Mekanisa Addis Kidan Baptist Church

Mekanisa Addis Kidan Baptist Church Mekansia Addis Kidan Baptist Church is dedicated to leading people to faith in Jesus Christ and nurturing them into faithful disciples.

We are rooted in biblical teaching and committed to building genuine fellowship among believers.

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን​እሁድ ነሃሴ 17, 2018 ዓ.ምበወንደም የኔነህ ታደሰየዕለቱ መልእክት አጭር ማጠቃለያ፦ የብሱ ይገለጥ!📖 የዕለቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል፦ «እግዚ...
23/08/2026

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን

እሁድ ነሃሴ 17, 2018 ዓ.ም

በወንደም የኔነህ ታደሰ

የዕለቱ መልእክት አጭር ማጠቃለያ፦ የብሱ ይገለጥ!

📖 የዕለቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል፦

«እግዚአብሔርም፦ ከሰማይ በታች ያለው ውኃ በአንድ ስፍራ ይሰብሰብ፥ የብሱም ይገለጥ አለ፤ እንዲሁም ሆነ።» — ዘፍጥረት 1፥9

✨ ከመልእክቱ የተወሰዱ ዋና ዋና ነጥቦች፦

1. እግዚአብሔር የተዘበራረቀውን ሕይወት ያስተካክላል
በመጀመሪያ ምድር ባዶና ጨለማ ነበረች፤ ነገር ግን በእግዚአብሔር ቃል ሁኔታዎች ተቀየሩ። እግዚአብሔር ሲሠራ ያልተደራጀው ይደራጃል፣ የጨለመው ይበራል፣ የተዘጋውም በር ይከፈታል።

2. የተሸፈነው ይገለጣል
የብሱ ከውኃ በታች ሆኖ ለሰው ዓይን ባይታይም እግዚአብሔር ግን ያውቀው ነበር። ያልታየ ማለት የሌለ ማለት አይደለም፤ ጊዜው ሲደርስ እግዚአብሔር በሕይወታችን የተሸፈነውን ሕልም፣ አቅም እና ዕቅድ “ይገለጥ” ብሎ ያወጣዋል።

3. ከመገለጥ በኋላ ፍርያማነት ይከተላል
እግዚአብሔር የተሸፈነውን ነገር ሲገልጥልን እንድንደነቅ ብቻ ሳይሆን ፍሬ እንድናፈራ ነው (ዘፍጥረት 1፥11)።

💡 የተሸፈነው እንዲገለጥና ፍርያማ እንድንሆን ምን እናድርግ?

* ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ወዳጅ እንሁን፦ ቃሉ ሕይወታችንን ይለውጣል፣ መንገዳችንን ያበራል፣ ሚስጥርን ይገልጣል፣ ባዶነታችንንም ይሞላል።

* የጸሎት ሕይወታችንን እናሳድግ፦ ጸሎት ኃይል አለው፤ የእግዚአብሔርን ድምፅ የምንሰማበትና በመንፈስ ቅዱስ የምንሞላበት መንገድ ነው።

የቡራኬ ቃል፦

በግል፣ በቤተሰብ፣ በቤተ ክርስቲያን፣ በከተማችንና በአገራችን የተዘጋው ይከፈት፤ የጠፋው ተስፋ ይታደስ፤ የተዘበራረቀው ሕይወት ሥርዓት ይያዝ፤ የተዘራው ዘር ፍሬ ያፍራ፤ የእግዚአብሔር ዓላማ በሕይወታችን ይገለጥ!

እግዚአብሔር ይባርካችሁ!

ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ!

የጉግል ማፕ አድራሻ (Google Maps)፦ https://maps.app.goo.gl/sFcqHewKLUofJDr89?g_st=ac

መካኒሳ አዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን
«እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ...።» — 1ኛ ቆሮንቶስ 1:23

Mekanisa Addis Kidan Baptist Church
“but we preach Christ crucified...” — 1 Corinthians 1:23

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን​       እሁድ ነሃሴ 10, 2018 ዓ.ም          በአገልጋይ ጸሃይ አየነው   የዕለቱ መልእክት አጭር ማጠቃለያ፦               ...
16/08/2026

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን

እሁድ ነሃሴ 10, 2018 ዓ.ም

በአገልጋይ ጸሃይ አየነው

የዕለቱ መልእክት አጭር ማጠቃለያ፦

የሚበልጠው በዚህ አለ!

