AFZAN MEDIA /አፍዛን ሚዲያ

AFZAN MEDIA /አፍዛን ሚዲያ "ለከል ሀምድ
ባንተ ፍቃድ እንጂ አንዱም አይሆንም
ባምፅህም ያላንተዉ መጠጊያም የለኝ
ኢላሂ ፈግፊር ሊ ላየግፊሩ ዘንበ ኢላ አንተ"

14/02/2026

የሲርለና በጎ አድራጎት ድርጅት ለ1 ሺህ ቤተሰቦች የረመዳን የአስቤዛ ድጋፍ አበረከተ!

- የካቲት 7 ቀን 2018 ዓ.ል

የሲርለና የበጎ አድራጎት ድርጅት የታላቁን የረመዳን ወር ፆምን በማስመልከት፣ በተለያየ ምክንያት በችግር ውስጥ ለሚገኙ 1,000 ቤተሰቦች የአስቤዛ ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ።

በኡስታዝ ኑሩ ቱርኪ የሚመራው ይህ ድርጅት ድጋፉን ሊያበረክት የቻለው፣ በቅርቡ በማኅበራዊ ሚዲያ (በተለይም በቲክቶክ) ለአራት ቀናት ባካሄደው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብር አማካኝነት መሆኑ ተገልጿል።

በዕለቱ ድጋፍ ከተደረገላቸው ወገኖች መካከል 315 የሚሆኑት የክርስትና እምነት ተከታዮች መሆናቸውንም ኡስታዝ ኑሩ ቱርኪ ገልጸው፤ ለዚሁ በጎ ተግባር ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት ወላጅ አልባ ሕፃናትን (የቲሞችን)፣ አረጋውያንን፣ ምስኪኖችንና ለችግር ተጋላጭ የሆኑ ወገኖችን ጨምሮ በቀጥታ ድጋፍ የሚያደርግላቸው ቤተሰቦች ቁጥር 1,700 መድረሱ ታውቋል።

የሲርለና በአሁኑ ወቅት ሥራዎቹን እያከናወነ የሚገኘው በኪራይ ቤት ውስጥ በመሆኑ፣ የሚመለከተው የመንግሥት አካል ድርጅቱ የሚሠራቸውን ዘርፈ-ብዙ የበጎ አድራጎት ተግባራት ከግምት ውስጥ በማስገባት ቋሚ የሆነ የመሥሪያ ቦታ እንዲሰጠው ጥሪ ቀርቧል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ፕሬዝዳንት ሸኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በመርካቶ የሚገኘውን ባዩሽ መስጂድ ጎበኙ!የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ፕሬዝዳንት ሸኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ዛሬ የጁሙዓ ሶላት በፊ...
13/02/2026

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ፕሬዝዳንት ሸኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በመርካቶ የሚገኘውን ባዩሽ መስጂድ ጎበኙ!

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ፕሬዝዳንት ሸኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ዛሬ የጁሙዓ ሶላት በፊት በመርካቶ አደሬ ሰፈር የሚገኘውን ባዩሽ መስጂድ እና የሰጋጅ ሁኔታ ጎብኝተዋል።
ባዩሽ መስጂድ የአንዲት እናት መኖሪያ የነበረና ለመስጂድነት የሰጠችው (ወቅፍ) በመሆን ምእመናንን ማገልገል ገጀመረ ረጅም አመታት ተቆጥረዋል። ነገር ግን የዚህ መስጂድ ጥበት እና የሰጋጁ ቁጥር መመጣጠን ባለመቻሉ ሰጋጆች በርካታ አመታትን በእለት ተእለት መስጂዱ ሞልቶ በዙሪያው ባሉ ቅያሶችና መንገዶች ሞልተው ተትረፍርፈው ሲሰግዱ ዛሬ ደርሰዋል።
በበጋ የፀሀዩ ብርታት እንዲሁም በክረምት መፋሰሻ የሌለው ጎርፍ እየፈሰሰባቸው ሲሰግዱ የቆዩት እነዚሁ የመስጂዱ ተጠቃሚዎች ይህን ችግራቸውን ፕሬዝዳንቱ ዛሬ ከጁሙዓ ሶላት በፊት እየተዘዋወሩ በአይናቸው ተመልክተዋል።

