የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብርሃን ለዓለም ሲያበራ፡፡

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብርሃን ለዓለም ሲያበራ፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብርሃን ለዓለም ሲያበራ፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብርሃን ለዓለም ሲያበራ፡፡

28/01/2023

ዲዮቅልጢያኖስን ያስቀና የ21ኛው ክፍለ ዘመን አህዛብ።

ንፁሃን እንደ በግ እየታረዱ ድረስ ሲባል "አልታዘዝኩም" የሚያስብለው መንግስት መነኩሳትን ለማስለቀስ ብርታቱን ከየት አገኘው? በታሪክ ማህደር ሰፍሯል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናን ቀኝህን ሲመታህ ግራህን ስጥ፤ ጠላትህን እንደራስህ አድርገህ ውደድ የሚለው ዶግማዊ አስተምህሮ የመጨረሻው ቀይ መስመር ተጥሷል።

NB፦ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ።

28/01/2023
24/01/2023

"የኖላዊነት ኃላፊነታችሁን የዘነጋችሁ ወንድሞቻችን እና ሌሎችም ሰዓቱ ከማለቁ አስቀድሞ ወደ ልባችሁ በመመለስ ወደ ቀድሞው ማንነታችሁ ተመለሱ" ብፁዐ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ ዘአዲስ አበባ

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል የበላይ ጠበቂ በትናንትናው ዕለት በተፈፀመው ኢ-ቀኖናዊ "ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳትን" አስመልክቶ በይፋዊ የፌስቡክ ገጻቸው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

እውነት እውነት እላችኋለሁ ወደ በጎች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚወጣ እርሱ ሌባ ወንበዴም ነው (ዮሐንስ 10፥1) በሚል የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል መልዕክታቸውን የጀመሩት ብፁዕነታቸው በትናንትናው ዕለት በወሊሶ በተፈጸአው ኢ-ቀኖናዊ "ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት" ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በእጅጉ አዝናለች ብለዋል።

መከራና ፈተና ከቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ተለይተው የማያውቁ ቢሆንም ካለን መከራንና ችግርን የማለፍ ልምድ በመማር ይህንን አስቸጋሪ እና ፈታኝ ወቅት በጥበብ እና ብስለት በተመላበት አኳኋን ልናሳልፈው ይገባል አሉት ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ

ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ ብዙ መናገር ቢቻልም ያለንበት ወቅት ይህንን ለመናገር ጊዜው ባለመሆኑ ምዕመናን ልጆቻችን ሁሉ ለቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ አፈጻጸም ራሳችሁን ዝግጁ በማድረግ ፤ መንፈስ ቅዱስ እና ቅዱስ ሲኖዶስ የሚወስኑትን ውሳኔ በትዕግስት እንድትጠብቁ እናሳስባለን ብለዋል።

ብፁዕነታቸው አቡነ ሄኖክ በዚህ ስህተት ውስጥ የገባችሁ የኖላዊነት ኃላፊነታችሁን የዘነጋችሁ ወንድሞቻችን እና ሌሎችም ሰዓቱ ከማለቁ አስቀድሞ ወደ ልባችሁ ተመልሳችሁ ወደ ቀድሞው ማንነታችሁ ትመለሱ ዘንድ ጸሎታችን መሆኑን እንገልጻለን ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል ።

24/01/2023

‹‹ሥጋን የሚገድሉትን በ ኋላም አንድ ስንኳ የሚበልጥ ሊያደርጉ የማይችሉትን አትፍሩ›› ሉቃ 12፡4

22/01/2023

የኢትዮጵያውያን ገመድ ለመበጠስ ታቅዶበት የሚሰራበት እንጅ ጉዳዩ ኃይማኖታዊ እንዳልሆነ ግልፅ ነው።

ስልጣን ላይ ያሉት አካላት የፖለቲካ ስልጣን በመጠቀም ኢኮኖሚውን በቡድን አጋብሰው እምነትን እንኳን መሳርያ በማድረግ ለአሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን እንኳን ያልተመለሱ የእፉኝት ልጆች መሆናቸውን በራሳቸው አውጀውታል፤ እመኑኝ የምትፀፀቱበት ቀን ቅርብ ነው።

አንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ።
አንድ ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ።
አንድ መንበር፤ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት።


NB፦ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ።

Address

Addis Ababa
776CODENO1110

Telephone

+251912057421

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብርሃን ለዓለም ሲያበራ፡፡ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብርሃን ለዓለም ሲያበራ፡፡:

Share