AFZAN MEDIA /አፍዛን ሚዲያ

AFZAN MEDIA /አፍዛን ሚዲያ "ለከል ሀምድ
ባንተ ፍቃድ እንጂ አንዱም አይሆንም
ባምፅህም ያላንተዉ መጠጊያም የለኝ
ኢላሂ ፈግፊር ሊ ላየግፊሩ ዘንበ ኢላ አንተ"

የዙል-ሂጃህ 1447 ዓ.ሂ ጨረቃ እሁድ ምሽት፣ ግንቦት 17፣ 2026 ታይቷል። ስለዚህ የዙል-ሂጃህ የመጀመሪያ ቀን ሰኞ፣ ግንቦት 18፣ 2026 ነው።በዚህ መሰረት፡-የአረፋ ቀን (9 ዙል-ሂጃ...
17/05/2026

የዙል-ሂጃህ 1447 ዓ.ሂ ጨረቃ እሁድ ምሽት፣ ግንቦት 17፣ 2026 ታይቷል። ስለዚህ የዙል-ሂጃህ የመጀመሪያ ቀን ሰኞ፣ ግንቦት 18፣ 2026 ነው።

በዚህ መሰረት፡-

የአረፋ ቀን (9 ዙል-ሂጃህ)፡ ማክሰኞ ግንቦት 26፣ 2026

ኢድ አል-አድሃ (10 ዙል-ሂጃህ)፡ ረቡዕ፣ ሜይ 27፣ 2026

1️⃣ በእነዚህ ቀናት ሙሉ ቁርአን ለማክተም ሞክር። ረሱል ﷺ በየሳምንቱ ቁርአንን ይክትሙ ነበር፤ እኛም እንከተላቸው።2️⃣ ስልክህን ለበጎ ነገር ተጠቀምበት። ከስልክ መራቅ ካልቻልክ፣ ቁርአን...
17/05/2026

1️⃣ በእነዚህ ቀናት ሙሉ ቁርአን ለማክተም ሞክር። ረሱል ﷺ በየሳምንቱ ቁርአንን ይክትሙ ነበር፤ እኛም እንከተላቸው።

2️⃣ ስልክህን ለበጎ ነገር ተጠቀምበት። ከስልክ መራቅ ካልቻልክ፣ ቁርአን ለማንበብ፣ ዚክር ለማድረግ እና የጠዋትና የማታ አዝካር ለማንበብ አድርገው።

3️⃣ በመንገድ፣ በመኪና፣ በመጠባበቂያ ሰዓት ሁሉ “አላሁ አክበር፣ ላኢላሀ ኢለላህ ፣ወልሀምዱሊላህን ድምፃችንን ከፍ አድርገን በብዛት ማለት (ተክቢራ)
ልጆችህንና ቤተሰብህን ተክቢራ አንዲሉ አስተምራቸው። ቀላል ነገር ቢመስልም ታላቅ ምንዳ አለው።

4️⃣ ኡዱህያ ለቻለ ሰው

5️⃣ ከዘጠኙ ቀናት የቻልከውን ጹም፤ በተለይ የዐረፋ ቀን (9ነኛ ቀን)።
☞ የዐረፋ ጾም የሁለት ዓመት ወንጀል ያስምራልና።

6️⃣ ሴት ልጅ በሃይድ ምክንያት ካልጾመች፣ ባሏን፣ ልጆቿንና ቤተሰቧን ለጾም ታበረታታ፤ ወደ መልካም የተጣራ ልክ እንደ አደረገው ይመነዳልና።

7️⃣ የሌሊት ሶላትን አትተው። ነቢዩ ﷺ ቂያሙል ለይልን አያቋርጡም ነበር። ሰዒድ ኢብኑ ጁበይርም “በእነዚህ ሌሊቶች መብራታችሁን አታጥፉ” ይሉ ነበር።

8️⃣ ሰደቃ አብዛ። ትንሽ ቢሆንም በየቀኑ ስጥ፤ በተለይ በስውር የሚሰጥ ሰደቃ ታላቅ ምንዳ አለው።

9️⃣ ኒያ ። ለእንቅልፍህ፣ ለምግብህ፣ ለስራህ እና ለሁሉም የዕለት ተዕለት ተግባሮችህ መልካም ኒያ አድርግ፤ ሁሉም ኢባዳ ይሆናሉ።

🔟 ዱዓ የሪዝቅ ቁልፍ ነው። ዱአ መቅቡል የሚሆንባቸውን ጊዜዎችን ተጠቀም፦

▪️ በአዛንና ኢቃማ መካከል
▪️ ከፈርድ ሶላት በኋላ
▪️ በሱጁድ ላይ
▪️ በሌሊት የመጨረሻ 1/3 ሰአት
▪️ በጁምዓ ቀን የመጨረሻ ሰዓት
#አስታውስ፦ ከሁሉ በላይ የተሻለው ዱዓ የዐረፋ ቀን ዱዓ ነው።

በኢባዳ እንበርታ ‼
አላህ በፃፍነውም ባነበብነውም የምንጠቀም ያድርገን!
አሚን!

አስደሳች ዜና!​አልሃምዱሊላህ! ልጃችን በሰላም ተገኝታለች!​ከአንድ ወር በፊት ጠፍታ የነበረችው ልጃችን፣ በቃሊቲና ሳሪስ አካባቢ በሚገኘው የሴቶችና ህፃናት መምሪያ መገኘቷ ተገልጾልን፣ በዛሬ...
05/05/2026

አስደሳች ዜና!

​አልሃምዱሊላህ! ልጃችን በሰላም ተገኝታለች!

​ከአንድ ወር በፊት ጠፍታ የነበረችው ልጃችን፣ በቃሊቲና ሳሪስ አካባቢ በሚገኘው የሴቶችና ህፃናት መምሪያ መገኘቷ ተገልጾልን፣ በዛሬው ዕለት በሰላም ወደ ቤተሰቧ ተቀላቅላለች። በዚህ አስጨናቂ ወቅት ከጎናችን ለቆማችሁ፣ በጸሎትም ሆነ መረጃ በማሰራጨት ላገዛችሁን ሁሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

​ለወላጆች የቀረበ ጥሪ፦

​ውድ ወላጆች፣ ልጆቻችን የነገ ተስፋዎቻችን ናቸው። ልጆቻችሁን ከአታላዮችና መሰል አደጋዎች ለመጠበቅ ተገቢውን ክትትልና ጥበቃ እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን። እኛ የደረሰብን ጭንቀት በማንም ላይ እንዳይደርስ ጥንቃቄው አይለይባችሁ።

​ፈጣሪ አምላክ ለሁላችሁም ክፉውን አያሳያችሁ!

የእናት አባት እንባ ይፍረድባቸው 😭😭😭😥⚠️ ጥንቃቄ - የተፈጸመ ማጭበርበርየልጅቷ ቤተሰቦች ልጃቸውን ለማግኘት ሌሊት ከቀን በሚለፉበት በዚህ ወቅት፣ ጨካኝ አጭበርባሪዎች "ከአዋሽ ፖሊስ ጣቢያ...
04/05/2026

የእናት አባት እንባ ይፍረድባቸው 😭😭😭😥
⚠️ ጥንቃቄ - የተፈጸመ ማጭበርበር
የልጅቷ ቤተሰቦች ልጃቸውን ለማግኘት ሌሊት ከቀን በሚለፉበት በዚህ ወቅት፣ ጨካኝ አጭበርባሪዎች "ከአዋሽ ፖሊስ ጣቢያ ኮማንደር ነኝ፣ ጥቆማ ደርሶን ነው ልጅቷ ከፍተኛ አደጋ ደርሶባት ሆስፒታል ናት ያለ ኦክስጅን መንቀሳቀስ አትችልም ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሪፈር ተደርጎላታል አምቡላንስ ሆስፒታሉ ስለሌለው እና ኦክስጅን ያለ ማስያዣ ይዞ መውጣት ስለማይቻል የኦክስጅንና የትራንስፖርት ብር ላኩ" በማለት ቤተሰቡን በስስ ጎን በመግባት ለሁለተኛ ጊዜ ሰለባ አድርገዋቸዋል። ቤተሰቡ ብሩን ከላኩ በኋላ ጉዳዩን ለፖሊስ ሪፖርት አድርገው ነበር ነገር ግን ግለሰቦቹ ስልካቸውን አጥፍተዋል። እባካችሁ ማንም ሰው በዚህ ስልክ ደውሎ ገንዘብ ቢጠይቅ እንዳታምኑ!