በስተመጨረሻም ወደ መስጂዱ በመመለስ መጠነኛ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸውም የባዩሽ መስጂድን ችግር በወሬ ይሰሙት እንደነበርና በአካል ያዩት ግን እጅግ እንዳስደነገጣቸው ተናግረዋል። ሰጋጁ በዚህ ልክ እየተንገላታ እንደነበር በወሬ የሚነገረው የሚገልፀው እንዳልሆነና ጉዳዩ አሳሳቢ መሆኑን በአይን አይተው መረዳታቸውን ገልፀው መስጂዱ የሀገርን ወደ ልህቀት ጉዞ በጠበቀ መልኩ የከተማን ውበትና ስታንዳርድ በጠበቀ መልኩ መስፋፋት እንደሚያስፈልገውና እንደ መጅሊስ በዚህ ሂደት የአቅማቸውን እንደሚያደርጉ በዚህም ጉዳይ የከተማው አስተዳደር ባለድርሻ አካላት ለባዩሽ መስጂድ መስፋፋት ትብብር እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

ባዩሽ መስጂድ በድምፃችን ይሰማ ግዜ ምን ያህል የታገለ ጀማአ መሆኑን አስታውሰውም ለዚህ የትላንት የትግል ጀማዓ ዛሬ ለውጥ ሲመጣ ከጎኑ ቁሞ ችግሩን መቅረፍ ከሁሉም በፊት ተገቢ እንደሆነም ገልፀዋል።

ረመዳንን እንዴት እንቀበል ?1. በየትኛውም ቅፅበት ሞት ሊመጣ ይችላልና እንዲያደርሰን ዱዓ ማድረግ፣ እንዲሁም ደርሰውም በጤና እክል፣ እስር ቤት በመግባትና በተለያዩ ስንክሳሮች የማይጠቀሙም ...
06/02/2026

ረመዳንን እንዴት እንቀበል ?

1. በየትኛውም ቅፅበት ሞት ሊመጣ ይችላልና እንዲያደርሰን ዱዓ ማድረግ፣ እንዲሁም ደርሰውም በጤና እክል፣ እስር ቤት በመግባትና በተለያዩ ስንክሳሮች የማይጠቀሙም አሉና ደርሰው ከሚጠቀሙት እንዲያደርገንም በዱዓ መበርታት ፣

2. ወደ አላህ በመመለስ ፣ ተውባህ ሹሩጦቹ ከተሟሉ ያልተሰራ ያህል ያለፈ ወንጀልን ሀሉ ያስምራል ፣ እንደ ኢኽላሱ መጠን በአላህ ቸርነት ወደ ሀሰናትም የሚቀይርላቸው አሉ ።

3. አላህ እንዲያዝንልን እና ይቅር እንዲለን ፆማችንም የተሟላ እንዲሆን እርስ በእርስ ይቅር መባባል ። በዙሪያችን ካሉ ሰዎች ጋ አዲስ የመልካም ግንኙነት በር መክፈት ፣ ረመዳንን በንፁህ ልብና በሰፋእ መቀበል ፣

4. ረመዷን ትልቅ ፀጋ ነውና ከፆመኞች ስላረገን አላህን ከልብ ማመስገን ፣

5. በረመዳን ለመጥ'ጠቀም ቆራጥ ውሳኔ መወሰን !

