Mahibere Medhanealem Ze-Horro/ማኅበረ መድኃኔዓለም ዘ-ሆሮ

Mahibere Medhanealem Ze-Horro/ማኅበረ መድኃኔዓለም ዘ-ሆሮ It is Ethiopian Orthodox Tewahido religious organization from Horro Guduru Wollega Shambu.

አሳዛኝ ዜናየሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ በሕገ ወጥ ታጣቂዎች ተገደሉ።የኅዳር  ጽዮን ማርያምን በዓል በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሥር በምትገኘው በሐረቶ ማርያም በ...
14/12/2025

አሳዛኝ ዜና

የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ በሕገ ወጥ ታጣቂዎች ተገደሉ።

የኅዳር ጽዮን ማርያምን በዓል በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሥር በምትገኘው በሐረቶ ማርያም በዓሉን አክብረው ሲመለሱ ሻምቡ ከተማ መዳረሻ ሲደርሱ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ ኡፋ እና በርካታ የሀገረ ስብከቱ ሠራተኞችና ወጣት የማኅበራት አገልጋዮች በሕገ ወጥ ታጣቂዎች ተወስደው የቆዩ ሲሆን ሌሎቹ ተፈትተው ቆይተው ወደ ቤተሰቦቻቸው የተመለሱ ሲሆን በትናንትናው ዕለት የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ ኡፋ እና ቀሲስ ደሳለኝ ነሞምሳ በሕገ ወጥ ታጣቂዎች መገደላቸው ተገልጿል::

ማኅበራችን ማኅበረ መድኃኔዓለም ዘሆሮ በመልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ ኡፋ እና በቀሲስ ደሳለኝ ነሞምሳ ሕልፈት የተሰማውን ጥልቅ ኃዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቻቸው ፣ለዘመዶቻቸው እንደ‍ሁም ለሃገረ ስብከቱ ምእመናን መጽናናትን ይመኛል::

ODUU GADDAAHojii Gaggeessaa biyya Lallaba Horro Guduruu Wallaggaa hidhattoota see-rmaleessaan ajjeefaman.Ayyaana Maariya...
14/12/2025

ODUU GADDAA

Hojii Gaggeessaa biyya Lallaba Horro Guduruu Wallaggaa hidhattoota see-rmaleessaan ajjeefaman.

Ayyaana Maariyaamii Tsiyoon ji'a Sadaasa Mana kiristaanaa Haaratoo Maariyaamii biyya Lallaba Horro Guduruu Wallaggaatti kabajanii yeroo deebi'an dhiyeenya Magaalaa Shaambutti E/Eedoom L/Dhugumaa fi hojjattootaa biyya Lallabichaa heddu fi dargaggoota tajaajiltoota waldolee hidhattoota see-rmaleessaan fudhatamanii kan turan yoo ta'u, baay'een isaanii gadhiifamanii gara maatii isaanitti kan deebi'ani yeroo ta’u guyyaa kaleessa Hojii gaggeessaan biyya lallabichaa E/Eedoom L/Dhugumaa Ufaa fi Lubni Dassaaleny Namoomsaa humna kanaan ajjeeffamuun ibsameera.

Waldaan keenya waldaa Madhaanee’aalam ZaHorroo lubbuun darbuu Luboota kanaatti gadda guddaa 'n itti dhaga'amuu isaa ibsaa, maatii, hiriyoota fi firootaa isaanii hundaaf akkasumas uummata biyya lallaba Horro Guduruu Maraaf jajjabina hawwa.

23/11/2025
አመታዊ ጉባኤያችንን በዚህ መልኩ!!!
21/11/2025

አመታዊ ጉባኤያችንን በዚህ መልኩ!!!

03/11/2025

Maqaa Abbaa maqaa Ilmaa maqaa Afuura Qulqullu waaqa tokko amen!