እኛ ሰፈር ይሄ ፎቶ ተበትኖ ሳይ አልቻልኩም ይቺ የ11 ዓመት ህፃን አልተገኘችም እባካችን ሁላችንም የበኩላችንን እንወጣ አንድ ወር ሆናት😭

ልጃችን ከጠፋች ወር ሆናት እባካችሁ እንድናገኛት ሼር በማድረግ ተባበሩን ይሉናል ቤተሰቦቿ

ይህቺ በምስሉ ላይ የምትመለከቷት ህፃን ከጠፋች ወር ሆናት እስካሁን ልትገኝ አልቻለችም!

ስሟ ፊርደውስ ሰኢድ ይባላል የምትኖረው አውቶቢስ ተራ ጀርባ ፈትህ አባቦራ መስጂድ አካባቢ ሲሆን እድሜዋ 11 ገደማ ነው እሁድ ለት በቀን 27/7/2018 ከጓደኛዋ ጋር ተጣልታ ቤተሰቦቿ መተው ክስ ሲመሰረትባት በድንጋጤ ከቤት ወጥታ እስካሁን አልተመለሰችም የለበሰችው ልብስ ነጭ ሂጃብ እና የዩናይትድ ማሊያ እና አበባ ያለበት ሸሚዝ በቡኒ ሱሪ ነው የለበሰችው ያያት ወይም ያለችበትን የሚያውቅ በዚህ ስልክ ቁጥር እንዲያሳውቀን እንጠይቃለን።

ይህ ፅሁፍ ለብዙ ሰዎች እንዲደርስ ሼር (Share) በማድረግ ተባበሩን። አንዲት "ሼር" ህፃኗን ወደ ቤተሰቧ ሊመልሳት ይችላል።
ያያት ወይም ያለችበትን የሚጠቁም መረጃ ያለው ሰው እባካችሁን በሚከተሉት ስልኮች ይደውሉ፦
📞 0900071556
📞 0913240619
📞 0966184311
ፈጣሪ ፊርደውስን ወደ ቤተሰቦቿ በሰላም ይመልሳት!
#አዲስአበባ

ችግሩን ለመፍታት በየዘመናቱ ከሚደረገው «የሙስሊሞች ተወካዮች ከክልሉ መንግስት አመራር ጋር ተወያዩ፣ ለመፍትሔም በጋራ እንደሚሰሩ ገለጹ» ከሚል የተደጋገመ ማደንዘዣ (ማስተኛ) ንግግርና ዜና ...
17/04/2026

ችግሩን ለመፍታት በየዘመናቱ ከሚደረገው «የሙስሊሞች ተወካዮች ከክልሉ መንግስት አመራር ጋር ተወያዩ፣ ለመፍትሔም በጋራ እንደሚሰሩ ገለጹ» ከሚል የተደጋገመ ማደንዘዣ (ማስተኛ) ንግግርና ዜና ሳይታለሉ እንዲሁም ከጊዜያዊ «እሳት ማጥፋት» ሥራ ወጥቶ፣ ለጭቆናው መፈልፈያ የሆኑትን ጥልቅ አስተሳሰቦችና መዋቅራዊ እንቅፋቶች ኢላማ አድርጎ መታገል ያስፈልጋል። መፍትሔው አክሱምን ከአፓርታይዳዊ አሠራር አላቆ፣ ወደ ሀገሪቱ ሕገ-መንግሥታዊና ዓለማዊ (ሴኩላር) ሥርዓት መመለስና የዜጎችን እኩልነት በተግባር ማረጋገጥ ነው።

የአክሱም ጉዳይ

በአክሱምም በደቡብ አፍሪካ እንደታየው ሁሉ፣ የአፓርታይድ አጥሮች ፈርሰውና ጭቆናው ቆሞ ሙሉ ዜግነትና ሙሉ መብት ሊረጋገጥ ይገባል። ለዚህም የችግሩን ጥልቀት ተረድቶ፣ በአክሱም የሰፈነውን «ክርስቲያናዊ አፓርታይድ» በስሙ በመጥራት አፓርታይዳዊ ሥርዓቱን መታገል ግድ ይላል።

ኡስታዝ አህመዲን ጀበል

17/04/2026

የአክሱምና የደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ 15 ምስስሎሽ
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴

በአሕመዲን ጀበል
✅✅✅✅✅✅

«ለመሆኑ አፓርታይድ ምን እንደሆነ ታውቃለህን?»
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥

ከቀናት በፊት «ክርስቲያናዊ አፓርታይድ በአክሱም» በሚል ርዕስ ባቀረብኩት ጽሑፍ ላይ ልዩ ልዩ አስተያየቶች ተሰንዝረዋል። አንዳንዶች በሃሳቡ መከፋታቸውን ሲገልጹ፣ ሌሎች ደግሞ «ይህ ተራ የመብት ጥሰት እንጂ እንዴት ከአፓርታይድ ጋር ይገናኛል?» በሚል ሞግተዋል።

ጥቂቶች ደግሞ «ለመሆኑ አፓርታይድ ምን እንደሆነ ታውቃለህን?» ሲሉ ጠይቀውኛል። ከዚህም አልፎ በርዕሰ ጉዳዩ ላይ ከመወያየት ይልቅ በስብዕናዬ ላይ በማነጣጠር ስድብና የ«በሕግ ይጠየቅልን» ዛቻዎችን የሰነዘሩም አልጠፉም።

እኔ በማንኛውም መልኩ ሥነ-ምግባርን የተላበሰ የሃሳብ ልዩነትን አከብራለሁ። ጽሑፎቼ የትኛውንም የማህበረሰብ ክፍል ለማዋረድ ወይም ለመተንኮስ ዓላማ የላቸውም። ይሁን እንጂ፣ ችግሮችን ለመፍታት የመጀመሪያው እርምጃ ችግሩን በትክክለኛ ስሙ መጥራት መሆኑን አምናለሁ። «ክርስቲያናዊ አፓርታይድ» የሚለውን ቃል የተጠቀምኩትም ችግሩን በትክክል ይገልጻል ብዬ ስለማምንን ነው።ለማንኛውም ይህን የሰባት ገጽ ጽሁፍ በትዕግስት አንበቦ መጨረስ ትዕግስት ይፈልጋል።ከተጋሾቹ ነህ?

አፓርታይድን ከዘር ባሻገር መረዳት
📮📮📮📮📮📮📮📮📮📮

«አፓርታይድ» (Apartheid) የሚለው ቃል መሠረታዊ ትርጉሙ "መነጠል" ወይም "መለየት" (Separateness) ማለት ነው። ምንም እንኳ ቃሉ በታሪክ ከደቡብ አፍሪካው የዘር መድልዎ ጋር ቢቆራኝም፣ በፖለቲካ ሳይንስ ትርጓሜው ግን ዜጎችን በማንነታቸው ላይ ተመስርቶ በስልታዊ መንገድ የመለየት ሥርዓትን ያመለክታል። ይህ ሥርዓት አንዱን ወገን በልዩ መብቶች አጥግቦ፣ ሌላውን ደግሞ በማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የጥቃት ሰለባ የሚያደርግ መዋቅር ነው።

በአክሱም ሙስሊሞች ላይ የሚታየው እውነታ ተራ የመብት ጥሰት ሳይሆን፣ ከዚህ ጽንሰ-ሃሳብ ጋር በቀጥታ የሚገናኝ "መዋቅራዊ አግላይነት" ነው። ለዚህም ማሳያ የሚሆኑት የሚከተሉት ነጥቦች ናቸው፦

1. የአምልኮ ነፃነት መነፈግ፦ ሙስሊሙ ማህበረሰብ የራሱ የአምልኮ ቦታ ተከልክሎ በየበረንዳውና በየመንገዱ እንዲሰግድ መገደዱ።

2. የክብር ማጣትና የመቃብር እጦት፦ በገዛ ትውልድ ከተማቸው መቃብር አጥተው፣ የጀናዛ (የሬሳ) ማረፊያ ፍለጋ እስከ 40 ኪሎ ሜትር እንዲጓዙ መገደዳቸው።