6. በረመዳን ውስጥ የምንከውናቸውን ዒባዳዎች ፕሮግራም ማውጣትና ላወጣነው ፕሮግራምም Committed መሆን። ምናወጣቸው ፕሮግራሞችም ቤተሰቦቻችንን ያካተተ ማድረግ ፣

7 . ረመዷንን እንዳንጠቀም የሚያዘናጉን ነገሮችን ሁሉ ማስወገድ ። በዋነኝነት ከሶሻል ሚዲያዎች መራቅ ። በምግብና መጠጥ ዝግጅት ረዥም ሰዐታትን አለመፍጀት ፣ .....

8. ስለ ፆም አህካምና ፈዷኢሎችን አስቀድሞ ማወቅ ። የረመዳንን ድባብ ሊያመጡልን የሚችሉ ቢዓዎችን መፍጠር ። ስለ ረመዳን አብዝቶ ማውራት ማዳመጥ ማንበብ እና የመሳሰሉት ፣

9. ወንጀላችንን ሚያስምረን ከአላህ ሚያቃርበን ወር በመሆኑ
በረመዷን መምጣት መደሰት ፣ ፈካ ማለት ፣ ኢስቲብሻር ማድረግ ።

ሽይኹና ሀሚድ ሙሳ
ሻዕባን 18 / 1447 في مسجد بايوش

ኡመር ሙኽታር"ተራራ ምንም ያህል ቢገዝፍ ጫፍ አለውየት'ግል ጉዞ ረዥም ቢሆን መድ'ረሻ አለው".....💪     "እኛ እጅ አንሰ'ጥም ድ'ል እናደር'ጋለን  አልያም የክብር ሞ'ት እንሞ'ታለን"...
29/01/2026

ኡመር ሙኽታር

"ተራራ ምንም ያህል ቢገዝፍ ጫፍ አለው
የት'ግል ጉዞ ረዥም ቢሆን መድ'ረሻ አለው".....💪

"እኛ እጅ አንሰ'ጥም ድ'ል እናደር'ጋለን
አልያም የክብር ሞ'ት እንሞ'ታለን"......🫡

የዒልሙ መሐንዲስ - ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ !ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ በ1945 አ.ል በዋድላ ደላንታ ተወለዱ ። የተወለዱባት መንደር ስያሜ አቃዱር ይሰኝ ነበር ። ከአባታቸው አህመድ...
06/01/2026

የዒልሙ መሐንዲስ - ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ !

ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ በ1945 አ.ል በዋድላ ደላንታ ተወለዱ ። የተወለዱባት መንደር ስያሜ አቃዱር ይሰኝ ነበር ። ከአባታቸው አህመድ ሸይኽ ሙስጠፋ እና ከእናታቸው ተዋበች አጋሽ ነበር የተገኙት ።

ገና በለጋ እድሜያቸው በአካባቢያቸው በነበረ የመኖሪያ እና የእርሻ ቦታ እጥረት ምክንያትና የኑሮው ነገር ስላልገራላቸው ከመንደሩ ለቀው እንዲወጡ ግድ ሆነባቸው ። ከመንደራቸው የመኮብለል ጉዳይ ለእናታቸው ወ/ሮ ተዋበች አጋሽ እንዲህ በቀላል የሚታይ አልነበረም ። ከባለቤታቸው ጋር እስከመለያየት አደረሳቸው ። የኑሮ መላ ያስኮበለላቸው የሸይኽ ሰዒድ አባት ፣ ታላቅ ወንድምና አጎታቸው አካባቢውን ለቀው ወደመተከል ያቀናሉ ። ሸይኽ ሰዒድ ግን ከእናታቸው ጋር በመንደራቸው ጸኑ ።

አባታቸው ለደረስነት እንዲሁም ልጃቸው በኢልሙ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ልዩ ፍላጎት ነበራቸው ። በርሳቸው ግፊትና ተፅዕኖ ሸይኽ ሰዒድ የደረስነት ህይወት ጀመሩ ። መሰረታዊውን የፊቅህን ስርዓተ እውቀት ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ቦረና ተጉዘው ለ3 ዓመታት ያክል የነህዉንና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነውም ቢሆን የተፍሲር ቂርዓታቸውን ቀጠሉ ።