📖 የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል፦ የሉቃስ ወንጌል 11 ÷ 14-32

በዚህ ትምህርት ውስጥ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የሚከተሉ ሰዎችን በሦስት ከፍለን እናያለን፦

1️⃣ ነገሩን በማስተዋል የሚመረምሩ፦ ዲዳውን ጋኔን ሲያወጣ አይተው የሚደነቁ።

2️⃣ ተቃዋሚዎች፦ የተገለጠውን መለኮታዊ ኃይል ሌላ ትርጉም በመስጠት "በብዔል ዜቡል በአጋንንት አለቃ አጋንንትን ያስወጣል" የሚሉ።

3️⃣ ምልክት ፈላጊዎች፦ ጌታን ሲፈትኑት ከሰማይ ታምራዊ ምልክት የሚፈልጉ።

ጌታችን ኢየሱስ ግን ለዚህ ትውልድ ከነብዩ ከዮናስ ምልክት በቀር ሌላ ምልክት እንደማይሰጠው መለሰ። ዮናስ ለነነዌ ሰዎች የጽድቅ ምልክት እንደሆነ፣ የሰው ልጅ (ኢየሱስ) ደግሞ ለትውልዱ የእግዚአብሔር ምህረት ምልክት ነው!
ንግሥተ አዜብ የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለች፤ እነሆም ከሰሎሞን የሚበልጥ ከዚህ አለ!

🌟 ማጠቃለያ መልእክት፦

ዛሬም በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ የተለያየ አመለካከት ይዘው ጌታን የሚከተሉ ሰዎች ይታያሉ።

ነገር ግን የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ይለናል፦
👉 ከዮናስ የሚበልጠው የጽድቅ ምልክት በዚህ አለ — ወደ እርሱ ተመለሱ!

👉 ከሰሎሞን የሚበልጥ፣ የትውልድን እንቆቅልሽ የሚፈታ የጥበብ ምንጭ በዚህ አለ — ወደ እርሱ ቅረቡ!

ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ!

የጉግል ማፕ አድራሻ (Google Maps)፦ https://maps.app.goo.gl/sFcqHewKLUofJDr89?g_st=ac

መካኒሳ አዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን
«እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ...።» — 1ኛ ቆሮንቶስ 1:23

Mekanisa Addis Kidan Baptist Church
“but we preach Christ crucified...” — 1 Corinthians 1:23

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን​📅 እሁድ ነሀሴ  3/ 2018 ዓ.ም                 በእህት ይደነቁ ተፈራ📖። መጀመሪያይቱ የሐዋሪያው ዮሐንስ መልእክት1. አብ እንዴት ...
09/08/2026

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን

📅 እሁድ ነሀሴ 3/ 2018 ዓ.ም

በእህት ይደነቁ ተፈራ
📖። መጀመሪያይቱ የሐዋሪያው ዮሐንስ መልእክት
1. አብ እንዴት ያለውን ፍቅር እንደ ሰጠን እዩ!
* ዋና ጥቅስ፦ "እዩ! የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን ልንጠራ አብ እንዴት ያለውን ፍቅር እንደ ሰጠን እዩ፥ እንዲሁም ነን።" — 1ዮሐ 3፥1
2. ፍቅሩ እንዴት እንደ ተገለጠ እዩ!
* ዋና ጥቅሶች፦
* "በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፥ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና።" — 1ዮሐ 4፥9
* "ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም።" — 1ዮሐ 4፥10
* "እርሱ ስለ እኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቶአልና በዚህ ፍቅርን አውቀናል" — 1ዮሐ 3፥16
3. የተወደዳችሁበትን ፍቅር እያያችሁ ታዘዙት
* ዋና ጥቅሶች፦
* "እዛዛቱንም ብንጠብቅ በዚህ እንዳወቅነው እናውቃለን።" — 1ዮሐ 2፥3
* "ትእዛዚቱም ይህች ናት፥ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናምን ዘንድ፥ ትእዛዝንም እንደ ሰጠን እርስ በርሳችን እንዋደድ ዘንድ ።" — 1ዮሐ 3፥23
* "ወዳጆች ሆይ፥ እግዚአብሔር እንዲህ አድርጎ ከወደደን እኛ ደግሞ እርስ በርሳችን ልንዋደድ ይገባናል።" — 1ዮሐ 4፥11
4. ለመታዘዝ የተገለጠውን ፍቅር እዩ
* ዋና ጥቅሶች፦
* "በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል።" — 1ዮሐ 4፥16
* "እግዚአብሔርንም ማንም ከቶ አላየውም፤ እርስ በርሳችን ብንዋደድ እግዚአብሔር በእኛ ይኖራል ፍቅሩም በእኛ ፍጹም ሆኖአል።" — 1ዮሐ 4፥12
* "ትእዛዙንም የምንጠብቅና በፊቱ ደስ የሚያሰኘውን የምናደርግ ስለሆንን የምንለምነውን ሁሉ ከእርሱ እናገኛለን።" — 1ዮሐ 3፥22

✨ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ! ✨

📍 መካኒሳ አዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን
✨ «1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1:23
እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ...።»