Akkam jirtu maatii waaqayyoo, yaa’iin waggaa haawiidhaan eegnu Kunoo kabajamuuf torban muraasatu haafe. Guyyaa kanattiis barsiisootaa fi faarfattoota jaallatamoota kan affeeraman yaroo ta’u kessummaa guddaa waggaa Kanaas ni qabaanna. Kanaafuu, guyyaa kanaaf gamanumaa qophii akka gootan maqaa waaqaatiin isin beeksisna.

Guyyaa 07/03/2018 Sanbata
Iddoo Wingeet bira Pheexiros Waphaawulos
Sa’aatii 5:00

በስምአብ ወወልድ ወመነፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን!

እንደምን አላችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች በናፍቆት የሚጠበቀው አመታዊ ጉባኤ እነሆ ጥቂት ሳምንታት ብቻ ቀርተውታል። በእለቱም ሰባክያንና ዘማርያን የሚጋበዙ ሲሆን የአመቱ ልዩ እንግዳም ይኖረናል። ስለሆነም ሁላችሁም በዕለቱ በመገኘት ከፕሮግራሙ በረከት እንድታገኙ ከወዲሁ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።

ቀን 07/03/2018 እሁድ
ቦታው ዊንጌት ዼጥሮስ ወዻውሎስ ቤተ ክርስቲያን
ሰዓት 5:00

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን!!!“ሰቀላ ቅዱስ ሚካኤል ይጣራል”እንደምን ሰነበታችሁ እናንት ደጋግ የአግዚአብሔርን ቤት እንደ ንጉስ ዳዊት ያይደለ እንደ ጠቢቡ ሰለሞን...
05/05/2025

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን!!!

“ሰቀላ ቅዱስ ሚካኤል ይጣራል”

እንደምን ሰነበታችሁ እናንት ደጋግ የአግዚአብሔርን ቤት እንደ ንጉስ ዳዊት ያይደለ እንደ ጠቢቡ ሰለሞን ለመስራት የተፈቀደላችሁ አባላቶቻችን፤
አሁን እንድንሰራ የሚጠበቅብን/የሚጠብቀን ቤተ ክርስቲያን በመናፍቃንና በኢአማንያን ተከባ ያለች ቤተክርስቲያን፣ ምዕመኗ ኢኮኖሚውም ሆነ የሃይማኖቱ ጥንካሬ ብቻውን ህንፃ ቤተ ክርስቲያኗን ሰርቶ ያጠናቅቃል ተብሎ የማይታሰብ ቤተ ክርስቲያን ናት።

ሰቀላ ቅዱስ ሚካኤል፤ ነባሩ ቤተ ክርስቲያን እንደምታዩት ረጅም ጊዜ ያስቆጠረና በእድሜ ብዛት ግድግዳው የሚንቀሳቀስ፣ ጣርያው የሚያፈስና ለዘመናችንም የማይመጥን በመሆኑ “የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል እኛም በርያዎቹ ተነስተን እንሰራለን” እንዳለ ነኸምያ የአካባቢው ምእመን መድኃኔዓለምን ተስፋ በማድረግ ተነስተው አፍርሰውታል።

የሰቀላ ሚካኤል አባቶች ድጋፍ ከጠየቁ ወራት ያለፉት ቢሆንም አንዳንድ ችግሮች ስለነበሩ እስኪስተካከል እየጠበቅንና በማስተካከሉ ሂደትም ማኅበራችን ተሳትፎ እያደረገ የነበረ ሲሆን ችግሩም እየተቀረፈ ይገኛል። ስለሆነም እንቅስቃሴ ተጀምሯል፤ ፕላን አላቸው፤ በእነርሱ አቅም መሰረትም ወጥቷል፤ እስከ ቶፕ ቢም ድረስ የሚያስፈልገው ታውቋል፤ ለግንባታው የሚያስፈልገው ሙሉውን ብረት እሸፍናለው ብሎ ቃል የገባ ያለ ሲሆን ሌሎች ግን ማለትም፣