በሀገራችን ኢትዮጵያ የሚሰጡ ኪታቦችን ካጠናቀቁ ቡሀላ ወደ አዲስ አበባ መጡ ። እዚህም የመጡበት ምክንያት ከዚህ ሀገር ወተው ወደ አረብ ሀገራት ተጉዘው የሀዲስ እንዲሁም ሌሎች ቂርአቶችን ለመቅራት አስበው ነበር ።

በወቅቱም ሀጂ ሙሐመድ ራፊዕ ከሳውድ አረቢያ ተመልሰው አንዋር መስጂድ ላይ ደረሶችን ሲያቀሩ የሚያቀሩበት ነበርና ያገኟቸዋል ። ሃሳባቸው ከሐጂ ሙሐመድ ራፊዕ ዘንድ ለመቅራት ነበር ። ቆይተው ሐጂ ሙሐመድ ራፊዕ ወደትውልድ መንደራቸው ይሄዱ ነበርና አልተሳካም ። ሸይኽ ሰዒድ ግን ቂርዓታቸውን ከሐጂ ሙሐመድ ወሌ ዘንድ ይቀጥላሉ ። ሐጂ ሙሐመድ ራፊዕ እስኪመለሱ ድረስ . . .!

ሐጂ ሙሐመድ ራፊዕም የጥቅምት ማገባደጃ ላይ ወደአዲስ አበባ ይመለሳሉ ። ሸይኽ ሰዒድ ወትሮም ጊዜያቸውን በአግባቡ የሚጠቀሙ ነበሩ ። ኩቱቡ ሲታን እሳቸው ጋር ቀርተው ማጠናቀቅ ቻሉ ። በማለዳው ክፍለ ጊዜ ደግሞ ከሐጂ ሙሐመድ ሳኒ ዘንድ ተፍሲርን ሙራጀዓ ሲያደርጉ ይቆያሉ ።

አዲስ አበባ የነበራቸውን ቆይታ እንደጨረሱ ወደ ትውልድ ስፍራቸው ሄደው የማስቀራት ፍላጎት የነበራቸው ቢሆንም እዚሁ አንዋር መስጂድ የነበሩት 3 ታላላቅ ዑለሞች ፍቃደኛ ሳይሆኑ ይቀራሉ ። ምክንያታቸው ደግሞ በወቅቱ የነበረው የደረሳ መጠን መብዛት ሸይኽ ሰዒድ እዚህ መቆየታቸውን ግድ ይል ነበር ።

ትዕዛዙን ተቀብለው ሸይኽ ሰዒድ ዒልምን ማቅራት ጀመሩ ። በቆይታቸው የማረፍያ ስፍራና የእለት ጉርስ ማግኘት በጣም አስቸጋሪ ሆኖባቸው እንደነበር ይናገራሉ ። በዚያ ወቅትም ቀኑን ወሎ ሰፈር ድረስ በእግራቸው በመጓዝ ልጆችን ያቀራሉ ። እዚያው ቤትም ምሽቱን በጥበቃነት ማገልገል ይጀምራሉ ።

በቀጣዩ የህይወት ምዕራፋቸው ለ15 አመታት አንዋር መስጂድ ዒልምን ሲያቀሩ ቆይተዋል ። ሸይኽ ሰዒድ በእድሜ ዘመናቸው በደማቁ ከሚወሱበት አበርክቷቸው መሐል በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያውን የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ማህበር ወይም በተለምዶ ሙነዘማን ማቋቋም ነበር ። እጅግ ብዙ ጥረትና ልፋት የታየበት ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች መብታቸው የሚጠይቁበትና ማንነታቸውን የሚያስከብሩበት ተቋም መሆን የቻለ 165 ያህል ቅርንጫፍ ማዕከላትን ማቋቋም የቻለ ነበር ። በጊዜው መንግስት ለተቋሙ ሕጋዊ እውቅናና ፈቃድ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም የኋላ ኋላ ስጋት ይሆናል በሚል አደረጃጀቱ እንዲፈርስ የተለያዩ ስራዎች ተሰርተዋል ።

