03/03/2026
ሥርዓተ ትምህርቱን ለሚያስተገብሩ የአብነት መምህራንና ደቀመዛሙርት ሥልጠና ተሰጠ።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የካቲት 24/2018 ዓ.ም
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ስር በሚገኘው የአሰላ ማኅደረ ስብሐት በዓታ ለማርያምና ቅዱስ ፋኑኤል ወቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ገዳም ለሚገኙ የአብነት መምህራንና ደቀ መዛሙርት ከየካቲት 21-22/2018 ዓ.ም ለኹለት ተከታታይ ቀናት ከመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በተላኩ ልዑካን በመ/ሃ ቀሲስ ይታገሡ ደሴና በመ/ር ሚኪያስ ግዛቸው የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ፣ ልሳነ ግዝ የማስተማር ዘዴ፣ ትምህርተ ሃይማኖትና ብቁ መምህራን እንዴት ማፍራት ይቻላል በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ሥልጠናው ተሰጥቶዋል።
በሥልጠናው የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች ክፍል ሓላፊ መ/ምሕረት ወልደ ሰንበት"፣ ክቡር የገዳሙ አስተዳዳሪና የሥልጠናው አዘጋጅ መልአከ ስብሐት ገረመው ሸዋዬ ተገኝተው ሥልጠናውን በማነቃቃት አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል። ከሥልጠናው በኋላም የአብነት መምህራኑ በሥርዓተ ትምህርቱ የተካተተውን ልሳነ ግእዝና ትርጓሜ መጻሕፍት ለሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች እንደሚያስተምሩ ይጠበቃል።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
https://www.youtube.com/-gssu
👉 Facebook
https://www.facebook.com/gssu.eotc
👉 Telegram
https://t.me/eotcgssu21
👉 Tiktok
https://www.tiktok.com/
👉 Website
https://eotc-gssu.org/a/