል።
ቃሉ የሕይወት መመሪያ እንጂ መዝናኛ አይደለም (ሕዝ 33፥30-33)፦ ቃሉን ሰምተው እንደ መዝናኛ የሚያጣጥሙ ነገር ግን ልባቸው በጥቅምና በምኞት ላይ ያረፈ፣ ቤታቸውን በአሸዋ ላይ እንደሠሩ ሞኞች ናቸው።
የሁለቱ ገንቢዎች ተመሳሳይነትና ልዩነት፦ ሁለቱም ይገነባሉ፣ ቤታቸውም ከውጭ ሲታይ አንድ ዓይነት ሊሆን ይችላል። ልዩነቱ ያለው ግን በቤቱ ውበት ሳይሆን በማይታየው መሠረት ላይ ነው።
አጥልቆ መቆፈር (ሉቃ 6፥48)፦ ጠንካራ መሠረት ብዙ ጉልበት ይሻል። ይህም በጸሎት፣ ቃሉን በማጥናትና ከእግዚአብሔር ጋር በግል በመጓዝ የሚገኝ ጥልቅ ሕይወት ነው።
ማዕበል የመሠረት መርማሪ ነው (ዮሐ 16፥33)፦ ማዕበሉ መምጣቱ አይቀርም፤ በሁሉም ላይ ይመጣል። ፈተና መምጣቱ የእኛ ደካማነት ሳይሆን የምድር ተፈጥሮ ነው። እውነተኛ ገንቢነታችን የሚታወቀው ግን ማዕበሉ ሲመጣ ነው።
"ቃሉን ዛሬ በግል ሕይወቴ ማድረግ ካልጀመርኩ፣ ነገ ማዕበል ሲመጣ የምጠለልበት ቤት አይኖረኝም!

ጌታ ይባርካችሁ!

📍 መካኒሳ አዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን
✨ «1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1:23
እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ...።»

📍 Mekanisa Addis Kidan Baptist Church
✨ “1 Corinthians 1:23
but we preach Christ crucified:.."

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን       እሁድ ግንቦት 02, 2018 ዓ.ምዛሬ የጌታ እራት እና የእግዚአብሔር ቃል አብረን ተካፍለናል!በወንድም ድንበር ንጉስጸሎት!ጸሎት ማለት፡...
10/05/2026

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን

እሁድ ግንቦት 02, 2018 ዓ.ም
ዛሬ የጌታ እራት እና የእግዚአብሔር ቃል አብረን ተካፍለናል!

በወንድም ድንበር ንጉስ

ጸሎት!

ጸሎት ማለት፡-
፨ከእግዚአብሔር ጋር በቀጥታ በነፍስ ግንኑነት ውስጥ መግባት/መነካካትማለት ነው እንጂ ማሰላሰል ወይም በነገሮች መመስጥ ማለት አይደለም፡፡ ስለዚህ ጸሎት፡-
-እግዚአብሔርን መለመን ነው ዘጸ 32፡11
-በእግዚአብሔር ፊት ነፍስን ማፍሰስ ነው 1ሳሙ 1፡15
-ወደ ሰማይ መጮህና ማልቀስ ነው 2ዜና 32፡20
-ወደ እግዚአብሔር መጠጋት፣ መንበርከክ በፊቱ መታየትና መሰንበት መዝ73፡28 እና ኤፌ 3፡14

ጸሎት ምንድን ነው?
-ስጦታ ነው፡፡ ሮሜ 8፡15 ገላ. 4፡6 አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት/የልጁን መንፈስ ተቀበላችሁ
-የመንፈስ ቅዱስ ሥራ/ጩኸት/ ነው፡፡ ሮሜ 8፡26
-ምስጢራዊ ግንኙነት ነው፡፡ የሐና ጸሎት
-በሰማይን መንሸራሸር (ማሰብ፣መሻት) ነው ቆላ 3፡1-3