ሸይኽ ሰኢድ አህመድ ሙስጠፋ በዚህ ሁኔታ ላይም ሆነው በ 5 መስጂዶች ላይ ተፍሲርን በማቅራት ሙሉ በሙሉ አጠናቀው የነበረ ሲሆን በኒ መስጂድ ፣ አንዋር መስጂድ ፣ ሀሺም መስጂድ ይገኙበታል ። በዚህ አጋጣሚ ኡምራ የማድረግ እድል ያገኙት ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ ዑምራቸውን ፈጽመው ከ15 ቀናት በኋላ የመመለስ እቅድ ነበራቸው ። ያ ግን በተለያየ ምክንያት ሊሰምር አልቻለም ። እርሳቸው ሄደው ቀናት ባስቀጠሩበት አጋጣሚ አገር ውስጥ ነገሮች ተቀያይረዋል ።

ታዲያ በጊዜው አንድ ሁነት ይከሰትና ነገሮች መልካቸውን ይቀይራሉ ። የወቅቱ መንግስት በአንዋር መስጂድ እጅግ ብዙ ወጣቶችን ህይወት በመቅጠፍ እንዲሁም ሙስሊሞች ተለይተው ድብደባ እንደተፈጸማባቸው ፣ የተለያዩ መሻዒኾች እየታሰሩ የግድያ ፍርድም እየተፈረደባቸው እንደሆነና እሳቸውም በጥብቅ እየተፈለጉ እንደሆኑ ይሰማሉ ።

ሸይኽ ሰዒድም በነዚህና መሰል ምክንያቶች ሳዑዲ አረቢያ ይሰነብታሉ ። በዚህ ሁኔታ ቀናት ቀናትን እየተካ ወራትም ወራትን እየተኩ አመታት ተቆጠሩ ። ሸይኽ ሰዒድ የመኖሪያ ፍቃድ ስላልነበራቸው ከአደባባይ ተሸሽገው ከማንም ጋር ሳይገናኙ ለ 2 አመት ያክል ከቆዩ ቡሀላ ሳዑዲ አረቢያ ይኖሩ የነበሩት ሸይኽ አህመድ ሀዲ ሸይኽ ሰኢድን አፈላልገው ያገኟቸዋል ። ሸይኽ አህመድ ያላቸውን አቅም ያውቁ ስለነበር ወደ አራት የሚጠጉ የዓቂዳ ኪታቦችን እንዲያቀሩና የድምፃቸውም ቅጂ ወደ ኢትዮጵያ በካሴት መልክ ተዘጋጅቶ እንዲሰራጭ ያማክሯቸዋል ። ሸይኽ ሰዒድም በጣም ደስተኛ እንደሆኑ በመናገር ስራቸውን ይጀምራሉ ።

ቆይቶ ሙሉ ለሙሉ ስራቸውን በማጠናቀቅ ሸይኽ አህመድ ሙአሰተል ሀረመይን ከሚባል ድርጅት ጋር የነበራቸውን ትውውቅ ተጠቅመው የሸይኽ ሰዒድ አህመድ ድምፅ ተቀድቶ በካሴት መልክ ወደ ኢትዮጵያ እንዲሰራጭ ሆነ ። ስራቸው ተወዳጅነት ማትረፍ የቻለና በብዙዎች ዘንድ የሚወሳ መሆን ችሏል ። ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖች ጭምር ወደው ያደምጡት እንደነበር ይወሳል ።

