18/05/2026
ሁል ጊዜ ያሉበትን መንሳዊ ህይወት ሁኔታ
መመርመር ከመናቅ ያስመልጣል
"እግዚአብሔርም በእስራኤል ላይ ንጉሥ እንዳትሆን ንቆሃል!"
ሁል ጊዜ የንጉስ ሳኦልን ታሪክ ሳስብ የሚገርመኝ ትልቅ እውነት አለ። ሰውየው የወጣው የጠፉትን አህዮች ፍለጋ ነበር፤ ነገር ግን ሳይዘጋጅበትና ሳይጠብቀው ንግስና በትከሻው ላይ ወደቀ።
ሳኦል አህያ ለመፈለግ እንጂ ለንግስና አልተዘጋጀም ነበር። በመጨረሻም ይህ የዝግጅት ማነስና አለመታዘዝ ዋጋ አስከፈለው። አንድ ቀን አድርግ የተባለውን ባለማድረጉ፣ ነቢዩ ሳሙኤል "የእግዚአብሔርን ቃል ንቀሃልና፥ እግዚአብሔርም በእስራኤል ላይ ንጉሥ እንዳትሆን ንቆሃል" አለው።
ለመሆኑ እግዚአብሔር መሪን ሲንቅና ስልጣኑን ሲወስድ ምን እንደሚያደርግ አስተውላችኋል?እግዚአብሔር ንጉስን ሲንቅ የሚያደርገው ግዑዙን የቤተ-መንግስት ወንበር መውሰድ ብቻ አይደለም፤ ከዛ በባሰ ሁኔታ ከህዝቡ የልብ ዙፋን ላይ ያወርደዋል።
በፌስ ቡክ መንደር የሚነበብ መንፈሳዊ ፅሁፍ