Orthodox tewhado የእመብርሃን ልጅ Page

Orthodox tewhado የእመብርሃን ልጅ Page የጥበብ የእውቀት ሁሉ መጀመሪያው እግዚአብሔርን መፍራት ነው!

ግንቦት-11 ቅዱስ ያሬድ አመታዊ ክብር በዓል እንኳን አደረሳችሁ!ያሬድ ካህኑ ዘመረ ያሬድ ካህኑ ዘመረዘመረ ያሬድ ዘመረ አምላኩን አመሰገነ×2ቅዱስ ያሬድ ውልደትና እድገቱ ኢትዮጵያ ወስጥ፣ አ...
18/05/2026

ግንቦት-11 ቅዱስ ያሬድ አመታዊ ክብር በዓል
እንኳን አደረሳችሁ!

ያሬድ ካህኑ ዘመረ ያሬድ ካህኑ ዘመረ
ዘመረ ያሬድ ዘመረ አምላኩን አመሰገነ×2

ቅዱስ ያሬድ ውልደትና እድገቱ ኢትዮጵያ ወስጥ፣ አክሱም ከተማ ከአባቱ ከአብዩድና ከእናቱ ታውክሊያ ነው፤ ዕድሜው ለትምህርት ሲደርስ እናቱ መምህር ወደ ሆነው አጎቱ አባ ጌዲዮን ትወስደዋለች

እርሱ ግን በመጀመሪያ ትምህርት ሊገባው አልቻለም ከዕለታት በአንድ ቀን መምህር ጌዲዮን ያሬድን ሲገርፈው በምሬት አለቀሰ ማይኪራህ ወደምትባል ቦታም ተጓዝ በመንገድ ላይ ሳለ ውኃ ስለተጠማ በዚያች ስፍራ ካለ ምንጭ ውኃ ጠጥቶ በዛፉ ሥር ለማረፍ ቁጭ አለ ወደ ላይም በሚመለከትበት ጊዜ ከዛፉ ላይ አንዲት ትል ፍሬ ለመብላት ከታች ወደ ላይ ስትወጣ ስትወርድ ተመለከተ
እርሱም ትኩር ብሎ አያት ትሏም ስድስት ጊዜ ያለመሰልቸት ከወጣች ከወረደች በኋላ በሰባተኛው ፍሬው ካለበት መድረስ ቻለች ፍሬውንም መብላት ጀመረች
በዚያን ወቅት ቅዱስ ያሬድ አሰበ፤ እንዲህም አለ "ይህች ትል ፍሬውን ለመብላት እንዲህ ከታገሠች እኔም እኮ ትምህርት ለመማር ብታገሥ እግዚአብሔር አምላክ ይገልጽልኛል"
ወደ ጉባኤው ተመልሶ መምህሩን ይቅርታ ከጠየቀ በኋላ መማር ጀመረ እግዚአብሔር አምላክም የ፹፤፩ መጽሐፍትንና የሊቃውንት መጽሐፍትን እንዲሁም ሌሎች ቤተ ክርስቲያን የተቀበለቻቸውን የቅዱሳት መጻሕፍትን ምሥጢር ገለጸለት መምህር ጌዲዮን ሲሞት የእርሱን ቦታ ተረክቦ ማሰተማር ቀጠለ

በ፭፻፴፬ ዓ.ም. ኅዳር ፮ ቀን ወደ ሰማይ ተነጠቀ በሰማይ ቅዱሳን መላእክት እግዚአብሔርን ልዩ በሆነ ጣዕመ ዝማሬ ሲያመሰግኑ ሰማ
ወደ ምድርም በተመለሰ ጊዜ አክሱም ጽዮን ውስጥ ወደ ምሥራቅ በኩል በመዞር ከሰማይ የሰማውን ዝማሬ ዘመረ አርያም ብሎም ሰየመው
በዚሁም በ፭፻፴፰ ዓ.ም. ቅዱስ ያሬድ ማኅሌትን ጀመረ
ታኅሣሥ ፩፣ በዕለተ ሰኞ ምህላ ያዘ እሰከ ታኅሣሥ ፮ ቀዳሚት ሰንበት ድረስም ዘለቀ በዚያች ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመልዕልተ መስቀል አንደተሰቀለ ሆነ ከቅዱሳን መላእክት ጋር ተገለጸለት