ሸይኽ ሰዒድ ሌላኛው ግዙፍ እድል ብለው የሚያነሱት አንጋፋው አፍሪካ ቲቪ ምስረታውን ያደርጋል ። እሳቸውም በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪው በሆነው ኢስላማዊ የሳተላይት የቴሌቭዥን ጣቢያ የቁርዓን ተፍሲርን ማስማር ጀመሩ ። የብዙዎች ዘንድ ተወዳጅ እና ተናፋቂ ሆኖ የብዙዎችን ልብ ከቁርዓን ጋር አዛምዷል ። በዚህ ሁሉ ውስጥ የ9 ልጆች አባት የሆኑት ሸይኽ ሰዒድ ቤተሰባቸውን አልዘነጉም ነበር ።

ከቅርብ ዓመታት በፊት ለ23 ዓመታት ርቀዋት ወደቆዩት አገራቸው በመመለስ ሙስሊሙን ማህበረሰብ ማገልገላቸውን ቀጥለዋል ። በአፍሪካ ቲቪ አል ፈታዋን ጨምሮ የተለያዩ ሸሪዓዊ መሰናዶዎች እያቀረቡ ያሉ ሲሆን አፍንጮ በር የሚገኘው የአቅሷ መስጂድ ዒማምና ኸጢብ በመሆን ከዚያን ባሻገር በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት የዑለሞች ምክር ቤት አባል በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ ።

አላህ ( ሱ.ወ ) ከመልካም አበርክቷቸው ጋር አጽንቶ በረዥም እድሜ በበረታ አፍያ ያቆያቸው ።

#አፍሪካቲቪ
#የህይወትጎዳና

☞ #ቡዲስት በነበርኩበት ጊዜ በነቢዩ  #ዒሳ (ዐ.ሰ) አላመንኩም ነበር።☞ #ክርስቲያን ስሆን በነቢዩ  #ሙሐመድﷺ  አላመንኩም ነበር።አላህ ሒዳያ ሰቶኝ ወደ  #እስልምና ስመጣ ግን  #በሁሉ...
03/01/2026

☞ #ቡዲስት በነበርኩበት ጊዜ በነቢዩ #ዒሳ (ዐ.ሰ) አላመንኩም ነበር።

☞ #ክርስቲያን ስሆን በነቢዩ #ሙሐመድﷺ አላመንኩም ነበር።

አላህ ሒዳያ ሰቶኝ ወደ #እስልምና ስመጣ ግን #በሁሉም የአላህ #ነብያት አመንኩ። #አልሀምዱሊላህ
ቻይናዊው ሃፊዘሁሏህ ( በ peace tv የምናውቃቸው ሼይኽ)
Hijra Tube ኢስላማዊ ድህረ ገፅ

29/12/2025

«...በእድሜው የተጫወተ ሰው ማለት የመዝሪያ ገዜውን እንዳጠፋ ሰው ነው። የመዝሪያ ግዜውን ያጠፋ ሰው ደግሞ በሚታጨድበት ቀን ላይ ይፀፀታል...»

ሱፍያን አስ–ሰውሪይ

25/12/2025

በተሰጠን ነገር አመስጋኝ እንሁን
#አልሀምዱሊላህ

♦️ መጽሐፍ ቅዱስ ባለፉት 2ሺህ ዓመታት➢ ሙሉ ቅጂው ከ776 በላይ በሆኑ ቋንቋዎች ተተርጉሟል።➢ በእንግሊዝኛ ብቻ 500 የሚደርስ የቃላት እርምት ተደርጎበታል። ➢ በአማርኛ 8 የሚደርሱ የተ...
24/12/2025

♦️ መጽሐፍ ቅዱስ ባለፉት 2ሺህ ዓመታት
➢ ሙሉ ቅጂው ከ776 በላይ በሆኑ ቋንቋዎች ተተርጉሟል።
➢ በእንግሊዝኛ ብቻ 500 የሚደርስ የቃላት እርምት ተደርጎበታል።
➢ በአማርኛ 8 የሚደርሱ የተሻሻሉ ትርጓሜዎች አሉ።
➢ በሁሉም ቋንቋዎች ደግሞ በሺህ የሚቆጠር የቃላት እርምት ተደርጎበታል።