ከጌታ ትምህርት ስለ ጸሎት ማቴ 6፡5-141. እንዲህ ጸልይ፡- (ቁ.5-8)
፨ አንተ ራስ ጸልይ፡፡ ኢየሱስ ያስተማረው አንተ ራስህ እንድትጸልይ ነው፡፡ “አንተ”፣”የአንተ” 7 ጊዜ ተጠቅሶአል፡፡
፨ አንተ የራስህን ጸልይ፡፡ (እንደ አይሁዳዊና እንደ አሕዛብ ሳይሆን /በኩረጃ ሳይሆን)
፨ ቀርበህ ተጠግተህ ጸልይ፡፡ (በምስጢርና እምነት አድርገው)2. የጸሎትን አድራሻ ዐውቀህ ጸልይ (ቁ.9):-
ትክክለኛው የጸሎት አደራሻ፡-
፨ወደ ሰማያት ነው (የርኅራኄ ስፍራ፣ እውነተኛ ስፍራ፣ ሙሉዑ ስፍራ፣ የፍትህ ስፍራ)
፨ ወደ አባታችን ነው( እውነተኛ አፍቃሪ፣ አስፈላጊውን የሚያውቅ፣ ሙሉ አቅርቦት ያለው)3. እግዚአብሔር በማስቀደም ጸልይ፡-
፨ ቀዳሚው ሲቀድም ነገሮች መሥመር ይይዛሉ፣ ሁሉም ልኩን ይይዛል፣ መረጋጋት ይሆናል፡፡ አውነተኛ ሰላም ይሆናል፡፡
(ቁ 11-13) “የዕለት እንጀራችንን ዛሬ ስጠን፤ እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን፤ከክፉም አድነን እንጂ ወደ ፈተና አታግባን፤”4. ስለ ራሳችሁ
፨ ሕይወታችን ሦስት የጊዜ ሂደቶች የተገለጠ ነው፡፡ (ትላንት ዛሬ እና ነገ)
ለመጸለይ ስንነሳ ማሰብ ያለብን፦

²⁰ እንግዲህ በእኛ ውስጥ እንደሚሠራው እንደ ኀይሉ መጠን፣ ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ በላይ እጅግ አብልጦ ማድረግ ለሚቻለው፣
²¹ በቤተ ክርስቲያን እንዲሁም በክርስቶስ ኢየሱስ፣ በዘመናት ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም ለእርሱ ክብር ይሁን፤ አሜን።
ኤፌሶን 3፥ 20-21

📍 መካኒሳ አዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን
✨ 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1:23
«እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ...።»

📍 Mekanisa Addis Kidan Baptist Church
✨ 1 Corinthians 1:23
"but we preach Christ crucified:.."

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን       እሁድ ሚያዚያ 25, 2018 ዓ.ም              “የወጣቶች ቀን”              በዶ/ር ቦኤዝ ምንዳዬ             ...
03/05/2026

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን

እሁድ ሚያዚያ 25, 2018 ዓ.ም
“የወጣቶች ቀን”

በዶ/ር ቦኤዝ ምንዳዬ

ራዕይ 3፥1-6
ያለ እድፈት እንጠብቅ

የሰርዴስ ታሪካዊ ዳራ
➢ ሰርዴስ በትንሿ እስያ (ባሁኗ ቱርክ) የምትገኝ የጥንቷ ሊዲያ መንግሥት ዋና ከተማ ነበረች
➢ በታላቅ ሀብቷ፣ በወታደራዊ ኃይል መተማመኗ፣ በቅንጦት ኑሮዋ፣ በጨርቃ ጨርቅ ምርቷና በብዙ አማልክት (ቤተ ጣዖት) አምልኮዋ ትታወቅ ነበር
➢ ከተማዋ በከፍተኛ ተራራማ ቦታ ላይ ስለምትገኝ የማይደፈር ምሽግ ተደርጋ ትታይ ነበር

ለሰርዴስ የቀረበ ወቀሳ

- “በሕይወት እንዳለህ ስም አለህ፥ ነገር ግን ሞተሃል ”
- “ ውጫዊ እንቅስቃሴ አለህ፣ ነገር ግን የውስጥ መንፈሳዊ ሕይወት የለህም ”
- “ ንቃት ማጣትህ ወደ መንፈሳዊ መውደቅ አመጣ ”
- “ ሥራህ በአምላኬ ፊት ፍጹም ሆኖ አላገኘሁትም “