ቅዱስ ያሬድም ጌታ የተገለጸለትን የመጀመሪያውን ሳምንት ‹ስብከት› ብሎ ሰየመው በሳምንቱም እንደገና በብርሃን አምሳል ስለተገለጸለት ያን ዕለት ‹ብርሃን› ብሎ ሰየመው በሦስተኛው ሳምንት እንዲሁ በአምሳለ ኖላዊ ስለተገለጸለት ‹ኖላዊ› ብሎ ሰየመው በመጨረሻም ሳምንት በአምሳለ መርዓዊ ሲገለጽለት ዕለቱን ‹መረዓዊ› ብሎ ሰይሞታል

ከዚህም በኋላ ቅዱስ ያሬድ ፭ የዜማ መጻሕፍትን ደረሰ እነዚህም ድጓ ጾመ ድጓ ምዕራፍ ዝማሬና መዋሥዕት ናቸው ከደረሳቸው የዜማ መጽሐፍቶችም ውስጥ ትልቁ ድጓ ነው በሦስትም ይከፈላል የዮሐንስ አስተምህሮና ፋሲካም ይባላሉ በንባባት ብቻ ይቀደስባቸው የነበሩትን ፲፬ቱ ቅዳሴያት በዜማ የደረሳቸው ቅዱስ ያሬድ ነው ዝማሬም በ፭ ይከፈላል ኅብስት ጽዋዕ መንፈስ አኮቴትና ምሥጢር ይባላል

ይህ ቅዱስ ደራሲ በተወለደ በ፸፭ ዓመቱ በሰሜን ተራራ ውስጥ ደብረ ሐዊ ከሚባል ገዳም ግንቦት ፲፩ ቀን ተሠውሯል
የዝማሬና መዋሥዕት መምህራን የቅዱስ ያሬድን ጉባኤ ተክተው አሁን በማስተማር ላይ እስካሉት መጋቤ ብርሃናት ፈንታ ድረስ ፵፮ ናቸው

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ባለውለታ ቅዱስ ያሬድ መምህር ወሐዋርያ መጻሕፍትን በጣዕመ ዜማ የደረሰ፣ መዝሙረ ዳዊትን ጨምሮ ሌሎችንም ቅዱሳት መጻሕፍትን በተለያየ ዜማ ያመሳጠረ ታላቅ ኢትዮጵያዊ ሊቅ ነው

የቅዱስ ያሬድን ጸጋና በረከት ያድለን!
አሜን አሜን አሜን🙏🙏🙏

ከቀናቶች ሁሉ የተለየ ቀን ከወራቶች ሁሉ የከበረ ወር ከአመታቶች ሁሉ የሚደነቅ አመት እመቤታችን ቤዛዊተ ዓለም ልደታ ማርያም የጭንቅ አማለጇ የተወለደችበት ቀን የዓለም ሕዝብ ተደምሮ አንዲቷን...
09/05/2026

ከቀናቶች ሁሉ የተለየ ቀን ከወራቶች ሁሉ የከበረ ወር ከአመታቶች ሁሉ የሚደነቅ አመት እመቤታችን ቤዛዊተ ዓለም ልደታ ማርያም የጭንቅ አማለጇ የተወለደችበት ቀን የዓለም ሕዝብ ተደምሮ አንዲቷን የጸጉሯን ዘለላ የማይሆነው ከተወለደችበት ቀን ድረስ አምላኳ ጌታዋ በልቧ ያለ በቤተ መቅደሱ ያደገች ለ ሰላሳ ሦስት አመት ከልጇ ያለተለየች እንደቃልህ ይሁንልኝ እነሆኝ የጌታ ባርያ ያለች ስትናገር የማትሰማ የሚላችሁን አድርጉ የምትል በእግዚአብሔር ህሊና ታስባ የነበረች የቤተመቅደስ ሙሽራ ዛሬ ተወለደች ለዓለም ሁሉ ድህነት ደስታ ሆነ ታዲያ በዚህ እለት ሰይጣን ዳቢሎስ ቅጥል የሚልበት ቀን ነው እንኳን ደስ አላቸው አደረሳችሁ;-

