11/10/2025
የኢ/እ/ጉ/ጠ/ም/ቤት የምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ ለምርጫ 2017
ማጠቃለያ ጋዜጣዊ መግለጫ
የኢትዮጵያ ሙስሊሞች በረዥም ጊዜ የትውልድ ቅብብሎሽ የመብት ትግል ውስጥ በየሂደቱየከፈላቸው የህይወት፣ የደም፣የሞራል፣ የማንነት ዋጋ በዓለም የሙስሊም ዑማ ታሪክ ውስጥበወርቅ ተጽፎ ክስተቶች ሁሉ በትውልድ ተመዝግቦ ከአንድ ወደ ሌላኛው እየተቀባበለ እነሆ
ዛሬ ያለፈውን ታሪክ ብለን የምንዘክርበት ወቅት ላይ መድረሳችን የአላህ ጸጋ ነውናአልሃምዱሊላህ ረቢልዓለሚን፡፡
የህዝብ ሙስሊሙ ሁለንተናዊ ጥያቄዎች ጥቅል መልስ የሆነው የተቋማዊ አሠራርና ራሱተቋሙ በሙሉ መዋቅራዊ ማንነቱ መኖር ላይ የተመረኮዘ በመሆኑ በየጊዜው ይነሱ ከነበሩ
ጥያቄዎች ውስጥ አብዛኛው በኢ/እ/ጉ/ጠ/ጉባኤ (መጅሊስ) ህጋዊ ተቋም መሆንና በህጋዊ ህዝባዊተሳትፎ እና ይሁንታ የተመረጡ አመራሮች ይኑረን የሚለው የመብት ጥያቄ ምላሽ የሆነውበ2017 የኢ/እ/ጉ/ጠ/ጉባኤ ሀገራዊ ምርጫ ማረጋገጡ ሌላኛው እምርታ ሲሆን ከፍ ሲል ተቋሙራሱ እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ተቋማት በአዋጅ ቁጥር 1207/12 ህጋዊ ዕውቅና ማግኘቱድርብ ድልና ከፍታ ሆኖ በታሪክ ተመዝግቧል፡፡
በሌላ በኩል የ2017 የመጅሊስ ሀገራዊ ምርጫን ለማካሄድ ትክክለኛ ውሳኔ ጠንካራ አቋምየያዘው የወቅቱ የመጅሊስ አመራር በተለይም የክቡር ዶ/ር ሸ/ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ቁርጠኛአመራር በዚህ ሂደት ውስጥ ሌላኛው ባለታሪክ ሆኖ ይዘከራል፡፡
ምርጫውን ለማስፈጸም የተቋቋመው አጠቃላይ ከፌደራል እስከ መስጂድ ድረስ በየክልሉ እናከተማዎች የተዋቀረው ተዓምራዊ ተግባርን የፈጸመና የዲን እና የዑማ ተቋማዊ ተልዕኮን
በአንጸባራቂ ድል ያገባደደው ስብስብ ያለቀ አፈጻጸም እና ከግቡ ሲያመነታ ችግሮችንናመሰናክሎችን ተቋቁሞና በጥበብ አልፎ አይሆንም አይቻልም የተባለን ታላቅ ጉዳይ በአላህፍቃድ ቀጥሎ በዓላማ ጽናት ሰርቶ አሳክቶታል በውጤቱ መላው የኢትዮጵያ ሙስሊም ከጫፍጫፍ ከባህር ማዶ ከአድማስ ባሻገር ጭምር አሳትፎ በድል አጠናቋል፡፡ ለዚህም ታላቅ ክብርናምስጋና ለልዑል አላህ ይሁን፡፡
ዳግም አልሃምዱሊላህ ረቢልዓለሚን ብለናል!!!ከመስጂዶች የጀመርነውን ምርጫ በመላ ሀገሪቱ የህዝበ ሙስሊሙ ጥያቄ የነበረው “ምርጫችንበመስጂዳችን” የሚለውን ህዝባዊ ድምጽ እውን ሆኖ ለመላ ሀገሪቱ ባሉ መስጂዶችእንደተጀመረ ሁሉ መዚጊያውም ታሪካዊና የኢትዮጵያ ሙስሊም አርማ በሆነው ታላቁ አንዋርመስጂድ በታላቅ ድምቀትና ህዝባዊ ተሳትፎ ዲናዊ ሥነ ሥርዓትና ሥነ-ምግባር ተጠናቋል፡፡
ምርጫውን ከሌላ ጊዜ እና የምርጫ ዓይነቶች ልዩ ከሚያደርጉት ጉዳዮች መሀከል፡-
➢ ከአሁን በፊት ስለ መጅሊስ ምርጫ ምንም ዓይነት በዚህ ሂደት ልምድም ሠነድም