3. የትምህርት ተቋማት መድልዎ፦ በትምህርት ቤቶች ውስጥ በሂጃብ ምክንያት ተማሪዎች መገለላቸውና ጥቃት መፈጸሙ።

4. የጸጥታ ኃይሎች ተሳትፎ፦ እነዚህ በደሎች በጸጥታ መዋቅሩ ጭምር የታገዙ መሆናቸው።

በአክሱም ያለው ሁኔታ ለምን ከአፓርታይድ ጋር ይመሳሰላል?
❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌

በአክሱም ያለው ሁኔታ በደቡብ አፍሪካ ከነበረው የዘር አፓርታይድ ጋር በመዋቅርና በግብ አንድ የሚያደርጉት ሦስት ዋና ዋና መሠረቶች አሉት፦

ሀ) መዋቅራዊ መሠረት (ዘርና ሃይማኖት)፦ የደቡብ አፍሪካው አፓርታይድ በቆዳ ቀለም ላይ እንደተመሠረተ ሁሉ፣ በአክሱም ያለው ሁኔታም ሃይማኖታዊ ማንነትን እንደ መለያ በመጠቀም ሙስሊሙን ማህበረሰብ "ሁለተኛ ዜጋ" የማድረግ ስልታዊ አካሄድ ነው።

ለ) ተቋማዊነቱ፦
📣📣📣📣📣

ይህ በደል በግለሰቦች ደረጃ ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን፣ ልክ እንደ አፓርታይድ ሁሉ ተቋማዊ ድጋፍ ያለው፣ በፖለቲካዊ ትርክቶች የታጀበ እና ዜጎችን ከይዞታና ከአምልኮ መብታቸው የሚያገል መዋቅር ነው። ምንም እንኳን በይፋ የወጣ "የአፓርታይድ ሕግ" ባይኖርም፣ በተግባር ግን በአስተዳደሩና በጸጥታ መዋቅሩ አማካኝነት ልክ እንደ ሕግ ተቆጥሮ ይተገበራል።

ሐ) የ«ባለቤት» እና «እንግዳ» ትርክት፦
💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢
አፓርታይድ ዜጎችን በዘራቸው ምክንያት የሀገር ባለቤትና ባዕድ አድርጎ እንደሚከፍለው ሁሉ፤ በአክሱም ያለው አስተሳሰብም አንዱን ሃይማኖት የታሪኩ ብቸኛ ባለቤት፣ ሌላውን ደግሞ «በቸርነት የሚኖር ስደተኛ» አድርጎ የመሳል ሥነ-ልቦናዊና ሕጋዊ ጫና ነው።

የአፓርታይድ ዋነኛ ግብ የአንድን ማህበረሰብ ማንነትና ድምፅ በማጥፋት የሌላኛውን ወገን ፍጹም የበላይነት ማረጋገጥ ነው። በአክሱም የሚታየውም "ሃይማኖታዊ አግላይነት" ይኸው ተመሳሳይ ግብ ያለው መዋቅራዊ በደል ነው።

ይህ ጽሑፍ እነዚህን ሁለት የጭቆና ሥርዓቶች ጎን ለጎን በማስቀመጥ፣ በአክሱም ምድር የነገሰውን ዝምታና መዋቅራዊ በደል በዝርዝር ይተነትናል።በትዕግስትና በጥሞና ሙሉ ጽሑፉን እንዲያነቡ እጋብዛለሁ። መልካም ንባብ።

1ኛ) "ለስላሳ አፓርታይድ"፦ ስውር ግን ውጤታማ
🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀
በደቡብ አፍሪካ የነበረው አፓርታይድ በግልጽ የወጡና ዓለም የሚያውቃቸው አግላይ ሕጎች ነበሩት፤ በአክሱም የሚታየው ግን "ለስላሳ አፓርታይድ" (Soft Apartheid) ተብሎ የሚገለጽ፣ በባህል፣ በፖሊሲና በትርክት ሽፋን ስር የተደበቀ ሥርዓት ነው። ይህ ዓይነቱ አፓርታይድ በግልጽ "ይህ የተከለከለ ነው" ከሚል ይፋዊ ሕግ ይልቅ፣ በተግባር ግን ሙስሊሙ ማህበረሰብ የሚጠይቃቸው መብቶች ሁሉ በቢሮክራሲያዊ ሰንሰለት እንዲታፈኑና መልስ እንዳያገኙ በማድረግ ይገለጻል።

ይህ አካሄድ በደሉን ለመሞገት አስቸጋሪ የሚያደርገው በሚዲያና በሕግ ሽፋን "ተቻችለን ነው የምንኖረው" የሚል የሐሰት ሽፋን ስለሚሰጠው ነው። ሆኖም ግን፣ ሙስሊሙ ዜጋ መስጂድ ለመሥራት ሲጠይቅ አንዴ «በአክሱም መስጊድ መሥራት አይቻልም» ሌላ ጊዜ ደግሞ "የሕብረተሰቡ ግንዛቤ እስኪሻሻል ድረስ መጠበቅ ያስፈልጋል»፥ «ይህን ጉዳይ ብትረሰት ይሻላል»፥ «ፈጽሞ የሚታሰብ አይደለም»፥«ጊዜው አይደለም» እና መሰል ሰበቦች እየተደረዱ ለዓመታት መጓተቱ፣ መቃብር ሲጠይቅ ደግሞ "ከአባቶች ሲተላለፍ የመጣው ባህል አይፈቅድም" መባሉ የዚሁ ስውር አፓርታይድ ውጤት ነው።

ለስላሳ አፓርታይድ ዜጎችን በአካላዊ ግድግዳ ከመለየት ይልቅ፣ በአስተሳሰብና በተቋማዊ አሠራር ግድግዳ በመለየት አንዱን ባለቤት ሌላውን ደግሞ በዝምታ እንዲጠፋ የተፈረደበት አካል ያደርገዋል። ይህ ስውርነት ደግሞ በደሉን ይበልጥ አደገኛና ተጠያቂነት የሌለው ያደርገዋል።

2ኛ) የቦታ ቁጥጥርና የይዞታ አፓርታይድ
🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺

በደቡብ አፍሪካ "Group Areas Act" የተባለው ሕግ ጥቁሮችን ከከተማ ማዕከላት በማፈናቀል ወደ ዳርቻዎችና ወደ መኖሪያ መንደሮች (Bantustans) ያገላቸው ነበር። በአክሱም የሚታየው ሁኔታም ከዚህ ጋር ቀጥተኛ ትይዩ አለው፤ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በከተማዋ ማዕከልም ሆነ በአጠቃላይ ከተማዋ ስፍራዎች መስጂድ የመሥራት መብቱ በይፋ ተከልክሏል። ይህ ጂኦግራፊያዊ መገለል አንዱን እምነት የቦታው ብቸኛ ጌታ፣ ሌላውን ደግሞ "የማይታይ ሰው" (Invisible Man) ለማድረግ የታለመ ስልታዊ እንቅስቃሴ ነው።

ከተማዋ በመቶዎች በሚቆጠሩ ሆቴሎች፣ መጠጥ ቤቶችና የንግድ ተቋማት ተሞልታ ሳለ፣ መስጂድ ግን "ከተማዋን ያረክሳል" በሚል ሰበብ መከልከሉ የቦታ የበላይነትን (Spatial Hegemony) ለማረጋገጥ የሚደረግ ጥረት ነው። መሬት እንደ ዜግነታዊ ሀብት ሳይሆን እንደ ሃይማኖታዊ ርስት ተቆጥሮ ለአንዱ ሲፈቀድ ለሌላው ይታገዳል፤ ይህ ደግሞ በደቡብ አፍሪካ ነጮች የመሬት ባለቤትነትን ለራሳቸው ብቻ ከወሰኑበት ፖሊሲ ጋር ተመሳሳይ የሆነ የቦታ አፓርታይድ ነው።

ሙስሊሙ በከተማዋ ቢኖርም እንኳ፣ በይዞታና በምልክት ደረጃ መኖሩ እንዳይታወቅ ይደረጋል፤ ይህም ዜጎችን ከከተማዋ የታሪክና የይዞታ ባለቤትነት የሚያገል መዋቅራዊ በደል ነው።

3ኛ) የሬሳ አፓርታይድ እና የሟቾች መገፋት
💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥

በደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ ወቅት መቃብሮችና የመቃብር ስፍራዎች በዘር የተከፋፈሉ (Cemetery Segregation) ነበሩ፤ በአክሱም ግን በደሉ ከዚህም የከፋ ደረጃ ላይ ደርሶ "የሬሳ አፓርታይድ" (Co**se Apartheid) ተብሎ ሊገለጽ ይችላል።

ሙስሊም ዜጎች በተወለዱበት፣ ባደጉበትና ግብር በከፈሉበት ከተማ የመቃብር ቦታ ተነፍገው አስክሬን ተሸክመው 40 ኪሎ ሜትር ርቆ ወደሚገኘው ውቅሮ-ማራይ ወደ ተባለ ስፍራ እንዲጓዙ መገደዳቸው እጅግ ዘግናኝ በደል ነው።

ይህ ክልከላ የሚመነጨው "የአክሱም ምድር በሙስሊም ሬሳ ትረክሳለች" ከሚል እጅግ አግላይና ጽንፈኛ ስነ-ልቦና ሲሆን፣ ይህም ዜግነትን እስከ መቃብር ድረስ በማንነት የሚከፋፍል ነው።
በከተማዋ ውስጥ የውሻና የአህያ አስክሬን የሚቀበርበት መሬት ባለበት ሁኔታ፣ ሙስሊም ዜጋ መቃብር ማጣቱ ዜጎችን ከእንስሳትም ያነሰ ደረጃ እንዲሰጣቸው መደረጉን ያረጋግጣል።

በከተማዋ ዉስጥ የሙስሊም መካነ መቃብር ስፍራ እንዳይኖር የነበረውም እንዳይታጠር መከልከሉና የቀብር ድንጋዮች በሌሊት እየተሰረቁ የቀብር ቦታው የእንስሳት መዋያ እንዲሆን መደረጉ፣ በሟቾች ላይ ጭምር በቀል የመውሰድ የአፓርታይድ ባህሪ ነው። ይህ ሁኔታ ዜጎች በገዛ አገራቸው ምድር ላይ እንኳ እንዲያርፉ የማይፈቅድ አረመኔያዊ መዋቅር መኖሩን ያሳያል።

4ኛ) የቃል ኪዳን ርዕዮተ-ዓለም፦ የ"ቅዱስ መሬት" ትርክት
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻

በደቡብ አፍሪካ የአፓርታይድ ሥርዓት እንዲገነባ መሠረት የሆነው አንዱና ዋነኛው ምሰሶ "የቃል ኪዳን ርዕዮተ-ዓለም" (Covenant Ideology) ነበር። አፍሪካነሮች (Afrikaners) በ17ኛው እና በ18ኛው ክፍለ ዘመን ወደ ደቡብ አፍሪካ የመጡ የደች፣ የጀርመን እና የፈረንሳይ ሰፋሪዎች ዘሮች ናቸው። እነዚህ «ቦሮች» (ገበሬዎች) በመባል የሚታወቁት ኃይሎች፣ ራሳቸውን በአምላክ እንደተመረጠ «አዲሱ የእስራኤል ሕዝብ» አድርገው ይስሉ ነበር። የዚህ ርዕዮተ-ዓለም መነሻ እ.ኤ.አ. በ1838 የተደረገው የ«ብለድ ሪቨር» ጦርነት ነው።

አፍሪካነሮች ከዙሉ ተዋጊዎች ጋር ከመገጠማቸው በፊት "ጦርነቱን ካሸነፍን ይህን ምድር እንደ ቅዱስ ምድር እናከብራለን" በሚል ከአምላክ ጋር ቃል ኪዳን እንደገቡ ያምናሉ። በጦርነቱ ድል ሲቀናቸው፣ ደቡብ አፍሪካን አምላክ የሰጣቸው «የቃል ኪዳን ምድር» (Canaan ) አድርገው በመቁጠር ሌላውን ወገን የማግለል መንፈሳዊና ፖለቲካዊ መሠረት ጣሉ።

ዛሬ በአክሱም ያለው አስተዳደርና የሃይማኖት ልሂቃንም ከተማዋን «የኦርቶዶክስ ብቻ» እና «ቅድስት» አድርገው በመሳል ሙስሊሙን ለማግለል ተመሳሳይ ርዕዮተ-ዓለም ይጠቀማሉ። በተለይም «ጽላተ ሙሴ ባለበት ከተማ መስጂድ አይሠራም»የሚለው መከራከሪያ፣ ቅድስናን ለሥርዓታዊ ኢ-ፍትሐዊነት እንደ መከላከያ ጋሻ የመጠቀም ስልታዊ አካሄድ ነው።

ይህ ትርክት አክሱምን ከኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት ውጭ የሆነች «የሃይማኖት መንግሥት» አስመስሎ የሚያቀርብ ሲሆን፣ ሙስሊሙን ደግሞ እንደ «መጤ» እና «እንግዳ» እንዲታይ ያደርገዋል። ቅድስና ለሰዎች መብት መከበሪያ መሆን ሲገባው፣ በአክሱም ግን ለስልታዊ ጂኦግራፊያዊ መገለል እንደ ሽፋን ሆኖ ያገለግላል።

ልክ አፍሪካነሮች መሬቱን የራሳቸው ብቻ እንደሆነና አምላካዊ ሥልጣን እንዳላቸው አምነው ሌላውን እንዳገለሉ ሁሉ፣ በአክሱምም መሬት እንደ ዜግነታዊ ሀብት ሳይሆን እንደ ሃይማኖታዊ ይዞታ ተቆጥሮ ለአንዱ ሲፈቀድ ለሌላው ይታገዳል። ይህ ርዕዮተ-ዓለም ጭቆናን «ቅዱስ ተግባር» በማስመሰል ሕዝቡን በሐሰት ትርክት እንዲታወር የሚያደርግ መዋቅራዊ በደል ነው።

5ኛ) መብትን መጠየቅን ወደ "ስጋት" የመለወጥ ስልታዊ ሂደት
🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒

የአፓርታይድ ሥርዓት ዋነኛ መገለጫ መሠረታዊ የሆኑ የመብት ጥያቄዎችን ወደ "የጸጥታ ስጋት" የመለወጥ ጥበብ (Reframing) ነው። ይህ ስልታዊ ውንጀላ ተጎጂውን ራሱ "ወንጀለኛ" በማድረግ ድምፁ እንዳይሰማ ያደርጋል።

የዚህ ስልት ትልቁ ታሪካዊ ማሳያ የኔልሰን ማንዴላ ክስና እስር ነው። ማንዴላና ጓደኞቹ በደቡብ አፍሪካ ለጥቁሮች እኩልነትና ለሰብዓዊ መብት መከበር በታገሉበት ወቅት፣ የአፓርታይድ ሥርዓት "ሽብርተኛ" እና "ኮሚኒስት" የሚሉ ታርጋዎችን በመለጠፍ ወንጀለኛ አድርጓቸዋል።

በታዋቂው የሪቮኒያ የፍርድ ሂደት (Rivonia Trial) ወቅት፣ ማንዴላ ክስ የቀረበበት "መንግሥትን በኃይል ለመገልበጥ በማሴር" እና "በሽብር ተግባር" ነበር። ዓላማው የእኩልነት ጥያቄውን ወደ "ሀገራዊ ስጋት" በመቀየር ማንዴላን ለ27 ዓመታት እንዲታሰር የሚያስችል ሕጋዊና ማኅበራዊ ቅቡልነት መፍጠር ነበር።
በአክሱም ሙስሊሞች ዘንድ የሚታየው እውነታም ከዚህ ጋር ተመሳሳይ ነው፦

ሀ) ከመብት ወደ ጽንፈኝነት፦ ሙስሊሞች መስጂድ እንዲገነባ ወይም ሂጃብ ለብሶ የመማር መብታቸው እንዲከበር ሲጠይቁ፣ ድርጊቱ ወዲያውኑ እንደ "ጽንፈኝነት" ወይም "ሰላም አደፈራሽነት" ተደርጎ ይሳላል።

ለ) ቅድስናን እንደ መከላከያ፦ "ሃይማኖታዊ መብቴ ይከበር" የሚለው ቀላል እውነት፣ በትርክት መሣሪያነት ተቀይሮ "የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ቅዱስ ስፍራ ለማርከስ የመጣ የባዕድ ወረራ" ተደርጎ እንዲታይ ይደረጋል።