➕➕➕   ➕➕➕እንኳን ለእናታችን ለአማላጃችን ለንጽሕይት ወብጽሕይት ቅድስት ድንግል ማርያም ታላቅ ክብር በዓል አደረሳችሁ አደረሰን፦የሴቶች ቀን የእናቶች ቀን ግንቦት 1 ቤዛዊተ ዓለም መለኮት...
06/05/2026

➕➕➕ ➕➕➕

እንኳን ለእናታችን ለአማላጃችን ለንጽሕይት ወብጽሕይት ቅድስት ድንግል ማርያም ታላቅ ክብር በዓል አደረሳችሁ አደረሰን፦

የሴቶች ቀን የእናቶች ቀን ግንቦት 1 ቤዛዊተ ዓለም መለኮትን የወለድሽ የአማኑኤል እናት የመዳናችን ምክንያት የአዳም ተስፋው የደናግል መመኪያቸው የሐዋርያት ስብከታቸው የቅዱሳን ምርኩዛቸው የመላእክት እህታቸው የሰማዕታት አክሊላቸው የዘረያቆብ እመቤት የአባ ሕርያቆስ ቅዳሴ የአባ ኤፍሬም ድርስቱ የአባ ሣሙኤል ዘይቱ የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ድርሰቱ ምሥጋናው የኤልሣ ማሰሮ የያሬድ ቅኔ ማህሌታት የዩሐንስ ስጦታ የክርስቲያኖች ሙኪያቸው አንቺ ነሽና ምልጃሽ ቃልኪዳንሽ ዛሬም ከእኛ ከደካሞቹ ልጆችሽ አይለየን:-

እመቤታችን ቅድስት ንጽህይት ብጽሕይት ድንግል ማርያም ከአባቷ #ከእያቄም ከእናቱ #ከሐና የተወለደች ሲሆን በአባቷ ከዳዊት ወገን ስትሆን ከእናቷ ደግሞ ከሊቀ ካሕናት ከአሮን ወገን ነች። እናትና አባቷ በሕገ እግዚአብሔር የሚያምኑ ቅዱሳን ነበሩ። ነገር ግን በአይሁዳውያን ዘንድ ልጅ ስላልነበራቸውና መካን በመሆናቸው እጅግ የተጠሉ ነበሩ። ከእዚህም የተነሳ እግዚብሔር አምላክ ልጅ እንዲሰጣቸው ስዕለት ተስለው እመቤታችን እመብርኅን ተወለደች። ጊዜውም ጌታ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው ሆኖ ሊወለድ #15 ዓመት ሲቀረው ሲሆን የተወለደችነት ቀን ቀን ከሊባኖስ ተራራ አካባቢ ነው።

እመቤታችን ቤዛዊተ ዓለም ገና በእናቷ በቅድስት #ሐና ማኅፀን እያለች ታአምራት ታደርግ ነበር። ከተአምራቶቹም መካከል ከብዙ ጥቂቱን ለመጥቀስ ያህል #የሐና ዘመድ የሆነች አንዲት ስሟ ቤርሴባ የተባለች አይነ ስውር #የሐናን ሆዷን ስትነካው ዓይኗ በርቶላታል። በሌላ ጊዜም #ሐና ጸንሳ ሳለ የሞተ ሰው ሬሳ ብትነካ ሙት ሊነሳ ችሏል።

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሰም( ስመ ድንግል ማርያም)
#ማርያም የሚለው ቃል በዕብራይስጥ "ማሪሃም" ሲሆን ትርጉሙም እመብዙኀን የብዙኀን እናት ማለት ነው።

#ማርያም ፦ ማለት " መርሕ ለመንግሥተ ሰማይ " ወደ መንግሥተ ሰማያት መርታ የምታስገባ ማለት ነው። በአዳም ምክንያት የተዘጋው የገነት በር የተከፈተባት የጸድቅ መክፈቻ ናትና ወደ መንግሥተ ሰማያት መርታ የምታስገባ ትባላለች። ስለዚህ ምክንያት የእርሷን እናትነትና አማላጅነት መመኪያ ሳያደርግ ወደ መንግሥተ ሰማያት መግባት የሚቻለው የለም። የገነት ደጃፍ የተከፈተባት ንጽሕይት ሙሽራ ናት።