ያሁኑ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ያለችበት ሁኔታ
:- ያለች የምትመስል፣ ሃይማኖታዊ መልክ ያላት ነገር ግን የሞተች
2 ጢሞቴዎስ 3፥1-5
"ራሳቸውንና ገንዘብን የሚወድዱ
ትምክሕተኞችና ትዕቢተኞች
ቅድስናና ፍቅር የሌላቸው
ለዕርቅ የማይሸነፉ፣ ሐሜተኞች
ችኵሎችና በከንቱ በትዕቢት የተወጠሩ
ከእግዚአብሔር ይልቅ ተድላን የሚወድዱ"

ያለ እድፈት እንዴት እንጠብቅ?
1.በመንቃት እና የቀረውን በማጽናት
•ራዕይ 3፥2 — “ንቃ፣ሊሞት የተቃረበውን የቀረውን ነገር አጽና”
•ያለንበትን ሁኔታ መፈተሽ
•የጸሎት ሕይወትን፣ቅድስናን መጠበቅ
•ለዘብተኝነትን ማስወገድ

2) የተቀበልነውን እውነት በመጠበቅ
•ራዕይ 3፥3 የተቀበልኸውንና የሰማኸውን አስታውስ፤ ታዘዘውም
•ዳግም ምጽዓቱን በመጠባበቅ በጽድቅ፣ በእውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወት በመኖር
ቲቶ 2፥12-13

3)ንስሃ መግባት
•በክርስቶስ ተስፋ ያላቸው ራሳቸውን ያነጻሉ
1 ዮሐንስ 3፥2–3

ለምን ያለ እድፈት እንጠብቃለን?
ታላቁ ተስፋች
•ከክርስቶስ ጋር ነጭ ልብሳችንን ለብሰን ለመሄድ
•በአብ ፊት ምስክርነትን ለማግኝት

ስለዚህ፦
•በመንፈስ ነቅተናል?
•ልብሳችን ሳናሳድፍ እየጠበቅን ነው?
•ትልቁ ተስፋችንን እየጠበቅን ነው ?

“መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚናገረውን ጆሮ ያለው ይስማ።”

📍 መካኒሳ አዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን
✨ 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1:23
«እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ...።»

📍 Mekanisa Addis Kidan Baptist Church
✨ 1 Corinthians 1:23
"but we preach Christ crucified:.."

30/04/2026

2 ቀን ቀረው

ያለ እድፈት እንጠብቅ!

በመካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን

ልዩ የእሁድ መደበኛ ፕሮግራም በቤተክርስቲያኒቱ ወጣቶች የተዘጋጀ።
እሁድ ሚያዝያ 25 2018 ዓ.ም
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!!!!

በእለቱ
የእግዚአብሔር ቃል
ግጥም
የዝማሬ ግዜ አብረን የምንካፈል ይሆናል።

ሁላችሁም ነጭ ለብሳችሁ እንድትመጡ ስንል በጌታ ፍቅር እናስታውቃለን።

ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ!
📍 መካኒሳ አዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን
✨ 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1:23
«እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ...።»
📍 Mekanisa Addis Kidan Baptist Church
✨ “1 Corinthians 1:23
«but we preach Christ crucified:.."

ያለ እድፈት እንጠብቅ!በመካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን ልዩ የእሁድ መደበኛ ፕሮግራም በቤተክርስቲያኒቱ ወጣቶች የተዘጋጀ።እሁድ ሚያዝያ 25 2018 ዓ.ምሁላችሁም ተጋብዛችኋል!!...
27/04/2026

ያለ እድፈት እንጠብቅ!

በመካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን
ልዩ የእሁድ መደበኛ ፕሮግራም በቤተክርስቲያኒቱ ወጣቶች የተዘጋጀ።

እሁድ ሚያዝያ 25 2018 ዓ.ም

ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!!!!