ፍርሃትን በማዛመት አብሮ መኖርን ወደ ግጭት የመለወጥ ስልት፣ ለአፓርታይዳዊው መዋቅር ሕጋዊና ማህበራዊ ቅቡልነትን ይሰጠዋል። ልክ ማንዴላ እኩልነትን በመጠየቁ "ሽብርተኛ" ተብሎ እንደታሰረው ሁሉ፣ በአክሱምም ዜጎች መብታቸውን ሲጠይቁ እንደ ስጋት መቆጠራቸው በከተማዋ የሕግ የበላይነት ሳይሆን የማንነት ፖለቲካ የበላይነት መኖሩን ያረጋግጣል። ይህ ሂደት ሙስሊሙ ማህበረሰብ በድፍረት መብቱን እንዳይጠይቅ ስነ-ልቦናዊ አጥር በመፍጠር ጭቆናውን ያራዝመዋል።

6ኛ) የትምህርት አግላይነት እና የሂጃብ ክልከላ፦ የማንነት መደምሰሻ ስልት
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴

በደቡብ አፍሪካ "Bantu Educati
on Act" የተባለው ሕግ ጥቁሮች ዝቅተኛና የተገደበ ትምህርት ብቻ እንዲያገኙ በማድረግ፣ ለባርነትና ለአገልጋይነት እንዲዘጋጁ ይሠራ ነበር። በአክሱም የሚታየው የሂጃብ ክልከላም ተመሳሳይ ግብ ያለው የትምህርት አግላይነት (Educational Exclusion) ነው።

በአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ አድርጎ መማርን ተክልክለዋል። ከ150 በላይ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃብ በመልበሳቸው ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው ተባረዋል።የክልሉ እስልምና ጉዳዮች በፍርድ ቤት፥ የክልሉ መንግስትን በማነጋገር እንዲሁም ሰላማዊ ሰልፍ በመውጣት ጭምር መፍትሄ ፍለጋ ላይ ተግቷል። ሆኖም መፍትሄ ማምጣት አልተቻለም።

ዜጎችን በማንነታቸው ምክንያት ከዕውቀት ዓለም ለማግለል የታለመ ስልታዊ እርምጃ ነው። ይህ ክልከላ ተማሪዎቹን በሁለት አደገኛ አማራጮች መካከል እንዲወጠሩ ያደርጋቸዋል፦

ሀ) ማንነትን መገበር (Identity Loss)፦
🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁
ተማሪዎቹ እስላማዊ ማንነታቸውን አውልቀው ትምህርቱን ቢቀጥሉ፣ ሥርዓቱ የማንነት መደምሰስ ዓላማውን ያሳካል። ትምህርት ቤት የመብት መከበሪያ ሳይሆን ማንነትን አስረክቦ ዕውቀት የሚሸመትበት "የመገበሪያ መድረክ" ይሆናል።
ለ) በድንቁርና መታጠር (Systemic Marginalization)፦
🏠🏠🏠🏠🏠🏠🏠🏠🏠🏠🏠

ተማሪዎቹ ማንነታቸውን ላለማጣት ሲሉ ትምህርታቸውን አቋርጠው ቢወጡ ደግሞ፣ ያልተማሩና ያልነቁ ሆነው እንዲቀሩ ይገደዳሉ። መሃይምነት ደግሞ የሚፈጸምባቸውን መዋቅራዊ በደል የመጠየቅ፣ የመሞገትና መብታቸውን የማስከበር አቅም ያሳጣቸዋል።

በሁለቱም መንገድ ሥርዓቱ አሸናፊ ሆኖ ይወጣል። ተማሪዎቹ "ወይ ሂጃባችሁን አውልቁ ወይም አትማሩ" ተብለው በር ሲዘጋባቸው፣ ትምህርት እንደ መብት ሳይሆን እንደ ማኅበራዊ መቆጣጠሪያና የማንነት መደምሰሻ መሣሪያ ሆኖ እያገለገለ መሆኑን ያሳያል።

ሂጃብን እንደ "ፖለቲካዊ መሣሪያ" በመፈረጅ ተማሪዎችን ማዋከብ፣ ሙስሊሙ ማህበረሰብ መሃይም ሆኖ እንዲቀርና በወደፊቱ የከተማዋና የክልሉ ጉዳይ ላይ የመወሰን አቅም እንዳይኖረው ለማድረግ የሚከናወን መዋቅራዊ የአፓርታይድ ስልት ነው። ይህ እርምጃ ተማሪዎቹ በገዛ አገራቸው እንደ "መጤነት" እንዲሰማቸውና ስነ-ልቦናዊ ሞራላቸው እንዲሰበር የሚያደርግ አፓርታይዳዊ "የማንነት ጥቃት" ነው።

7ኛ) ተቋማዊ ወገንተኝነት፦ ሕግ ሳይሆን ሃይማኖት ሲነግሥ
🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮

በአፓርታይድ ሥርዓት ውስጥ የመንግሥት ተቋማት ገለልተኛ ሳይሆኑ ለአንዱ ወገን ብቻ የሚቆሙ መሣሪያዎች ናቸው። በአክሱም ከተማም የመንግሥት መዋቅር፣ የጸጥታ ኃይሎችና የሕግ ተርጓሚዎች ገለልተኝነታቸውን በማጣት የቤተ-ክህነትና የፅንፈኞች ረዳት ሆነው ይገኛሉ። የከተማው አስተዳደር "አክሱም ከሕግ በላይ ናት" በሚል ትርክት፣ የሀገሪቱን ሴኩላር ሕገ-መንግሥት ወደ ጎን በመገፍተር የሐይማኖት የበላይነትን አንግሷል።

ዜጎች መብታቸው ሲጣስ ጥበቃ ሊያደርግላቸው የሚገባው ፖሊስ፣ ራሱ በጁምዓ ሰላት ሰጋጆች ላይ ድብደባ ሲፈጽም፥ ቁርዓን ሲቀድና በርካታ የማዋከብ ተግባር ሲፈጽም በተደጋጋሚ ታይቷል። ይህ ተቋማዊ ወገንተኝነት ሕጉን ለአንዱ ወገን "ጋሻ" ለሌላው ግን "ጦር" በማድረግ ዜጎች በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ እምነት እንዳይኖራቸው ያደርጋል።

በደቡብ አፍሪካ እንደታየው ሁሉ፣ ተቋማዊ አድልዎ ጭቆናውን መደበኛ (Normalized) በማድረግ ዜጎች በገዛ አገራቸው ባይተዋር እንዲሆኑና መብታቸውን በልመና እንዲጠይቁ ያስገድዳል። ይህ መዋቅራዊ ወገንተኝነት በአክሱም ውስጥ "አፓርታይድ" በይፋ እንዲዘረጋ መዋቅራዊ ዋስትና ሰጥቷል።

8ኛ) የመንግሥት ድጋፍ ያለበት ጥቃት እና ተጠያቂነት ማጣት
♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦

በደቡብ አፍሪካ የነበረው የሻርፕቪል ጭፍጨፋና መሰል ጥቃቶች በመንግሥት ኃይሎች የሚፈጸሙና ተጠያቂነት የማይታይባቸው ነበሩ። በአክሱምም በጁምዓ ሰጋጆች ላይ የሚፈጸመው ድብደባና ወከባ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ቀጥተኛ ተሳትፎ የሚከናወን ነው።

በተለይም ሚያዚያ 2 ቀን 2018 ዓ.ል (2026) በከተማዋ የጸጥታ ምክትል ኃላፊ መሪነት የተፈጸመው ጥቃት፣ ተቋማዊ ጥበቃው ወደ ተቋማዊ ጥቃት መለወጡን ያረጋግጣል። ሰላማዊ ሰጋጆች በዱላና በድንጋይ ሲደበደቡና ስድስት ያህል ሰዎች ከባድ የአካል ጉዳት ሲደርስባቸው፣ በዚያው በአክሱም ስብሰባ እያደረገ የነበረው የሕወሃት ፓርቲ፥ በአክሱምም ሆነ በክልሉ ያለው መንግሥት ዝምታን መምረጣቸውና ጥቃቱን የፈጸሙ ኃላፊዎች ተጠያቂ አለመሆናቸው ድርጊቱ የመንግሥት ፖሊሲ አካል መሆኑን ያሳያል። ይህ "በሕግ የተደገፈ ግፍ" ዜጎች በሀገራቸው የደህንነት ስጋት እንዲሰማቸውና ድምፃቸውን እንዲያጠፉ ለማድረግ የሚከናወን የአፓርታይድ ስልት ነው። ተጠያቂነት በሌለበት ሁኔታ የሚፈጸም ጥቃት ደግሞ ፅንፈኛ ኃይሎች ይበልጥ እንዲደፋፈሩና ጭቆናውን እንዲያራዝሙ በር ይከፍታል።