#ማርያም ፦ ማለት "ጸጋ ወሀብት" ማለት ነው ከእመቤችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደው መድኃኔዓለም አዳምን ወደ ቀደመ ክብሩ ስለመለሰው አጥቶት የነበረው መንፈሳዊ ሃብትና ጸጋ አግኝቷል እመቤታችን ማርያም ጸጋና ሃብት የተገኘባት ብፅዕት እናት ናት። ሉቃስ 1፥28 "ጸጋን የሞላብሽ ሆይ ጌታ ከአንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ"

#ማርያም ፦ማለት "መልዕልተ ፍጡራን መትህተ ፈጣሪ" ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች ያለች ማለት ነው። መላዕክት በመፍራትና በመንቀጥቀጥ ለምስጋና በፊቱ የሚቆሙትን አምላክ እርሷ ግን በማኅፀኗ ተሸከመችው ጡቷን አጠባችው በጀርባዋ አዘለችው ልጄ አምላኬ አለችው አዘዘችው መላእክት እንኳን ሊነኩት ሊያዩት የማይላቸውን ባሕርየ መለኮት በማኅፀኗ ተሸክማዋለችና ከፍጡራን ሁሉ በላይ ከፈጣሪ በታች መሆኗ የሚታመን ነው።

#ማርያም ፦ማለት "እግዝእተ ብዙኅን" (የብዙዎች እመቤት) ማለት ነው ሔዋን የሕያዋን ሁሉ እናት ተብላ ነበር። ዘፍ 3፥20 ነገር ግን በሔዋን መሳሳት ምክንያት የሰው ልጅ ሁሉ ከተፈረደቸው ሞት ከዳያቢሎስ ባርነት ነፃ ያወጣቸው ዘንድ አምላክ ከቅድስ ብጽሕት ድንግል ማርያም ተወልዷልና የብዙዎች እመቤት እናት ተብላች እርሷን የሚመስል ማንም የለምና።

#ማርያም ፦ማለይ በምድር "ማር" በሰማይ "ያም" ከሚለው ተገናኝቶ የተገኘ ስም ነው። በምድር በጣፋጭቱ የሚታወቀው በጣዕሙ ወደር የሌለው ምግብ ማር ነው። እንዲሁም በገነት ቅዱሳን ብቻ የሚመገቡት እጅግ የሚጣፍጥ ያም የሚባል ምግብ አለ። የእመቤችን ርኅራሄዋና ፍቅሯ በምድር ባሉ እና በሰማይ በሚኖሩ ዘንድ እጅግ ጣፋጭ በመሆኑ #ማርያም ተብላለች።

እመቤችን ቅድስት ድንግል ማርያምን የስሟን ፊደል አባቶች እንዲህ ብለው በዚህ መሰረት ተርጉመውታል፦

#ማ ፦ "ማኅደረ መለኮት" የመለኮት ማደሪያ

#ር ፦ "ርግብዬ ይቤላ" ሰለሞን ርግብዬ ይላታልና

#ያ ፦ "ያንቃዐዱ ኅቤኪ ኩሉ ፍጥረት" ፍጥረት ሁሉ ለምኝልን እያሉ ወደ አንቺ ያንጋጥጣሉ።

#ም ፦ "ምስዐል ወምስጋደ ወመስተሥራየ ኅጢአት" መስገጃ መለመኛ የኅጢአትም ማስተሰሪያ ማለት ነው።

የሐና እና የእያቄም ፍሬ በረከት እመቤታችን ቅድስት ንፅዕት ብፅዕት ድንግል ማርያም የሴቶች መመኪያ እመብርኃን እመብዙኃን እመአዶናይ እመአምላክ ወላዲተ ቃል የሰዎች ይመዳናቸው ምክንያት ተወለደች,,,,,,,,,,,,,,,,,,,

እመቤታችን በመወለዷ የሴትነትን የእናትነትን ክብርና ነጻነት አገኘን ክብር ምስጋና ይግባት አምላክን የወለደች ንጽይት በቅድስና ወብፅዕይት በድንግልና ልጅሽ ምሕረት ቸርነትን ይቅርታን ያደርግልን ዘንድ ልምኚልን፣

➕➕➕    ➕➕➕የትንሣኤው የጌቶች ጌታ የንጉሶች ንጉሥ የአምላክት አምላክ የንፅዕት ብፅዕት ቅድስት ድንግል ማርያም ልጅ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቸርነትህ በምህረትህ በይቅርታህ...
18/04/2026

➕➕➕ ➕➕➕

የትንሣኤው የጌቶች ጌታ የንጉሶች ንጉሥ የአምላክት አምላክ የንፅዕት ብፅዕት ቅድስት ድንግል ማርያም ልጅ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቸርነትህ በምህረትህ በይቅርታህ ማረን ይቅርም በለን!

