12/03/2022
#ምኩራብ
-> የዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሣምንት ምኩራብ ይባላል።
-> ምኵራብ ፦ የአይሁድ መቅደስ ቤተ ጸሎት ታላቅ አዳራሽ ነበር።
-> በዚህ ሣምንት ጌታ በመዋዕለ ስብከቱ፡ በምኩራብ ገብቶ ማስተማሩ ይነገራል (ማቴ 4፥23 ማር 1÷21 ሉቃ 4÷15)
-> ክርስቶስ ለማስተማር በገባ ጊዜ አይሁድ ቤተ ጸሎቱን እንደ ስያሜው ሳይሆን መሸጫና መለዋወጫ መገበያያ አድርገውት ስለአገኛቸው ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ መሸጫ መለዋወጫ አደረጋችሁት ብሎ ሰዎችንና እንስሳትን በጅራፍ እየገረፈ ገበታቸውን እየገለበጠ አባሮአቸዋል ስለዚህ ይህ ሳምንት ለታሪኩ መታሰቢያ ምኩራብ ተብሉአል (ማቴ 21፥12-13
ማር 11፥15-18:: ሉቃ 19÷45-47 ዮሐ 2÷14-16)
-> ቅዱሳን ሐዋርያትም እንደ ጌታችን ለጸሎትና
ለትምህርተ ወንጌል ወደ ምኩራብ ይወጡ ነበር፡፡ የሐዋ 3፥1። የሐዋ.13፥5:: የሐዋ.14፥1:: የሐዋ.17-1:: የሐዋ.10-17:: የሐዋ.18-4:: የሐዋ.19፥8)
-> ምኩራብ ፦ ለአምልኮና ለትምህርት ለሕብረተሰቡም ጠቅሞአል
-> ምኩራብ በአለቆች ይመራ ነበር (ማር 5፥ 22፡፡ የሐዋ 3÷14-15:: የሐዋ18፥8)
-> በየሳምንቱ ሕዝቡ ሁሉ በምኩራብ ይሰበሰቡ ነበር፡፡ (ሉቃ 4÷16፡፡ የሐዋ.15 21)፡፡
-> ወንዶችና ሴቶች ለየብቻቸው ይቀመጡ ነበር።
->የእግዚአብሔር ቃል ሲነበብ አንባቢው እንዲሰማ በተዘጋጀው ከፍተኛ ቦታ ይቆም ነበር::
የክብር ወንበሮች ከዚህ ቦታ ፊት ለፊት ነበሩ (ማቴ 23÷6:: ሉቃ 4፥20)
➕ መዝሙር ዘምኩራብ :-
ቦአ ኢየሱስ ምኩራቦሙ ለአይሁድ
➕ ምንባባት ምኩራብ ዘቅዳሴ :-
- ቆላ 2÷16-ፍም፡፡
- ያዕቆብ 2፥14-ፍም::
- ግ.ሐዋ 10፥1-9
➕ ምስባክ ፦
" እስመ ቅናተ ቤትከ በልዐኒ ትዕይርቶሙ ለእለ ይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ " (መዝ 68፥9)
➕ ወንጌል ዮሐ 2፥12-ፍም
➕ ቅዳሴ ዘእግዚእነ (ነአኩተከ)