በእለቱ

የእግዚአብሔር ቃል
ግጥም
የዝማሬ ግዜ አብረን የምንካፈል ይሆናል።

ሁላችሁም ነጭ ለብሳችሁ እንድትመጡ ስንል በጌታ ፍቅር እናስታውቃለን።

ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ!
📍 መካኒሳ አዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን
✨ 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1:23
«እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ...።»
📍 Mekanisa Addis Kidan Baptist Church
✨ “1 Corinthians 1:23
«but we preach Christ crucified:.."

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን       እሁድ ሚያዚያ 18, 2018 ዓ.ም    የ1ኛ ጴጥሮስ ተከታታይ ትምህርት              ማጠቃለያ     በአገልጋይ ሰለሞን ሀ/የሱ...
26/04/2026

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን

እሁድ ሚያዚያ 18, 2018 ዓ.ም

የ1ኛ ጴጥሮስ ተከታታይ ትምህርት ማጠቃለያ
በአገልጋይ ሰለሞን ሀ/የሱስ

1ጴጥሮስ 5፥ 12-14
ይህ እውነተኛ የእግዚአብሔር ጸጋ ነው!

፦ ጸጋ የምንለው ለማይገባው ሰው፣ የማይገባውን ቸርነት በማድረግ የሚሰጥ፤ በሰጪው ማንነትና መልካም ፈቃድ ላይ ብቻ የተመሠረተ ነጻ ስጦታ ማለት ነው!

በአንደኛ ጴጥሮስ ትምህርታችን የተመለከትናቸው እግዚአብሔር ለእኛ የሰጣቸው ውድ ስጦታዎች፦

1. በእግዚአብሔር የተሠራ ድንቅ የማዳን ሥራ፤ ይህ የእግዚአብሔር እውነተኛ ጸጋ ነው!
2. በመንፈስ ቅዱስ የቅድስናን ሕይወት ለመኖር ተጠርተናል፤ ይህ የእግዚአብሔር እውነተኛ ጸጋ ነው!
3. ለሕያው ተስፋ የተመረጥን ነን፤ ይህ የእግዚአብሔር እውነተኛ ጸጋ ነው!
4. በኑሯችን ሁሉ ክብርን ለእግዚአብሔር ለማምጣት ተጠርተናል፤ ይህ የእግዚአብሔር እውነተኛ ጸጋ ነው!

ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ!

📍 መካኒሳ አዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን
✨ «1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1:23
እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ...።»

📍 Mekanisa Addis Kidan Baptist Church
✨ “1 Corinthians 1:23
but we preach Christ crucified:.."

26/04/2026

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተ-ክርስቲያን እሁድ ሚያዚያ 18/2018 ዓ.ም

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን       እሁድ ሚያዚያ 11, 2018 ዓ.ምየ1ኛ ጴጥሮስ ተከታታይ ትምህርት     በመጋቢ ምንዳዬ ሀይሌ            1ጴጥሮስ 5፥1-11፨ ...
19/04/2026