ቅድስት እናት ቤተክርስቲያናችን ዕለትና ቀን አበጅታ የሰራችልን የትንሣኤ ሣምንት ዳግም ትንሣኤ:-

ዳግም ትንሣኤ ሲባል መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ዳግም ሞቶ ተቀበሮ ተነሳ ሳይሆን በድጋሜ ቅዱስ ቶማስ ባለበት ልክ በመጀመሪያ እንደተገለጠላቸው
ሆኖ ስለታያቸው ነው

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአሰሩ ሐዋርያት ሲገለጥላቸው ሐዋርያው ቶማስ አልነበረምና መጥቶ በተገናኛቸው ጊዜ እነሱም ጌታችን እንደተነሳና ተገልጦ ሰላምታ እንደሰጣቸው ሲነግሩት የተቸነከረውን እጁን እና እግሩን በጦር የተወጋ ጎኑን ካላየሁ አላምንም በመለቱ (ዮሐንስ 20:25) እንደገና ተገልጦላቸዋል

ቶማስ ይሄንን ሊል የቻለው የተጠራው ትንሣኤ ሙታን
የለም ከሚሉት ከማያምኑት ከሰዱቃውያን ወገን ነበርና ነው አንድም ሌሎች ሐዋርያት ሞትን ድል አድርጎ ተነሳ አየነው እያሉ ሲያስተምሩ እኔ ግን
ሰማሁ ብዬ ላስተምር ነው ብሎ ነው ጌታም የቶማስን ጥርጣሬ ያስወግድለት ዘንድ በተነሳ በስምንተኛው ቀን ቅዱስ ቶማስ ከሌሎች ሐዋርያት ጋር ሳለ እንደገና በትንሣኤ እንደታያቸው ሆኖ በዝግ ቤት ገብቶ ሰላምታ ከሰጣቸው በኋላ ሐዋርያው ቶማስን ለይቶ "ቶማስ ቶማስ ና በችንካር የተቸነከሩ እጆቼን እይ እንዲሁም እጅሀን አምጥተሀ በጦር ወደ ተወጋው ጎኔ አግብተሀ ዳሰኝ ያመንክ እንጅ ተጠራጣሪ አትሁን በጦር የተወጋ ጎኑን በእጆቹ በዳሰሰ ጊዜ ከእሳት እንደገባ ጅማት ኩምትርትር ሲል "ጌታም አንተ አይተኽ አምነሃል ነገር ግን" ሳያዩ የሚያምኑ ብፁአን ናቸው "ብሎ ፈውሶታል(ዮሐ 20:29)
እስከ ዛሬም ይህቺ ጌታን የዳሰሰች የቅዱስ ቶማስ እጅ በሕንድ አገር ከታቦት ጋር በመንበሩ ላይ ተገኛለች

በሌላ በኹል ዳግም ትንሣኤ የተባለበት በአከባበር
በሥርዓት የመጀመሪያውን ትንሣኤ ስለሚመስል ነው የትንሣኤ ዕለት የሚባለው ቃለ እግዚአብሔር ሳይለወጥ በሙሉ በዚህ ቀን ይባላል።

ከዚህም ሌላ ሁለት መጠሪያ ስሞች አሉት፦
እነዚህም "ፈጸምነ እና "አግብዖተ_ግብር" ይባላል።
"ፈጸምነ" የተባለበት የሰሙነ ትንሣኤን በዓል አክብረን ፈጸምን ማለት ነው። "አግብዖተ ግብር"የተባለበትም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "አባ ወአቡየ ግብር ዘወሀብከኒ ፈጸምኩ" እኔ ልሠራው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጸሜ በምድር ላይ አከበርሁህ" ያለውን ከቅዳሴ በኋላ ሊቃውንት በዚህ ቀን ስለሚዘምሩት ነው። (ዮሐንስ 17:4)

