የሰንበት ፡ ትምህርት ፡ ቤቶች ፡ አንድነት

የሰንበት ፡ ትምህርት ፡ ቤቶች ፡ አንድነት በኢትዮጵያ ፡ ኦርቶዶክስ ፡ ተዋሕዶ፡ ቤተክርስቲያን ፡ መንበረ ፡ ፓትርያርክ ፡ ጠቅላይ ፡ ቤተ ፡ ክህነት ፡ የሰንበት ፡ ትምህርት ፡ ቤቶች ፡ ማደራጃ ፡ መምሪያ ፡ ፡የሰንበት ፡ ትምህርት ፡ ቤቶች ፡ አንድነት ፡፡
(1)

የ2019 ዓ.ም የሥርዓተ ትምህርት ማስተግበሪያ የጊዜ ሰሌዳ በተመለከተበኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መም...
08/08/2026

የ2019 ዓ.ም የሥርዓተ ትምህርት ማስተግበሪያ የጊዜ ሰሌዳ በተመለከተ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ከቅዱስ ሲኖዶስ በተሰጠው ተልዕኮ በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ የሚገኙ ሕፃናት፣ ወጣቶች እና ጎልማሶችን በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖት የጸኑ፣ ሥነ ምግባራቸው ያማረ፣ ቀደምት አባቶቻቸውን በመምሰል ቤተ ክርስቲያንን የሚረከቡ እና ሀገርን የሚጠብቁ ትውልድን የማፍራት ሥራውን በመሥራት ላይ ይገኛል።

ይህንንም ከተዥጎረጎረ እና ወጥነት ከጎደለው፣ ለአንድ ዓላማና ግብ የተናጠል ሩጫ ከበዛበት አሠራር ሰንበት ትምህርት ቤቶቻችን ተላቀው በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች በአንድ ሐሳብና በአንድ ቃል እንዲጓዙ የሚያስችል ሥራን በመሥራት ላይ ይገኛል።

ከነዚህም አንዱና ዋነኛው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ነው። ይህም ሥርዓተ ትምህርት በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ባሉ አህጉረ ስብከት በትግበራ ላይ ይገኛል። ሰንበት ትምህርት ቤቶችም ለአተገባበር ያመቻቸው ዘንድ ዓመታዊ የትምህርት መርሐ ግብር የሚያስፈልግ በመሆኑ በሀገር ዐቀፍ ደረጃ ይህን ማስተገበሪያ ሰነድ ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኗል። ይህም ዓመታዊ የትምህርት ማስተግበርያ ሰነድ ለ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን እንዲሆን ተደርጎ ተዘጋጅቷል።

በዚህ ማስተግበርያ ሰነድ ውስጥ የዓመቱን የትምህርት መርሐ ግብር መጀመርያ እና መጨረሻ ጊዜ፣ የፈተና መርሐ ግብራት፣ የሴሚስተር የሪፖርት ጊዜያትን፣ የመርጃ መሣርያ ዝግጅትን ወዘተ በዝርዝር የያዘ ነው። ለዚህም የትምህርት መርሐ ግብር የየአህጉረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት እንዲሁም አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ሓላፊነታቸውን በአግባቡ በመወጣት ሰፊውን ድርሻ መያዝ ይጠበቅባቸዋል። ይህ የትግበራ ሰነድ ወይም የትምህርት መርሐ ግብር በተቀመጠለት ጊዜና ሰዓት ተፈጻሚ መደረግ ይኖርበታል።

ሰነዱንም በአንድነቱ የዌብሳይት ገጽ ላይ ከስር ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ማግኘት ይችላሉ።

https://eotc-gssu.org/a/የ2019-ዓ-ም-የሥርዓተ-ትምህርት-ማስተግበሪያ/

መንበረ ፓትርያርክ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሀገር አቀፍ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
ሐምሌ 2018 ዓ.ም

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!