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን

እሁድ ሚያዚያ 11, 2018 ዓ.ም

የ1ኛ ጴጥሮስ ተከታታይ ትምህርት
በመጋቢ ምንዳዬ ሀይሌ

1ጴጥሮስ 5፥1-11
፨ ሐዋርያው ጴጥሮስ በዚህ ክፍለ ምንባብ ላይ ፣ ምክርን የሚሰጠው፦
- ለሽማግሌዎች
- ለጎልማሶች
- ለአጠቃላይ ማኀበሩ
፨ ሐዋርያው ጴጥሮስ ምክሩን ከመጀመሩ በፊት፣ በአገልግሎት ያገኘውን ልምድ ያካፍላቸዋል። እራሱንም የሚገልጥባቸው ሦስት መንገዶች አሉ፦
ሀ. ሽማግሌው
ለ. የክርስቶስ መከራ ምስክር
ሐ. ወደፊት የሚገለጠው ክብር ተካፋይ
፨ ሐዋርያው በዚህ ክፍል ላይ የሚያስተላልፋቸው ምክሮች፦
1. ለመሪዎች የተሰጠ ምክር (ቁ.2-4)
፨ መሪዎች የእግዚአብሔርን መንጋ በአግባቡ እንዲመሩ ይመክራቸዋል፤ ይኽንንም ለማድረግ፦
# መንጋውን በመጠበቅ መምራት
# ሕዝቡን በፈቃደኝነትና ጽኑ ፍላጎት መምራት
# በመልካም ምሳሌ መምራት
ሐዋ.20፥28
፨ የእግዚአብሔርን ሕዝብ የማንመራባቸው መንገዶች፦
- በማስገደድ
- ለጥቅም በሠስገብገብ
- በላያቸው በመሰልጠን
ሕዝ.34፥1-16
፨ በትክክል ከመራችሁ የእረኞች አለቃ፣ እርሱም ክርስቶስ በሚገለጥበት ጊዜ ሽልማትን ትቀበላላችሁ!
2. ጎልማሶች ለሽማግሌዎች እንዲገዙ የተሰጠ ምክር (ቁ.5-7)
፨ መሪዎችን እንደ መሪ መቀበልና በትሕትና ራስን ለእነረሱ ማስገዛት ያስፈልጋል።
፨ ጎልማሶች ራሳቸውን ለእግዚአብሔር እንዲያስገዙ፣ ራሳቸውን የሚገዙና ንቁ እንዲሆኑ ይመክራቸዋል፤ ይኽንንም ማድረግ ከእኛ ይጠበቅብናል።
3. ሁላችሁም በእምነት ጸንታችሁ ቁሙ (ቁ.9-11)
፨ ጌታ ሊመጣ በደጅ ነው፣ ስለዚህም በእምነታችን ጸንተን መቆም ይጠበቅብናል።
፨ የዲያብሎስን ውጊያ ልናሸንፍ የምንችለው በእምነታቸን ጸንተን በመቆም ነው።
፨ በመከራ ውስጥ ጸንተን እንድንቆም የሚያደርግና የሚያበረታ አምላክ አለን፣ ስለዚህም ጸንተን እንቁም!
ከዚህ ምን እንማር?
1. የእግዚአብሔርን ሕዝብ መምራት ተጠያቂነት ደግሞም ሽልማት እንዳለው!
2. ታላቅ ተስፋ እንዳለን በማወቅ በመከራ ውስጥ መጽናት እንዳለብን!

ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ!

📍 መካኒሳ አዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን
✨ «1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1:23
እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ...።»

📍 Mekanisa Addis Kidan Baptist Church
✨ “1 Corinthians 1:23
but we preach Christ crucified:.."

በኢትዮጲያ ዐዲስ ኪዳን መጥመቃዊት ቤተ ክርስቲያን የመካኒሳ አጥቢያ የሕፃናት ልዩ የክርስቶስ ትንሣኤ መታሰቢያ መርሃ ግብር፤ ቅዳሜ ሚያዝያ 3/2018 ዓ.ም. የተካሄደ ሲሆን፣ በእለቱ፦፨ የዝ...
14/04/2026

በኢትዮጲያ ዐዲስ ኪዳን መጥመቃዊት ቤተ ክርስቲያን የመካኒሳ አጥቢያ የሕፃናት ልዩ የክርስቶስ ትንሣኤ መታሰቢያ መርሃ ግብር፤ ቅዳሜ ሚያዝያ 3/2018 ዓ.ም. የተካሄደ ሲሆን፣ በእለቱ፦
፨ የዝማሬ
፨ የእግዚአብሔር ቃል
፨ የጥያቄና መልስ
፨ የኀብረትና የጨዋታ ጊዜያት ተከናውነዋል!

መልካምን ጊዜ የሰጠን እግዚአብሔር ይመስገን!

ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ!

📍 መካኒሳ አዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን
✨ 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1:23
«እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ...።»

📍 Mekanisa Addis Kidan Baptist Church
✨ “1 Corinthians 1:23
but we preach Christ crucified:.."

Address

Ethiopia, Kore Square 200m Down
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30
Saturday 08:30 - 17:30
Sunday 08:30 - 17:30

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mekanisa Addis Kidan Baptist Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category