***ሲሚንቶ 260 ኩንታል
***አሸዋ 4 ቢያጆ
***ኮረት 4 ቢያጆ
***ብሎኬት 4000 ፍሬ
***ባለሙያ 170,000 ብር የሚያስፈልጋቸው መሆኑን በደብዳቤ ገልፀውልናል።

እኛስ ምን ማድረግ እንችላለን? መቼስ ይሄንን ማኅበርና አባላቱን በጠቅላላ ቅዱስ ሚካኤል እንዴት እየባረከው እንደሆነ፤ ልብ አድርጉ ልብ አምላክ ለተባለው ዳዊት ያልተፈቀደውን ነው እኛ እንድንሰራ እየተጠየቅን ያለነው።

እንግዲህ በቁጭት እንነሳ!!! የኛ ሃገረ ስብከት በአገልግሎት 45ኛ መሆኑን ስንቶቻችን እናውቃለን? ከ45 ሃገረ ስብከት ነው ልብ በሉ። ይሄ በኛ ዘመን መሆኑ አያስቆጭም ትላላችሁ?
በሆሮ ቡሉቅ ውስጥ ደግሞ እግዚአብሔር የሚመለክባቸው እና ህዝቡ የሚባረክባቸው ቦታዎች ሰቀላ ቅዱስ ሚካኤልና ፎቃ ቅድስት ማርያም ብቻ ናቸው፤ ይሄም ይነዳል በውነት።

በሉ አሁን ልክ ለመንበር ቅዱስ ሚካኤል እንደተረባረብነው ሁሉ ለሰቀላ ቅዱስ ሚካኤልም እንሯሯጥ፤ በረከትን ለሰው ከማካፈል አንቆጠብ፤ መረጃውን ለሰው ባደረስን ቁጥር በረከትን እያካፈልንና እያስባረክናቸው ነውና ያለመሳቀቅ እናዳርስ። ከኛ የሚጠበቀው ላልሰማ ማሰማት ብቻ ነው ሌላው የቅዱስ ሚካኤል ስራ ነው
“ተባርካችሁ ሰው አስባርኩ”

Maqaa Abbaa Maqaa Ilmaa Maqaa Afuura qulqulluu Waaqa tokko Amen!!!“QULQULLUU MIKAA’EELIIN SAQALAA NU WAAMA”Akkam jirtuu ...
05/05/2025

Maqaa Abbaa Maqaa Ilmaa Maqaa Afuura qulqulluu Waaqa tokko Amen!!!

“QULQULLUU MIKAA’EELIIN SAQALAA NU WAAMA”

Akkam jirtuu miseensoota akkaa Daawwiit otoo hin taane akka Solomon mana Waaqayyoo akka ijaartan kan isiiniif eeyyamame, manni kiristaanaa amma akka kan nurraa eegamu/kan nu eegu amantaa biraa fi namoota amantii hin qabneen marsamtee kan jirtu, uummatni naannoo sana jiru iikoonoomiinis ta’e beekumsi aamantii isaan qaban gamoo mana kiristaanaa kana hojjeetanii xumuru jedhamee kan hin yaadamne dha.

Saqalaa Qulqulluu Mikaa’eeliin, mani kiristaanaa duraanii akka argaa jirtan yeroo baay’ee kan turee ta’uu isaan walqabatee yeroo itti hirkatan kan socho’uu, xaaraan isaas kan dhim’isu fi bara kanaaf illee kan hin taane waan ta’eef akka Nahamiyaan “Waaqni samii irraa nuuf xumuraatii nuti kaane nii hojjennaa” jedhetti uummatni naannoo sanaa Madaanaalamii andatanii diiganiiru.