የተቀመጠ መነሻ አቅጣጫ አለመኖሩ፣
➢ ለምርጫ የተቀመጠ ጊዜ በጣም አጭር መሆንና የሚፈለገው ሀገራዊ የሆነ ምርጫ በመሆኑ
ረዥም ጊዜ የሚፈለግ መሆኑ፣
➢ ተመራጭም ምረጡኝ ብሎ ለራሱ የማይቀሰቅስ በመሆኑ ህዝበ ሙስሊሙን ማንን እና
እንዴት ለየት እርከን እንደሚመርጥ፣ ማሳወቅና ማብቃቱ ውስብስብ መሆኑ፣
➢ በቂ በጀት እና በዘረፉ የሰለጠነ የሰው ሀይል ያልነበረ መሆኑ፣
➢ በህዝበ ሙስሊሙ መሀከል በአመለካከትና በመዝሀብ ተከፋፍሎ ወትሮውንም በተለያየ ጎራ
ላይ የተሰለፉ እያንዳንዱን ክንዋኔ ከራሱ አንግልና ውክልና ብቻ በሚመለከትበት ሁኔታ ላይ
መሆኑ፣
➢ የመጅሊሱ መዋቅሮች እና የዑለማዕ ምክር ቤት መዋቅሮች በሚገባው ደረጃ ሙሉ በሙሉያልተደራጀና በየ እርከኑ ድጋፍ የሚያደርግ አካል በበቂ ደረጃ አለመኖሩ በተለይም የዑለማዕ
አደረጃጀት ሙሉ በሙሉ የለም በሚባል ደረጃ ላይ መሆኑ፣
በምርጫ ቦርዱ እነዚህን ከላይ የተጠቀሱትን ጉዳዮች ሁሉንም እንደየ ሁኔታውና አመጣጡአጣጥሞ ችሎ እና አቻችሎ በመያዝ ከየትኛውም ጊዜ በተሻለሁኔታ ፈጥኖ አደራጅቶ አሰልጥኖ
በቂ የምርጫ ቁሳቁስ አዘጋጅቶ አወያይቶ በሹራ ባህል አማክሮ አስመርጦ ውጤት ለይቶየተቋሙን የመምራት ሚና ሊሚወጡ የህዝብ ተመራጮች ምርጫን በግልፀኝነት፣በፍትሃዊነት፣ በአካታችነትና በአሳታፊነት በማካሄደ ስልጣንን አረካክበዋል፡፡
ሌላው የዘንድሮን ምርጫ ልዩ ከሚያደርገው ጉዳይ የሰለጠኑ ሀገራት ዛሬ ላይ የሚጠቀሙበትንየIT ቴክኖሎጂን በምርጫ 2017 በመጠቀም በምያስደምም ሁኔታ የምርጫን ሂደት ከምዝገባእስከ ውጤት በማሳለጥ ማከናወኑ ነው፡፡
በዚህ ዘርፍ የምርጫ ቦርዱ የወሰዳቸው ቴክኒካዊ እርምጃዎች ከተቋሙ ባሻገር ለሀገርምተምሳሌታዊ ተግባር ሆኖ አልፏል፡፡ ለምርጫ ምዝገባ የሚዉሉ ቁሳቁሶችን በተመለከተ
ከ20,000,000 ባለይ የሚሆን የምርጫ ካርድና መዛግብት ታትሞ ተሰራጭቷል፡፡
የምርጫሂደቱን አሳታፊና አካታች ለማድረግ ከተለያየ አመለካከትእና መዝሃብ ጀማዓዎች፣ ተቋማትከ38 ስብሰባና ውይይቶች በላይ ተደርገዋል፡፡ ሂደቱ ከ 49,000 በላይ መሳጂዶችን በምርጫውያሳተፈ ሲሆን በዚህም ከ 13,000,000 ሙስሊም ማህበረሰብ እንደየዘርፉ በዑለማዕ፣ በምሁር፣በወጣት፣ በሴት እና በሥራ ማህበረሰብ በፍቃደኝነትና በሙሉ ተነሳሽነት ተሳተፈዋልለምርጫ ከተመዘገበው ሙስሊም ማህበረሰብ ውስጥ በአጠቃላይ እንደ ሀገር ከ 80% በላይ
ወጥቶ የመረጠ ሲሆን፡፡
ከመስጂድ እስከ ፌዴራል ምክር ቤት በተደረጉት ምርጫዎች በአጠቃላይ እንደሀገር441,378 ተመራጮች በመስጂዶች በየዘርፉ ተመርጠዋል፡፡
በወረዳ ላይ የተደረገ ምርጫ 9126 ተመራጮች በሀገር ደረጃ በወረዳ ም/ቤትየተመርጠዋል፡፡
በሀገር ደረጃ ለዞኖች ም/ቤት የተመረጡ 1377 ተመራጮች ናቸው፡፡
ሁሉም ክልሎች የራሳቸውን ምክር ቤት ለማቋቋም በተካሄደው ምርጫ ምርጫችንበመስጂዳችን በሚል መርህ መሠረት እንደሚከተለው ምርጫቸውን አከናውነዋል፡፡