📍 Mekanisa Addis Kidan Baptist Church
✨ “1 Corinthians 1:23
but we preach Christ crucified:.."

https://maps.app.goo.gl/PQx4CyvMJfjPxb8z6?g_st=com.google.maps.preview.copy

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን​         እሁድ ሐምሌ 26 , 2018 ዓ.ም             በመጋቢ ምንዳዬ ሀይሌ​የዕለቱ መልእክት አጭር ማጠቃለያ፦ "ኑ የፈረሰው ቅጥር...
02/08/2026

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን

እሁድ ሐምሌ 26 , 2018 ዓ.ም
በመጋቢ ምንዳዬ ሀይሌ
​የዕለቱ መልእክት አጭር ማጠቃለያ፦ "ኑ የፈረሰው ቅጥር እንሥራ!"

​በሕይወታችን እንደ ግለሰብ፣ ማኅበረሰብ፣ ቤተ ክርስቲያን ወይም ሀገር የፈረሱብንና መልሰው ሊገነቡ የሚገባቸው አያሌ ነገሮች አሉ፤ የዕለቱ ትምህርት የነህሚያን ታሪካዊ ዳራና የኢየሩሳሌም ቅጥር መልሶ መገንባትን መሠረት በማድረግ ለተግባራዊ ሕይወታችን የሚሆን ታላቅ መንፈሳዊ ጥሪን ያቀረበ ነው::
​📌 የመልእክቱ 3 ዋና ዋና አበይት ነጥቦች፦
​1️⃣ ሰምቶ የተገበረው ራዕይ (ነህሚያ 1-3)
• የልብ ስብራትና ጸሎት፦ ነህሚያ በሱሳ ግንብ ሳለ ስለ ኢየሩሳሌም የፈረሱ ቅጥሮችና የሕዝቡ ውርደት ሰማ። ችግሩን እንደሰማ አልቀሰ፣ ጾመ፣ በጸሎትም ወደ እግዚአብሔር ቀረበ።
• ራዕይን ማካፈል፦ በጸሎት በንጉሡ ፊት ተቀባይነት አግኝቶ ወደ ኢየሩሳሌም ከተጓዘ በኋላ፣ ራዕዩን ለሕዝቡ በማካፈል «እንነሣና እንሥራ» ብለው በጋራ እንዲነሡ አደረገ።
• ሕዝባዊ ተሳትፎ፦ ሊቃነ ካህናት፣ ወርቅ አንጥረኞች፣ ነጋዴዎችና አባወራዎች በሙሉ እጃቸውን ለበጎ ሥራ አበረቱ።
​2️⃣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና አፈታታቸው (ነህሚያ 4-6)
• የውጭ ተግዳሮት፦ በጠላቶች በኩል ንቀት፣ ሽብር፣ የስም ማጥፋት ዘመቻና የሐሰት ትንቢት ገጥሞት ነበር። ነህሚያ ግን ወደ እግዚአብሔር በመጸለይ፣ ሕዝቡን በማበረታታት፣ መሣሪያ ታጥቆ በመጠበቅና በመንፈሳዊ መለየት አሸነፈው።
• የውስጥ ተግዳሮት፦ የምግብ እጥረት፣ የዐራጣ ብድርና የባርነት ችግር በሕዝቡ መካከል ተከሰተ። ነህሚያ መኮንኖችን በመገሰጽና ፍትሕን በማስፈን ችግሩን ፈታው።
• ውጤት፦ የቅጥሩ ሥራ በ52 ቀን ውስጥ ተጠናቀቀ፤ ጠላቶችም ሥራው በእግዚአብሔር እንደ ተደረገ አወቁ።
​3️⃣ መንፈሳዊ ተሃድሶ (ነህሚያ 8-10, 13)
• የቃል ተሃድሶ፦ የሕጉ ቃል ተነቦና ተበራርቶ ለሕዝቡ ተብራራ።
• ንስሐና ቃል ኪዳን፦ ሕዝቡ ኃጢአቱን በመናዘዝ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ለመጠበቅ በርግማንና በመሐላ ቃል ገባ።
• ተግባራዊ ማስተካከያ፦ የሰንበት ቀን አከባበርና የሌዋውያን አገልግሎት ወደ ቦታው ተመለሰ።

​💡 ከመልእክቱ የምንማራቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
​• ጸሎት፦ ሥራንና አገልግሎትን ውጤታማ ለማድረግ የመጀመሪያውና ዋነኛው ቁልፍ ነው።
• ጽናት፦ በየትኛውም ተግዳሮት ውስጥ የእግዚአብሔርን ሥራ በማከናወን ጸንቶ መቆም ይገባናል።
• ቁርጠኝነት፦ ከእግዚአብሔር የተቀበልነውን ጥሪ በሁኔታዎች ሳንበገር ማስቀጠል አለብን።
• መንፈሳዊ ተሃድሶ፦ ለመታደስ የወደቅንበትን ቦታ አውቆ መስተካከል ቀዳሚ ጉዳይ ነው።

​ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ!
📍 የጉግል ማፕ አድራሻ (Google Maps)፦ https://maps.app.goo.gl/sFcqHewKLUofJDr89?g_st=ac

መካኒሳ አዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን
«እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ...።» — 1ኛ ቆሮንቶስ 1:23

Mekanisa Addis Kidan Baptist Church
“but we preach Christ crucified...” — 1 Corinthians 1:23

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን​         እሁድ ሐምሌ 19 , 2018 ዓ.ም          በአገልጋይ ሰለሞን ሃ/ኢየሱስየዕለቱ መልእክት አጭር ማጠቃለያ፦ "ከእነዚኽ ሽሹ!"...
26/07/2026

መካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን

እሁድ ሐምሌ 19 , 2018 ዓ.ም
በአገልጋይ ሰለሞን ሃ/ኢየሱስ

የዕለቱ መልእክት አጭር ማጠቃለያ፦ "ከእነዚኽ ሽሹ!" (2ጴጥሮስ 1፥16-2፥22 እና ይሁዳ 1-25)

የእግዚአብሔር እውነተኛ ቃል ልባችንን የሚያበራ መብራት ነው፤ በመጨረሻው ዘመን ከሚመጡ አታላይና ሐሰተኛ ትምህርቶች ራሳችንን በመጠበቅ በእምነታችን እንጽና!

➡️ እውነተኛው የእግዚአብሔር ቃል በሰው ፈቃድ የመጣ ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ቅዱሳን ሰዎች ተናገሩት።
➡️ ሐሰተኞች አስተማሪዎች በእግዚአብሔር ሕዝብ መካከል አሹልከው ገብተው ሰዎችን የሚያስቱበት ጊዜ ስላለ በንቅናት ልንጠነቀቅ ይገባል።
➡️ የሐሰተኛ አስተማሪዎች ዋነኛ ዓላማ በራሳቸው ፍላጎትና በገንዘብ መሻት ተነሳስተው የእውነትን መንገድ ማጣመም ነው።
➡️ እግዚአብሔር በሐሰተኛ አስተማሪዎችና በእውነት መንገድ ላይ በሚያምጹት ላይ ፍጹም ፍርዱን ያመጣባቸዋል።
➡️ በቅዱስ እምነታችን ላይ ራሳችንን ለማነጽና ለማጽናት ሁልጊዜ በመንፈስ ቅዱስ መጸለይ ይኖርብናል።
➡️ በእምነታቸው የተጠራጠሩትንና ተስፋ የቆረጡትን በምሕረትና በፍቅር ደግፈን ልናወጣቸው ይገባል።
➡️ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳንወድቅ ሊጠብቀንና በክብሩ ፊት ያለ ነቀፋ ሊያቆመን የሚችል የታመነ አምላክ ነው።

ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ!
📍 የጉግል ማፕ አድራሻ (Google Maps)፦ https://maps.app.goo.gl/sFcqHewKLUofJDr89?g_st=ac

መካኒሳ አዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን
«እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ...።» — 1ኛ ቆሮንቶስ 1:23

Mekanisa Addis Kidan Baptist Church
“but we preach Christ crucified...” — 1 Corinthians 1:23

በመካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተ ክርስቲያን በዛሬው እለት የወንጌል ሥርጭት ሥልጠና፣ በቤተ ክርስቲያን ለሚገኙ አባላትና አገልጋዮች ተከናውኗል።      ✨ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ! ✨ 📍...
25/07/2026

በመካኒሳ ዐዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተ ክርስቲያን በዛሬው እለት የወንጌል ሥርጭት ሥልጠና፣ በቤተ ክርስቲያን ለሚገኙ አባላትና አገልጋዮች ተከናውኗል።

✨ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ! ✨

📍 መካኒሳ አዲስ ኪዳን መጥምቃዊት ቤተክርስቲያን
✨ «1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1:23
እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ...።»

📍 Mekanisa Addis Kidan Baptist Church
✨ “1 Corinthians 1:23
but we preach Christ crucified:.."

https://maps.app.goo.gl/PQx4CyvMJfjPxb8z6?g_st=com.google.maps.preview.copy

22/07/2026

መዝሙር 23:6
"በሕይወቴ ዘመን ሁሉ፣ በጎነትና ምሕረት በርግጥ ይከተሉኛል፤ እኔም በእግዚአብሔር ቤት፣ ለዘላለም እኖራለሁ።"

Address

Ethiopia, Kore Square 200m Down
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30
Saturday 08:30 - 17:30
Sunday 08:30 - 17:30

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mekanisa Addis Kidan Baptist Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category