9ኛ) መንፈሳዊ ማንነትን የመስበር ስልት
💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥

የደቡብ አፍሪካ አገዛዝ የጥቁሮችን ባህላዊ ምልክቶችና ማንነቶች በማጥፋት የበታችነት ስሜት እንዲሰማቸው ይሠራ ነበር። በአክሱምም የጸጥታ ኃይሎች ቅዱስ ቁርዓንን የመቅደድና የመበተን ተግባር መፈጸማቸው፣ ከአካላዊ ጥቃት ባለፈ የማህበረሰቡን መንፈሳዊ ማንነት ለመስበር የተነደፈ "Symbolic Violence" ነው።

የሙስሊሞችን ቅዱስ መጽሐፍን መቅደድና በመስገኛ ስፍራቸውና ቁሳቁሳቸው ማላገኝ ዜጎችን በማንነታቸው ለማንቋሸሽና ስነ-ልቦናዊ ጫና ለመፍጠር ታስቦ የሚከናወን ነው። ይህ ድርጊት ሙስሊሙን ማህበረሰብ "እሴቶቻችሁ እዚህ ቦታም ሆነ ዋጋ የላቸውም" የሚል መልእክት የሚያስተላልፍ ሲሆን፣ ይህም የአፓርታይድ ጭካኔ መገለጫ ነው።

ማንነትን በመስበር ዜጎች ለራሳቸው ያላቸውን ክብር እንዲያጡና በጭቆናው ፊት እንዲንበረከኩ ማድረግ የሥርዓቱ ዓላማ ነው። መንፈሳዊና ባህላዊ እሴቶች ሲረገጡ ዜጎች ያላቸውን የሀገር ባለቤትነት ስሜት ሙሉ በሙሉ እንዲያጡ ይደረጋል። ይህ ዓይነቱ ጥቃት በአክሱም ያለውን መዋቅራዊ አፓርታይድ ከማንኛውም ግጭት በላይ አደገኛና የሕሊና ቁስል የሚያስከትል ያደርገዋል።

10ኛ) የዜግነት ተዋረድ፦ ባለቤትና
❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌

አፓርታይድ ዜጎችን "ባለቤት" እና "አገልጋይ" አድርጎ በመክፈል፣ የጌታና የሎሌ ግንኙነት (Master-Servant Dynamic) ይፈጥራል።

በአክሱምም ሙስሊሙ ማህበረሰብ እንደ "እንግዳ" ወይም "መጤ" ተቆጥሮ መብቱን በቸርነት እንዲጠይቅ ይደረጋል። በኢትዮጵያ እንዳሉት የሶሪያ ስደተኞች በከተማ አስተዳደሩና በልሂቃኑ ለአክሱማውያን ሙስሊሞች "በአክሱም የምትኖሩት እኛ ፈቅደንላችሁ ነው" የሚለው የዘወትር ትርክት፣ ዜጎችን በባለቤትነትና በባዕድነት ይከፍላል። ይህ ስነ-ልቦናዊ ተዋረድ ሙስሊሙን ዜጋ በገዛ አገሩ ሁለተኛ ደረጃ ዜጋ በማድረግ፣ በከተማዋ ጉዳይ ላይ እኩል ድምፅ እንዳይኖረው ያደርጋል።

ልክ በደቡብ አፍሪካ ነጮች የመሬቱ ተፈጥሯዊ ባለቤቶች እንደሆኑና ጥቁሮች ግን በፈቃድ እንደሚኖሩ ተደርጎ እንደሚታሰበው ሁሉ፣ በአክሱምም ኦርቶዶክሳዊ ማንነት እንደ ብቸኛ የዜግነት መለኪያ ሆኖ ቀርቧል። ይህ ተዋረድ የዜግነትን ክብር የሚንድና ዜጎች ለሀገራቸው ያላቸውን ታማኝነት የሚሸረሽር የሞራል ክስረት ነው። ዜግነት በሐይማኖት ማንነት ሲለካ፣ ሕገ-መንግሥታዊው እኩልነት ዋጋ ያጣና አፓርታይዳዊው መዋቅር ይነግሣል።

11ኛ) የትርክት ቁጥጥር እና የሚዲያ ዝምታ
📷📷📷📷📷📷📷📷📷📷📷📷

የአፓርታይድ ስርዓት እውነታውን በመደበቅና የተሳሳተ ትርክት በማሰራጨት የሚታወቁ ሲሆን፣ በአክሱም የሚፈጸመው በደልም በሚዲያ ዝምታ የታጀበ ነው። የክልሉና የሀገሪቱ ሚዲያዎች ስለ አክሱም ሙስሊሞች መቃብርና መስጂድ መከልከል፣ እንዲሁም ስለሚፈጸሙ ጥቃቶች ዘገባ ከመሥራት ይልቅ ሆን ብለው ዝምታን መርጠዋል።

ይህ የትርክት ቁጥጥር (Narrative Control) እውነተኛውን ጭቆና ለማድበስበስና ጉዳዩ ከሳምንት አጀንዳነት እንዳያልፍ ተቀናጅቶ የመዳፈን አካሄድ ነው። ቤተ-ክህነት በደሉን እንደ "ታሪክና ባህል ጥበቃ" አድርጋ ስታቀርብ፣ ሚዲያው ደግሞ የተበዳዩን ድምፅ በማፈን ለጭቆናው ምቹ ሽፋን ይሰጣል።

ዝምታ ራሱ የጭቆና መሣሪያ ሆኖ እያገለገለ ሲሆን፣ ተበዳዩ ማህበረሰብ ደግሞ "የማይታይ ሰው" (Invisible Man) እንዲሆን ተፈርዶበታል። ይህ በትርክት ላይ የሚደረግ ጦርነት ዜጎች እውነታው ላይ እንዳይስማሙ በማድረግ፣ ፍትሕን እንዳይጠይቁ አቅማቸውን ያዳክማል።

12ኛ) የታሪክ መሰረዝ እና "መጤ" የማድረግ ሴራ
📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶

በደቡብ አፍሪካ የጥቁሮች የታሪክ ድርሻ ተደብቆና ተዛብቶ እንደሚቀርበው ሁሉ፣ በአክሱምም የሙስሊሙ ማህበረሰብ የታሪክ አሻራ ሆን ተብሎ እንዲደበዝዝ ይደረጋል። ሙስሊሙን ከየመን የመጣ ስደተኛ አድርጎ የመሳል ትርክት፣ ዜጎችን ከታሪካዊ ነባርነታቸው በመንቀል የባለቤትነት መብታቸውን ለመግፈፍ የሚደረግ ሴራ ነው።

ክርስትናና ኢስላም ከዉጭ በመጡ ስደተኞች ሲሰበኩ አክሱማውያን እንደተቀበሉ እንዲሁም አክሱም የእስልምናና የክርስትና እኩል መናገሻ መሆኗ እየታወቀ፣ እስልምናን ብቻ ነጥሎ እንደ አዲስ መጤ መቁጠር የአፓርታይድ ሎጂክ አካል ነው።

የታሪክ ድርሳናትና የመማሪያ መጻሕፍት ስለ አክሱም ሙስሊሞች መስዋዕትነትና ነባርነት ዝምታን እንዲመርጡ መደረጋቸው፣ የስልታዊ ማግለሉ አካል ነው። የታሪክ መሰረዝ (Erasure of History) ዜጎች በገዛ አገራቸው ታሪክ ውስጥ ውክልና እንዳይኖራቸው በማድረግ፣ ለዛሬው ጭቆና ታሪካዊ ሰበብ ለመፍጠር ይሠራል። ታሪክን በማጣመም ዜጎችን በማንነታቸው መፈረጅ፣ ለመዋቅራዊ አግላይነቱ ዋነኛው የአፓርታይዳዊ የርዕዮተ-ዓለም
መሸፈኛ ነው።
13ኛ) ድርብ መመዘኛ እና የ"መካ" ሰበብ
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥

የአፓርታይድ ሥርዓት አንዱ መለያ ባህሪ የሚሰነዘርበትን ትችት ለማምከን በደቡብ አፍሪካ የነበረው አፓርታይዳዊ አካሄድ "ሌሎች ሀገራትም ጋ እኮ ችግር አለ" የሚል የመከላከልና ትኩረት የማስቀየር ስልት (Diversionary Tactic) መጠቀም ነው።

በአክሱም የሚታየው "መካ ላይ ቤተክርስቲያን ከሌለ አክሱም ላይ መስጂድ አይሠራም" የሚለው መከራከሪያ የዚሁ የታወቀ ስልት ውጤት ነው። ይህ አካሄድ በሦስት ዋና ዋና ምክንያቶች የሞራልና የፖለቲካ ኪሳራ ነው፦

ሀ) የዜግነት ክብርን ከዲፕሎማሲ ጋር ማያያዝ፦
🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺
የኢትዮጵያ ዜጎችን መብት ከሌላ ሀገር (ለምሳሌ ከሳዑዲ ዓረቢያ) ፖሊሲ ወይም ዲፕሎማሲያዊ ድርድር ጋር ማያያዝ የዜግነት ክብርን የሚንድ ነው። የኢትዮጵያ ሙስሊሞች መብት መከበር ያለበት ኢትዮጵያዊ በመሆናቸውና ሕገ-መንግሥታዊ ዋስትና ስላላቸው እንጂ፣ በዓለም አቀፍ ድርድር የሚገኝ "የንግድ ዕቃ" (Commodity) አይደለም።

ለ) የ"ባዕድ ወኪል" ትርክት፦
🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀
ሙስሊሙን ማህበረሰብ ከውጭ ሀገራት ጋር አያይዞ እንደ "ባዕድ ወኪል" መሳል፣ ዜጎችን በስነ-ልቦና ደረጃ የመስበርና የማግለል የአፓርታይድ ስልት ነው። ዜግነትን በማንነት ደረጃ በመክፈል አንዱን "ታማኝ" ሌላውን ደግሞ "ተላላኪ" አድርጎ የመፈረጅ አደገኛ አካሄድ የሀገሪቱን አንድነትና የዜጎችን እኩልነት ከሥሩ ይበላዋል።

ሐ) ተግባራዊው ድርብ መመዘኛ፦
🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒

በኢትዮጵያ ሙስሊም ክልሎች (እንደ አፋርና ሱማሌ) በርካታ ቤተክርስቲያናት ሲገነቡና የክርስቲያኑ ማህበረሰብ መብት በሕግ ሲከበር፣ በአክሱም ግን ለሙስሊሞች ዝምታን መምረጥ ግልጽ ድርብ መመዘኛ (Double Standard) ነው።

መብትን እንደ ንግድ ዕቃ በማየት አንዱን ግፍ በሌላው ለመሸፈን መሞከር፣ ኢትዮጵያን ተበዳዮች በደል የሚቀያየሩባት "የግፍ ደሴት" (Island of Injustice) ያደርጋታል።

ባጭሩ፣ የዜጎችን እኩልነት በውጭ ሀገር ሰበብ መደራደሪያ ማድረግ የሞራል ክስረት ከመሆኑም በላይ፣ ዜግነትን በማንነት በመክፈል ሀገራዊ ሰላምን የሚንድ አደገኛ አካሄድ ነው። መብት የሚከበረው በሰውነትና በዜግነት እንጂ በዲፕሎማሲያዊ "መስጠትና መቀበል" ቀመር መሆን የለበትም።

14ኛ) የሕግ መራጭነት፦ ሕገ-መንግሥቱ እንደ «የወረቀት አንበሳ»
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴

በአክሱም ምድር የኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት ለሙስሊሙ ማህበረሰብ የማይሠራ፣ ጥርሱ የተሰበረ «የወረቀት አንበሳ» ብቻ ሆኖ ይገኛል። ሕግ ለሁሉም ዜጎች እኩል ጥበቃ መስጠት ሲገባው፣ በአክሱም ግን ለሃይማኖታዊ የበላይነት ሲባል ሕገ-መንግሥታዊው ሴኩላሪዝም (የመንግሥትና የሃይማኖት መለያየት) በይፋ ተጥሷል።

ሀ) የሕግ የበላይነት መፍረስ፦
🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒

የከተማዋ አስተዳደርና የጸጥታ መዋቅር ከሀገሪቱ የበላይ ሕግ ይልቅ ለፅንፈኛ ቡድኖች ግፊትና ለሃይማኖታዊ የበላይነት ስሜት ቅድሚያ መስጠታቸው፣ የሕግ የበላይነት (Rule of Law) መክሰሙን ያሳያል።

ለ) «መንግሥት በክልል ውስጥ መፈጠር»፦
📕📕📕📕📕📕📕📕📕📕📕📕

«አክሱም የራሷ ሕግ አላት» የሚለውና በዝምታ የጸደቀው ይፋዊ አቋም፣ ከተማዋን ከሀገሪቱ የሕግ ማዕቀፍ ውጭ በማድረግ ሙስሊሙን ዜጋ ለተቋማዊ ጥቃትና ለሕግ አልባነት አጋልጧል።
ይህ የሕግ መራጭነት (Legal Selectivity) በደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ ዘመን ከነበረው «Separate Amenities Act» (ዜጎችን በመገልገያ ቦታዎች የመለያ ሕግ) ጋር በእጅጉ ይመሳሰላል። ያ ሥርዓት ለአንዱ መብት ሰጪ፣ ለሌላው ግን ከልካይና ቀጥቃጭ እንደነበረው ሁሉ፤ በአክሱም ያለውም አሠራር አንዱን ሃይማኖት «ሕግ አውጪና ፈጻሚ»፣ ሌላውን ደግሞ «የሕግ ተገዢ ብቻ» አድርጎታል።

ዜጎች በገዛ ሀገራቸው ሕግ ተጠብቀው የመኖር ዋስትና ሲነፈጉ፣ ሥርዓቱ ከዴሞክራሲያዊነት ወደ አፓርታይድነት ይቀየራል። በአክሱም እየሆነ ያለውም ይኸው የመዋቅር ለውጥ ነው። ሕገ-መንግሥቱ መብትን ማስከበር ተስኖት «የወረቀት አንበሳ» ሆኖ በቆየ ቁጥር፣ የአፓርታይድ ቀንበር በዚያው ልክ እየጠነከረ ይሄዳል።

15ኛ) ተበዳዩን ወንጀለኛ የማድረግ ሂደት
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥

በደቡብ አፍሪካ በጥቃቱ ሰለባ የሆኑት ጥቁሮች "ቀስቃሽ" ተብለው እንደሚታሰሩት ሁሉ፣ በአክሱምም ድብደባ የደረሰባቸው ምዕመናን "ለምን ተደበደብን" በማለታቸው ብቻ "ሰላም አደፈራሽ" ተብለው ለእስር ይዳረጋሉ። የንጹሐን ሰለባዎችን ወንጀለኛ የማድረግ ሂደት (Victim Criminalization) ዓላማው ድምፃቸውን ማጥፋትና ለጭቆናው ሕጋዊ ሽፋን መስጠት ነው።

የጸጥታ ኃይሎች ጥቃት ፈጽመው ሳለ፣ ተጠያቂ የሚሆኑት ግን ተደባዳቢዎቹ ሳይሆኑ ተደበዳቢዎቹ ሙስሊሞች ናቸው። ይህ ሂደት ተቋማዊ ጥበቃው ወደ ተቋማዊ ጥቃት መለወጡን የሚያሳይ ሲሆን፣ ተበዳዩን የሁኔታው ፈጣሪ አድርጎ በመሳል ፍትሕን ያጠፋል።

ሙስሊም ተማሪዎች በሂጃብ ምክንያት ሲባረሩ ጥፋተኛው ተማሪዎቹ እንደሆኑ ተደርጎ መቅረቡ የዚሁ ስርአታዊ አድልዎ ማሳያ ነው። ተበዳዩን ወንጀለኛ ማድረግ በጭቆናው መዋቅር ውስጥ የመጨረሻው የውርደትና የፍትሕ አልባነት ደረጃ ነው።