(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)

👉 Youtube
https://www.youtube.com/-gssu

👉 Facebook
https://www.facebook.com/gssu.eotc

👉 Telegram
https://t.me/eotcgssu21

👉 Tiktok
https://www.tiktok.com/

👉 Website
https://eotc-gssu.org/a/

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት የውስ...
18/07/2026

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት የውስጥ ዝርዝር ማስፈጸሚያ ሰነድ በ2016 ዓ.ም በተዘጋጀው እና በ2018 ዓ.ም የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ ሰነድ መሠረት ሁሉም ሀገረ ስብከቶች ወደ ተግባራዊ ሥራ በመግባት ላይ መሆናቸው ይታወቃል።

በመዋቅራዊ አሠራሩም በተገለጸው መሠረት አጥቢያ ሰንበት ት/ቤት፣ ክፍለ ከተማ፣ መንበረ ጵጵስና እና መንበረ ፓትርያርክ ደረጃ በደረጃ ወጥ በሆነ አሠራርና ጊዜ እንዲፈጸም ትግበራ ላይ ይገኛል።

በዚህም መሠረት የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በሀገረ ስብከቱ የሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማከናወናቸውን ተከትሎ በአዲሱ አደረጃጀት የተመረጡ ከ2300በ ላይ የሰንበት ት/ቤት ሥራ አመራሮች እና የአፈጻጸም ቁጥጥር እና ክትትል ጉባኤ አባላትን ሐምሌ 11 ፣12 እና 25 /2018 ዓ.ም በተመረጡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሥልጠና ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቅቆ ሥልጠናው ዛሬ ሐምሌ 11/12/18/25 /2018 ዓ.ም ከቀኑ 7:30 አስከ 11:30 በአስራ ኹለት የስልጠና ጣቢያዎች መስጠት ጀምሯል።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!

(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)

👉 Youtube
https://www.youtube.com/-gssu

👉 Facebook
https://www.facebook.com/gssu.eotc

👉 Telegram
https://t.me/eotcgssu21

👉 Tiktok
https://www.tiktok.com/

👉 Website
https://eotc-gssu.org/a/

በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት 4ኛው የአህጉረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ አዳራሽ በ...
13/07/2026

በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት 4ኛው የአህጉረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ አዳራሽ በዛሬው ዕለት ተጀመረ።

(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 06/2018 ዓ.ም

በዛሬው የመክፈቻ መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ አገልግሎት መምርያ ሊቀ ጳጳስ ፣ መጋቤ ሐዲስ ኃይለ እግዚእ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ ፣ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት መምሪያ ሐላፊ ፣ ሊቀ ጉባኤ መሐሪ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ምክትል ሐላፊ ፣ ዲ/ን ስንታየሁ ምስጋና የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሥራ አመራር አባላት እና የመምሪያው ልዩ ልዩ ሠራተኞች በተገኙበት በጸሎተ ወንጌል ተጀምሯል።

ብፁዕ አቡነ ማርቆስ በመዝሙር 125(126):5 ላይ "በልቅሶ የሚዘሩ በደስታ ያጭዳሉ።" የሚለውን የዳዊት መዝሙር መነሻ አድርገው ገበሬ በልቅሶ በመከራ በክረምት ዘርን እንደሚዘራ በገበሬ አምሳል መምህራንም ዘር የተባለ ቅዱስ ወንጌልን በልቅሶ በመከራ ለማስተማር መዘጋጀት ይገባችዋል በማለት ለሰልጣኝ መምህራኑ አባታዊ ቡራኬና መልእክት አስተላልፈዋል።

"የተጠማ ቢኖር ወደኔ ይምጣና ይጠጣ በእኔ የሚያምን ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚል የሕይወት ውኃ ምንጭ ከሆዱ ይፈልቃል።" ዮሐ 7:38 በሚል ቃል መነሻ አድርገው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

በመቀጠልም በዲ/ን ስንታየሁ ምስጋናው አጠቃላይ የሥልጠናውን ይዘትና አካሄድ ላይ ገለጻ አድርገዋል። ሥልጠናው በ3 መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሲሆን እነርሱም መሠረተ እምነት ዶግማ እና የሥርዓተ አምልኮ ጉዳዮች ፣ ሥርዓተ ትምህርትን የሚመለከቱ ሥልጠናዎች እንዲሁም ተግባራዊ ሥራና የሕይወት ክህሎት ናቸው። በሥልጠናውም ላይ ከ37 አህጉረ ስብከት የተወጣጡ ከ315 በላይ ሠልጣኞች ይሳተፋሉ።

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!