Abbooliin Qulqulluu Saqalaa Miikaa’eelii deeggarsa eerga gaafatanii ji’oottan muraasa kan darbe ta’uus rakkoon tokko tokko waan turaniif hanga sirraa’uutti kan eegaa turree fi adeemsa sirreessuu irrattis waldaan keenya hirmaachaa kan turee ta’ee amma rakkoon isaa sirraa’aa jira. Kanaafuu sochiin jalqbqmee jira. Pilaanii qabu, gamoos jalqabanii jiru, miini haanga TOP BIIMIItii barbaachisus barameera, feerroon gamichaaf barbaachisus guutuun isaa nama tokkoon akka bitamus waadaan galameeraafi.
Warreen biroo akka;

***Simiintoo Kuntaala 260
***Ashawaa Baajoo 4
***Korota Baajoo 4
***Bilookeettii 4000
***Ogeessaaf 170,000 kan barbaachisu ta’uu isaa xalayaadhaan nuu ibsaniiru.

Nutoo maal gochuu dandeenya? Qulqulluun Miikaa’eel waldaa fi miseensicha akka eebbisaa jiru hundi keenya ilaalaa jirra. Qalbeeffadhaa, kuni Daawwit abbaa keenyaaf illee kan hin eeyyamamnetu nuti akka hojjennu kan gaafatamaa jirru.

Egaa gaabbiidhaan haa kaanu!!! Naannoo keenyi tajaajilaan 45ffaa ta’uu isaa eenyutu beekaa laata? Isayyuu 45 keessaadhammooti. Kuni bara keenyatti ta’uusaa yeroo yaadnu nama hin ciquu?
Horro bulluq keessaa immoo tajaajilli mana amantaa kan geggeeffamu Qulqulluu Mikaa’eelii Saqalaa fi qulqulleettii Maariyaamii Fooqaa duwwaa dha, kunis nama aarsa mitiiree?

Jedhaa amma akkuma Qulqulluu Mikaa’eelii manbariif birmanneetti Qulqulluu Mikaa’eelii Saqalaafiis haa kaanu, namaafis sharii gochuu irraa of hin qusatiinaa, yeroo namaan bira geenyu namni eebba waan argatuuf ni birmata kan nurraa eegmu odeeffannoo isaanii bira geesissuu duwwaa dha. Kanaafuu haafe hojii Mikaa’eelii ti.
“EBBIFAMAATII NAMA EEBBISIISAA”

Yaa’iin ji’aa waldaa keenyaa akkanaan geggeeffamaa jira.የማኅበሩ ወርሃዊ ጉባኤ በዚህ መልኩ እየተካሄደ ይገኛል።
04/05/2025

Yaa’iin ji’aa waldaa keenyaa akkanaan geggeeffamaa jira.

የማኅበሩ ወርሃዊ ጉባኤ በዚህ መልኩ እየተካሄደ ይገኛል።

እንኳን ደስስስ አላችሁ!!!“ሁለት መቶ ሺ ትንሽ መሆኑን አሁን አወቅን”ለካስ በህብረት ምንም ማድረግ ቀላል ነው!? ለካስ በመተባበር የማይገፋ የሚመስለው ዳገት ይናዳል!? ለካስ አንድነት ትል...
02/05/2025

እንኳን ደስስስ አላችሁ!!!

“ሁለት መቶ ሺ ትንሽ መሆኑን አሁን አወቅን”

ለካስ በህብረት ምንም ማድረግ ቀላል ነው!? ለካስ በመተባበር የማይገፋ የሚመስለው ዳገት ይናዳል!? ለካስ አንድነት ትልቅ ሃይል ነው!? ይገርማል. . .

