አንዲት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስትና ሀይማኖት One Orthodox Tewahdo Christian Religion

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • አንዲት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስትና ሀይማኖት One Orthodox Tewahdo Christian Religion

አንዲት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስትና ሀይማኖት One Orthodox Tewahdo Christian Religion ፈጣሪያችን ሆይ እንደ ስራችን ሳይሆን እንደ ቸርነትህ አስበን🙏🙏🙏 Welcome to Ethiopian Orthodox Church �

01/05/2026
‹‹ሚያዚያ 23›› በዚህች ዕለት የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕትነት የተቀበለበት ዕለት ነው።ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዐላዊያን (ከሐዲያን) የሮማ ነገስታት በተለይም ከ284-305 ዓ.ም ነግ...
30/04/2026

‹‹ሚያዚያ 23›› በዚህች ዕለት የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕትነት የተቀበለበት ዕለት ነው።

ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዐላዊያን (ከሐዲያን) የሮማ ነገስታት በተለይም ከ284-305 ዓ.ም ነግሰው በነበሩ የዲዮቅልጥያኖስ እና ዲዲያኖስ ዘመነ መንግስታት ስለ ክርስቶስ ሲል ሰባት ዓመታት ለመስማት እንኳን የሚያስጨንቅ መከራን የተቀበለ።

እንዲሁም ሦስት ጊዜ ቢገድሉትም የታመነለት ክርስቶስ ሶስት ጊዜ ከሞትም ያስነሳው፣ በአራተኛውም ጊዜ ሚያዚያ 23.303 ዓ.ም ላይ አንገቱን የተቆረጠበትና የምስክርነት አክሊልን የተቀበለ ንዑድ፣ ክቡር ሰማዕት ነው።

ቅዱስ ጊዮርጊስም ራሱን ዘንበል አደረገ፤ በሰይፍም ቆረጡት፤ በመንግሥተ ሰማያት አክሊላትን ተቀበለ፡፡

ክርስቲያኖቹም ሥጋውን ወስደው በልብስ ጠቀልለው ወደ ሀገሩ ልዳ ከወሰዱት በኋላ ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው በውስጥዋ አኖሩት፤ ከእርሱም ቍጥር የሌላቸው ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ፡፡

ይህ ዕለት ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በሰማዕትነት ያረፈበት ዕለት በማሰብ የሚከበር በዓል ሲሆን፣ ከክብረ ጌታ ከጌታችንና ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ በምድር መታሰቢያውን ለሚያደርግ ኃጢያቱን እንደሚሰረይለት፣ በመከራ፣ በደዌ ውስጥም ቢሆኞ ልመናውን እንደሚሰማለትና ድኅነትን እንደሚያገኝ ቃልኪዳን የተሰጠበት ሰማዕት ነው።

ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ይሰውረን 🙏

❖ ሚያዝያ ፳፫፦ በዓለ ዕረፍቱ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕት ❖ ሚያዝያ ፳፫ ቀን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሰማዕታት አለቃ፣ ኮከበ ብሩህ፣ የልዳው ፀሐይ የተባለ የቅዱስ ጊዮርጊስን ዓመታዊ የዕረፍ...
30/04/2026

❖ ሚያዝያ ፳፫፦ በዓለ ዕረፍቱ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕት ❖

ሚያዝያ ፳፫ ቀን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሰማዕታት አለቃ፣ ኮከበ ብሩህ፣ የልዳው ፀሐይ የተባለ የቅዱስ ጊዮርጊስን ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በታላቅ ድምቀት ታስባለች።

ቅዱስ ጊዮርጊስ ስለ ክርስቶስ ፍቅር ሲል ሰባ ነገሥታትን ተቋቁሞ፣ ሰባት ዓመታት ሙሉ ልዩ ልዩ መከራዎችን በመቀበል የሰማዕትነት አክሊልን የተቀዳጀበት ዕለት ነው።

መጽሐፈ ስንክሳር እንደሚነግረን፣ በሰማዕትነቱ ማጠቃለያ ላይ ንጉሡ ዱድያኖስ በቅዱስ ጊዮርጊስ ጽናት አፍሮና ደንግጦ ሳለ፣ ቅዱሱ በጸሎቱ የንጉሡን ሚስት ንግሥት እስክንድርያን ወደ ክርስቶስ እምነት እንዲመጡ አድርጓል።

ንጉሡም በዚህ ተቆጥቶ ንግሥቲቱን በመጋዝ እንዲሰነጥቋት አዝዞ የሰማዕትነት አክሊልን ተቀብላለች። ከዚህም በኋላ ነገሥታቱ ቅዱስ ጊዮርጊስን በሰይፍ እንዲገድሉት መከሩት።
ቅዱስ ጊዮርጊስ ለሰማዕትነት ከመቅረቡ በፊት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጦለት ታላቅ ቃል ኪዳን ሰጥቶታል፦

"በምድር መታሰቢያህን ለሚያደርግ ሁሉ እኔ ኃጢአቱን ሁሉ እደመስሳለሁ፤ በመከራም ውስጥ ሆኖ በባሕርም ሆነ በየብስ ወይም በደዌ በስምህ የሚለምነኝን እኔ ፈጥኜ ከመከራው አድነዋለሁ" (ስንክሳር ዘወርኃ ሚያዝያ ፳፫)።

ቅዱሱም ራሱን ዘንበል አድርጎ በሰይፍ ተቆርጦ በታላቅ ክብር የሰማዕትነት አክሊል ተቀዳጅቷል። ምእመናንም ሥጋውን ወስደው በትውልድ ሀገሩ በልዳ ቤተ ክርስቲያን አንጸው አኑረውታል። ከቅዱስ ሥጋውም ቍጥር የሌላቸው ድንቅ ተአምራት ተገልጠዋል።

የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ ምልጃና ተራዳኢነት ከሁላችን ጋር ይሁን። በቃል ኪዳኑ ታምነን ዝክሩን የምናዘክር፣ በስሙ ለተቸገሩት እጃችንን የምንዘረጋና በጸሎቱ የምንታመን ሁሉ በረከቱ ይደርብን። አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር በሰማዕቱ ቃል ኪዳን ከሥጋና ከነፍስ መከራ ይጠብቀን።

የእግዚአብሔር አብ ቸርነት፣ የወልድ ፍቅር፣ የመንፈስ ቅዱስ አንድነት፣ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ፍጹም ፍቅርና አማላጅነት፣ የቅዱሳን መላእክት ፈጣን ተራዳኢነት፣ የቅዱሳን አባቶቻችን ጸሎት፣ የአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰላም በሁላችንም ላይ ይደር። አሜን።

እንኳን ለሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

በዲ/ን አየለ

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አንዲት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስትና ሀይማኖት One Orthodox Tewahdo Christian Religion posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to አንዲት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስትና ሀይማኖት One Orthodox Tewahdo Christian Religion:

Share