(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)

👉 Youtube
https://www.youtube.com/-gssu

👉 Facebook
https://www.facebook.com/gssu.eotc

👉 Telegram
https://t.me/eotcgssu21

👉 Tiktok
https://www.tiktok.com/

👉 Website
https://eotc-gssu.org/a/

"የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫እንኳን ለዓመታዊው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች...
30/05/2026

"የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫

እንኳን ለዓመታዊው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!

የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በጋራ ጉባኤ በአንድነት ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሚመክሩበት፣ የትውልዱን መጻኢ ጉዞ የሚተልሙበት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለነገው ትውልድ ሊያሻግሩ የሚችሉ ዐውደ ሐሳቦች ለውይይት የሚቀርቡበት ታላቅ በዓል ነው። ይህ በቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅና ተሰጥቶት በየዓመቱ እየተከናወነ የሚገኘው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ዘንድሮ በሀገራዊ ጉዳይ ምክንያት በመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ደረጃ ጠቅላላ ጉባኤውን በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማከናወን ባይችልም በሁሉም አህጉረ ስብከት፣ በየወረዳው እና በየአጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ዕለቱ በደማቅ ሁኔታ "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫ በሚል መሪ ቃል ተከብሮ ይውላል።

ቅዱስ ጳውሎስ "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ብቻ አይደለም ያለን ይህንንም የመንፈስ አንድነት እንዴት መጠበቅ እንዳለብን በመንገርም ጭምር ነው እንጂ። ይኸውም በፍጹም የዋሕነት፤ ራሳችሁን ዝቅ አድርጋችሁ፣ እየታገሣችሁ፣ ለወንድሞቻችሁም እሺ እያላችሁ፣ በፍቅር እየተጋችሁና እየተባበራችሁ በማለት ነው። የአንድነታችንንም ዓላማ እንዳንዘነጋ ሲገልጽልን “ለአንዱ ተስፋችሁ እንደመጠራታችሁ” ይለናል። እኛም የ15ኛ ዓመት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ቀንን ስናከብር ከወትሮ በላቀ የመንፈስ አንድነታችንን ለመጠበቅ መትጋት እንዲገባን ይህን የቅዱስ ጳውሎስን ምክር መርሐችን አድርገናል። ከሁል ጊዜው በላይ ዓለምም ሆነ ሀገራችን እየተጓዘችበት ካለው አስፈሪ የጥፋት ጉዞ ትውልዱን መጠበቅ፣ ማዳንና ማሰማራት የሚቻለው የመንፈስ አንድነታችንን ለመጠበቅ ስንተጋ ብቻ ነው።

የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ትውልዱን በቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር ለመጠብቅ የመንፈስን አንድነት መርሕ ይዞ የሚጓዝ መዋቅር ነው። ታዲያ ይህንን አንድነታችንን ከውስጥም ከውጭም ፈተናዎች ለመጠበቅ እየታየ ያለውን በጎ ፍሬ ለማስቀጠል ትጋትን ገንዘብ ልናደርግ ይገባናል እንላለን። ምንም እንኳን በበዓለ ጰራቅሊጦስ የዘንድሮውን ዓለም አቀፋዊ ጠቅላላ ጉባኤያችንን ማከናወን ባንችልም በያለንበት መዋቅር ዕለቱን ልንዘክረው ይገባናል። በመጨረሻም የዘንድሮውን ዓለም ዓቀፍዊ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ የሚከናወንበትን ዕለት በቅርቡ የምናሳውቅ መሆኑን እየገለጽን እንኳን ለዓመታዊው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ እንላለን።

የመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
ግንቦት 22/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