አባቶቻችን ይህን ድጋፍ ሲጠይቁን፣ ከጉዳዩ አሳሳቢነትና አስቸኳይነት አንጻር ‘የተወሰነውን ብናገኝ ቀሪውን እናስብበታለን የሆነው ሆኖ ግን ሙሉውን ቆርቆሮ ማኅበሩ መሸፈን አለበት’ በሚል አቋም የገቢ ማሰባሰብያውን በጀመርን ማግስት መድኃኔዓለምን ተስፋ በማድረግ ለሰበካ ጉባኤዎች ይህንኑ አሳወቅን። እነሱርም ጨንቋቸው ኖሯል እረፍት የተሰማቸው በሚመስል ሁናቴ ደስታቸውን በምርቃት ገለጹ፤ “ልጆቻችን ተባረኩልን፣ ኑሩልን፣ ማኅበራችዉን ያስፋው፣ ተስፋችን ናቸ‍እሁ እንደማታሳፍሩን እናውቅ ነበር” ሲሉ

ግን ደግሞ ምን ተፈጠረ? ተአምር!!

እናንተ መልካም ሰዎች፣ እናንተ ለኛ ለዛሬ ኩራት ለነገ ተስፋ የሆናችሁ አባላቶቻችን መጣችሁና ታሪኩን ቀየራችሁት። “የቅዱስ ሚካኤል ጣርያ ክፍት ሆኖ የክርስቶስ ስጋና ደም የተፈተተበት ቦታ ዝናብ እና ፀሐይ እየተፈራረቀበት እንደምን በተደላደለ ቤትና አልጋ መተኛት ይቻለናል?” ስትሉ ብድግ አላችኋ።

ይሄ በእውነት ለኛ ከቃላት በላይ ነው በምን ቋንቋ እንኳ እንደምናመሰግናችሁ አናውቅም። ምንም እንኳ በረከቱ ከቅዱስ ሚካኤል ቢሆንም እኛን አምናችሁ የዛ አካባቢ ችግር የኛም ችግር ነው ብላችሁ ጥሪ ስናደርግ “ሆ” ብላችሁ ስለተረባረባችሁ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የሚፈለገው ብር ሞልቶ ክፍያውን ፈፅመን ቆርቆሮው በዚህ መልኩ ግዢ ተከናውኖ 200 ቆርቆሮ ተረክበዋል።

እንግዲህ ምን እንላለን? ቅዱስ እግዚአብሔር ለሰጣችሁ ሁሉ ረድኤት በረከቱን በቤታችሁ፣ በህይወታችሁ፣ በትዳራችሁ፣ በልጆቻችሁ፣ በስራችሁ፣ በኑሯችሁ ሁሉ ያትረፍርፍላችሁ። ይልቁንም የሰው መጨረሻው ሲያምር ነውና መልካም መጨረሻችሁን ያሳምረው፣ እደሜያችሁ በቤቱ ይለቅ፣ የነፍስ ዋጋ ያድርግላችሁ፣ እንደዚህ በመልካም ስራ እንደሰበሰበን ተስፋ በምናደርጋት በሰማያዊት እየሩሳሌም የሰበስበን ዘንድ የአምላካችን መልካም ፍቃድ ይሁንልን።

ለኛ ይሄ እንደ ኮሚቴ በውነት ትልቅ ሃላፊነት ትልቅ አደራ ነው። አደራችሁን ተቀብለን በታላቅ ትጋት በአካባብያችን ላሉ አብያተ ክርስቲያናት ከወትሮው በላቀ ሁኔታ ለመስራት ተነስተናል። የማኅበራችን አገልግሎት በ24 አብያተ ክርስቲያናት ላይ መሆኑን ልብ ይሏል።

በዚህ አንቆምም እንቀጥላለን ይህ አመት የሚካኤል ነው የተባለ ነው የሚመስለው፤ ሰቀላ ቅዱስ ሚካኤል ይቀጥላል አገልግሎቱ አላለቀም፤. . .

Address

Addis Ababa

Telephone

+251977309393

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mahibere Medhanealem Ze-Horro/ማኅበረ መድኃኔዓለም ዘ-ሆሮ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Mahibere Medhanealem Ze-Horro/ማኅበረ መድኃኔዓለም ዘ-ሆሮ:

Share