♦️ ቁርኣን ከወረደ 1400 ዓመታት ሆኖታል።
➢ ከ100 በላይ በሆኑ ቋንቋዎች ተተርጉሟል።
➢ በእነዚህ ዓመታት ሁሉ እስካሁን ዐረቢኛው አንድም የቃላት እርምት አልተደረገበትም።

⏺ ይህንን ብቻ ያስተዋለ ሰው የትኛውን መጽሐፍ ማመን እንዳለበት ማስረጃ ይሆነዋል።
©ሰልማን
AFZAN MEDIA /አፍዛን ሚዲያ

ሶሻል ሚዲያን ያጨናነቀ ያስቆጣ ያሳዘነ በሀገረ ግብፅ የተከሰተ አፀያፊ ወንጀል የ13 አመት ሸይማ በአንድ ወጣት ተደፈረች ከደፈራትም ቡላ የደፈራትን እዳታውቅ አይኗን ለማውጣት ሲታገል የከፋ ...
24/12/2025

ሶሻል ሚዲያን ያጨናነቀ ያስቆጣ ያሳዘነ በሀገረ ግብፅ
የተከሰተ አፀያፊ ወንጀል

የ13 አመት ሸይማ በአንድ ወጣት ተደፈረች ከደፈራትም ቡላ
የደፈራትን እዳታውቅ አይኗን ለማውጣት ሲታገል የከፋ ጉዳት አደረሰባት🥺

ምን አይነት ዘመን ለይ ደረስን ነገሩ እዲነው ልጅቷ ሸይማ ትባላለች ሸይማ እናቷን ቀን በስራ ታግዛለች የሚሸጡ ነገሮችን እየዞረች ሽጣ ማታ ከቤቷ ትገባለች ሸይማ ለእናቷ አንድ ናት አባት የላትም አባቷ ሞቷል ሸይማ እቃ ሸጣ ከቤት ስትመጣ በጣም እርቧት ስለነበር ለእናቷ ምግብ ስጪኝ ስትላት ምግብ እኪደርስ ከውጭ ገዝተሽ ብይ አለቻት እናቷ ሰአቱም መሽቷል ሸይማም ለመግዛት በአቅራቢያዋ ከሚገኘው ሱቅ ስትሄድ የፈለገችውን እቃ ታጣለች ትንሽ ከሰፈሯ ራቅ ከሚልበት ሱቅ ስትሄድ የምትመለከቱት ወጣት ሸይማን ይከተላትና ሞባየል ትገዣለሽ ሲላት አይ አልፈልግም ብላው ስትሄድ ተከትሏት ይሄድና ከሀላዋ ከአንድ ጨለማ ዛፍ ወዳለበት አስገብቶ እዳትጮህ አፏን አፍኖ ይደፍራትና ከደፈራት ቡሀላ ታሲዘኛለች ስለዚ እዳታውቀኝ አይኗን ማውጣት አለብኝ ብሎ አይኗን ለማውጣት ሲታገል ሸይማ እራሷን ስታ ስትወድቅበት ሞታለች ብሎ ጥሏት ስሄድ ሸይማ ከተወሰኑ ሰአታት ቡሀላ ስትነቃ ካለችበት ቦታ ስትጮህ ፖሊሶች ደርሰውላት
እሱም ተያዘ ልጁን በቁጥጥር ስር አዋሉት ሸይማ በጣም ቆንጆ
ዘላ ያልጠገበች ህፃን አይኗን እንደዚ አድርጎ አበላሻት
የልጅነት ህልሟን አጨለመባት 🥺💔

እናትየው የልጁ ቤተሰቦች እያስፈራሯት ይገኛሉ በጣም ተጎድታለች እደምታያት 💔💔
AFZAN MEDIA /አፍዛን ሚዲያ

Address

Addis Ababa

Telephone

+251905586634

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AFZAN MEDIA /አፍዛን ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to AFZAN MEDIA /አፍዛን ሚዲያ:

Share