👉 Youtube
https://www.youtube.com/-gssu

👉 Facebook
https://www.facebook.com/gssu.eotc

👉 Telegram
https://t.me/eotcgssu21

👉 Tiktok
https://www.tiktok.com/

👉 Website
https://eotc-gssu.org/a/

https://youtube.com/live/7NXwJ7bgm_s
05/04/2026

https://youtube.com/live/7NXwJ7bgm_s

የደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴደራል የቀጥታ ሥርጭት የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር

ሥርዓተ ትምህርቱን ለሚያስተገብሩ የአብነት መምህራንና ደቀመዛሙርት ሥልጠና ተሰጠ።(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)  የካቲት 24/2018 ዓ.ምበምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ስር በሚገኘው የአሰላ ማኅ...
03/03/2026

ሥርዓተ ትምህርቱን ለሚያስተገብሩ የአብነት መምህራንና ደቀመዛሙርት ሥልጠና ተሰጠ።

(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የካቲት 24/2018 ዓ.ም

በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ስር በሚገኘው የአሰላ ማኅደረ ስብሐት በዓታ ለማርያምና ቅዱስ ፋኑኤል ወቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ገዳም ለሚገኙ የአብነት መምህራንና ደቀ መዛሙርት ከየካቲት 21-22/2018 ዓ.ም ለኹለት ተከታታይ ቀናት ከመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በተላኩ ልዑካን በመ/ሃ ቀሲስ ይታገሡ ደሴና በመ/ር ሚኪያስ ግዛቸው የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ፣ ልሳነ ግዝ የማስተማር ዘዴ፣ ትምህርተ ሃይማኖትና ብቁ መምህራን እንዴት ማፍራት ይቻላል በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ሥልጠናው ተሰጥቶዋል።

በሥልጠናው የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች ክፍል ሓላፊ መ/ምሕረት ወልደ ሰንበት"፣ ክቡር የገዳሙ አስተዳዳሪና የሥልጠናው አዘጋጅ መልአከ ስብሐት ገረመው ሸዋዬ ተገኝተው ሥልጠናውን በማነቃቃት አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል። ከሥልጠናው በኋላም የአብነት መምህራኑ በሥርዓተ ትምህርቱ የተካተተውን ልሳነ ግእዝና ትርጓሜ መጻሕፍት ለሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች እንደሚያስተምሩ ይጠበቃል።

(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!

(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)

👉 Youtube
https://www.youtube.com/-gssu

👉 Facebook
https://www.facebook.com/gssu.eotc

👉 Telegram
https://t.me/eotcgssu21

👉 Tiktok
https://www.tiktok.com/

👉 Website
https://eotc-gssu.org/a/

አድዋ"በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፥ በስምህም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን።" መዝ 43፡5 እንኳን ለአድዋ ድል መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ!መልካም በዓል!የሰንበት ት/ቤቶች አንድ...
02/03/2026

አድዋ

"በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፥ በስምህም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን።" መዝ 43፡5

እንኳን ለአድዋ ድል መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ!

መልካም በዓል!

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!

(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)

👉 Youtube
https://www.youtube.com/-gssu

👉 Facebook
https://www.facebook.com/gssu.eotc

👉 Telegram
https://t.me/eotcgssu21

👉 Tiktok
https://www.tiktok.com/

👉 Website
https://eotc-gssu.org/a/

https://youtu.be/dFEbc2I2e54
21/02/2026

https://youtu.be/dFEbc2I2e54

Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.

 "ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።" ራዕ 12፡1እንኳን ለእመቤታችን ...
29/01/2026



"ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።" ራዕ 12፡1

እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍት በዓል (አስተርዕዮ ማርያም) በሰላም አደረሳችሁ!

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!

(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)

👉 Youtube
https://www.youtube.com/-gssu

👉 Facebook
https://www.facebook.com/gssu.eotc

👉 Telegram
https://t.me/eotcgssu21

👉 Tiktok
https://www.tiktok.com/

👉 Website
https://eotc-gssu.org/a/

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሰንበት ፡ ትምህርት ፡ ቤቶች ፡ አንድነት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share