«ክርስቲያናዊ አፓርታይድ» በአክሱምን በስሙ መጥራት
💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢

በአክሱም ከተማ የሚታየው «ለስላሳ አፓርታይድ» በአጋጣሚ የሚከሰት ግጭት ሳይሆን፤ በአክሱም ቤተ-ክህነት ድጋፍ፣ በትረክት ሴራ እና በመንግሥት ወገንተኝነት ላይ የቆመ መዋቅራዊ አግላይነት ነው። የዚህ መዋቅር ዋነኛ ግብ የክርስትናን የበላይነት (Hegemony) ማስጠበቅ ሲሆን፣ መላዋን ከተማ እንደ «ገዳም» አድርጎ የመሳል ትርክት ለዚህ ግብ እንደ ዋነኛ መሣሪያ ያገለግላል።

በዚህ ሂደት ውስጥ የሚከተሉት ነጥቦች በግልጽ ሊታዩ ይገባል፦

ሀ) በአክሱም ሙስሊሞች ላይ የሚፈጸመውን በደል የሚከላከሉት፣ መግለጫ የሚሰጡትና ግፉን የሚያጸኑት፤ ራሳቸውን «የአባ ሰላማ መንበር» በሚል ስያሜ ያደራጁ ቀሳውስትና የሃይማኖቱ ልሂቃን ናቸው። ይህ መንበር ክርስትናን ለመጀመሪያ ጊዜ በአክሱም በሰበኩት በሶሪያዊው ስደተኛና መጤ - በአባ ሰላማ (ፍሬምናጦስ) -ስም የተሰየመ ነው። ስለሆነም «የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በአክሱም ሙስሊሞች ላይ እየተፈጸመ ያለውን ክርስቲያናዊ አፓርታይድ ጉዳይ ከዚህ መዋቅር ነፃ ናት ወይስ የአፓርታይዱ አካል?» የሚለው ጥያቄ ምላሽ ይሻል።

ለ) ቤተክርስቲያኗ በአክሱም ሙስሊሞች ላይ ለሚደርሰው አፓርታይዳዊ ጭቆና «እጄ የለበትም፤ አይመለከተኝም» ብላ ራሷን አለማግለሏ፣ እንዲሁም ለሚደርሰው ጥቃት ከማውገዝ ይልቅ ዝምታን መምረጧ(መጅሊስ በክርስቲያን ወገኖቻችን ላይ የሚደርሰውን ጥቃት በተደጋጋሚ በመግለጫ እያወገዘ ጭምር) ፥ ድርጊቱን ደግፈው የሚቆሙ ልጆችዋን አለመገሰጽዋ ከወቀሳ ባያድናትም፤ ለጊዜው ጉዳዩ እስኪጠራ ድረስ «ክርስቲያናዊ አፓርታይድ» የሚለውን ቃል መርጫለሁ።

የመላው ቤተክርስቲያኗ መዋቅር የዚህ አግላይነት ባለቤት መሆኑ በተረጋገጠ ጊዜ ግን ስያሜው ወደ «የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አፓርታይድ በአክሱም» ይቀየራል።

ችግሩን ለመፍታት በየዘመናቱ ከሚደረገው «የሙስሊሞች ተወካዮች ከክልሉ መንግስት አመራር ጋር ተወያዩ፣ ለመፍትሔም በጋራ እንደሚሰሩ ገለጹ» ከሚል የተደጋገመ ማደንዘዣ (ማስተኛ) ንግግርና ዜና ሳይታለሉ እንዲሁም ከጊዜያዊ «እሳት ማጥፋት» ሥራ ወጥቶ፣ ለጭቆናው መፈልፈያ የሆኑትን ጥልቅ አስተሳሰቦችና መዋቅራዊ እንቅፋቶች ኢላማ አድርጎ መታገል ያስፈልጋል። መፍትሔው አክሱምን ከአፓርታይዳዊ አሠራር አላቆ፣ ወደ ሀገሪቱ ሕገ-መንግሥታዊና ዓለማዊ (ሴኩላር) ሥርዓት መመለስና የዜጎችን እኩልነት በተግባር ማረጋገጥ ነው።

በአክሱምም በደቡብ አፍሪካ እንደታየው ሁሉ፣ የአፓርታይድ አጥሮች ፈርሰውና ጭቆናው ቆሞ ሙሉ ዜግነትና ሙሉ መብት ሊረጋገጥ ይገባል። ለዚህም የችግሩን ጥልቀት ተረድቶ፣ በአክሱም የሰፈነውን «ክርስቲያናዊ አፓርታይድ» በስሙ በመጥራት አፓርታይዳዊ ሥርዓቱን መታገል ግድ ይላል። ቸር እንሰንበት። መልካም እለተ ጁምዓ።

የሳዑዲ ዐረቢያ የሥነ ፈለክ ባለሞያዎች ቀጣዩ የሸዋል ወር ጨረቃ መታየት አልያም አለመታየቱን ለማረጋገጥ ረቡዕ ረመዳን 29/1447 ለፍለጋ እንደሚሠማሩ ኢንሳይድ ሐረመይን ዘግቧል። በዚህም መ...
16/03/2026

የሳዑዲ ዐረቢያ የሥነ ፈለክ ባለሞያዎች ቀጣዩ የሸዋል ወር ጨረቃ መታየት አልያም አለመታየቱን ለማረጋገጥ ረቡዕ ረመዳን 29/1447 ለፍለጋ እንደሚሠማሩ ኢንሳይድ ሐረመይን ዘግቧል። በዚህም መሠረት በዕለቱ ጨረቃ የሚታይ ከሆነ የዒድ አል ፊጥር በዓል ሐሙስ መጋቢት 10/2018 ይከበራል። መታየት ካልቻለ ደግሞ የረመዳን ወር ሐሙስ በሠላሳኛው ቀን ተጠናቆ በማግሥቱ ጁመዓ መጋቢት 11/2018 በዓሉ ይከበራል።

14/02/2026

የሲርለና በጎ አድራጎት ድርጅት ለ1 ሺህ ቤተሰቦች የረመዳን የአስቤዛ ድጋፍ አበረከተ!

- የካቲት 7 ቀን 2018 ዓ.ል

የሲርለና የበጎ አድራጎት ድርጅት የታላቁን የረመዳን ወር ፆምን በማስመልከት፣ በተለያየ ምክንያት በችግር ውስጥ ለሚገኙ 1,000 ቤተሰቦች የአስቤዛ ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ።

በኡስታዝ ኑሩ ቱርኪ የሚመራው ይህ ድርጅት ድጋፉን ሊያበረክት የቻለው፣ በቅርቡ በማኅበራዊ ሚዲያ (በተለይም በቲክቶክ) ለአራት ቀናት ባካሄደው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብር አማካኝነት መሆኑ ተገልጿል።

በዕለቱ ድጋፍ ከተደረገላቸው ወገኖች መካከል 315 የሚሆኑት የክርስትና እምነት ተከታዮች መሆናቸውንም ኡስታዝ ኑሩ ቱርኪ ገልጸው፤ ለዚሁ በጎ ተግባር ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት ወላጅ አልባ ሕፃናትን (የቲሞችን)፣ አረጋውያንን፣ ምስኪኖችንና ለችግር ተጋላጭ የሆኑ ወገኖችን ጨምሮ በቀጥታ ድጋፍ የሚያደርግላቸው ቤተሰቦች ቁጥር 1,700 መድረሱ ታውቋል።

የሲርለና በአሁኑ ወቅት ሥራዎቹን እያከናወነ የሚገኘው በኪራይ ቤት ውስጥ በመሆኑ፣ የሚመለከተው የመንግሥት አካል ድርጅቱ የሚሠራቸውን ዘርፈ-ብዙ የበጎ አድራጎት ተግባራት ከግምት ውስጥ በማስገባት ቋሚ የሆነ የመሥሪያ ቦታ እንዲሰጠው ጥሪ ቀርቧል።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251905586634

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AFZAN MEDIA /አፍዛን ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to AFZAN MEDIA /አፍዛን ሚዲያ:

Shortcuts

Share