#እንኳን ለዳግማ ትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን

መልካም በዓል🙏

✝️✝️✝️  #ማዕዶት ✝️✝️✝️ቅድስት እናት ኦርቶዶክስ ተወሕዶ ቤተክርስትያን ዕለትና ቀን አበጅታ ሰርታ ከቤተመቅደሱ እስከ ደጀ ሰላሙ ድረስ ኢየሱስ ክርስቶስን የምትመስለው ዕምነት ሐይማኖታ...
13/04/2026

✝️✝️✝️ #ማዕዶት ✝️✝️✝️

ቅድስት እናት ኦርቶዶክስ ተወሕዶ ቤተክርስትያን ዕለትና ቀን አበጅታ ሰርታ ከቤተመቅደሱ እስከ ደጀ ሰላሙ ድረስ ኢየሱስ ክርስቶስን የምትመስለው ዕምነት ሐይማኖታችን ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ናት በእውነት እችን ቤተክርስትያን የሰጠን አምላካችን ልዑል ቅዱስ እግዚአብሔር አምላክ የተመሰገነ የተወደሰ የተከበረ የተቀደሰ ይሁን ዕምነት ሐይማኖታችንን ከሚያስተን ነጣቂ ሁሉ ይጠብቀን ከአቅማችን ከማንችለው መከራ ፈተና ውስጥ አይክተተን፣

=>ማዕዶት ማለት (ዐደወ-ተሻገረ) ከሚል የግእዝ ግስ የተወረሰ ሲሆን በጥሬው "መሻገር" ማለት ነው:: ይሕም በደመ ክርስቶስ ተቀድሰን: በትንሳኤውም ድኅነት ተደርጐልን መከራን: መርገምን: የኃጢአትን ባሕር: አንድም ባሕረ እሳትን መሻገራችንን ያመለክታል::

+ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ ደሙ
*ከባርነት ወደ ነጻነት
*ከጨለማ ወደ ብርሃን
*ከሞት ወደ ሕይወት
*ከኃጢአት ወደ ጽድቅ
*ከሲዖል ወደ ገነት

*ከገሐነመ እሳት ወደ መንግስተ ሰማያት
አዳምንና እኛን ልጆቹን አሸጋግሮናል::
+አባታችን አዳምና ልጆቹ ከሲዖል የወጡት በዕለተ ዐርብ በሠርክ ቢሆንም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዚሕ ዕለት እዲታሰብ ታዛለች::

+ጌታችን ምርኮን ማርኮ: ጥጦስ መንገድ ጠራጊ ሆኖለት ወደ ገነት ሲያስገባቸው ለድንግል ማርያም አሳይቷታል::

እመ አምላክም በፍጹም ልቧ ደስ ተሰኝታለች:: አዳምና ልጆቹ እመቤታችንን ከላይ ሆነው እጅ ነስተዋታል:: እርሷ የድኅነታቸው ምክንያት ናትና::

=>አማናዊው ብርሃን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ጨለማችንን በምሕረቱ ያብራልን::

=>+"+ ክርስቶስም እኮ ስለ ሰው ኃጢአት አንድ ጊዜ ሞቶአል:: ኃጢአት የሌለበት ክርስቶስ ጻድቁ ስለ እኛ ሞተ:: ስለ ኃጢአታችን እኛን ወደ እግዚአብሔር ያቀርበን ዘንድ::

በሥጋ ሞተ: በመንፈስ ግን ሕያው ነው:: ነፍሳቸው ታስራ ወደ ነበረችበት ሔደ:: ቀድሞ ክደውት ለነበሩት ነጻነትን ሰበከላቸው:: +"+ (1ዼጥ. 3:18)
>
አሜን አሜን አሜን 🙏🙏🙏

➕➕➕   ➕➕➕የጌታችን የአምላካችን የአዳኛችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ፦ ክርስቶስ አምላክ በተቀበረ በሶስተኛው ዕለት በመንፈቀ ለሊት ልክ በዝች ሰዓት ሲነሣ የመቃብር ጠባቂዎ...
12/04/2026

➕➕➕ ➕➕➕

የጌታችን የአምላካችን የአዳኛችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ፦ ክርስቶስ አምላክ በተቀበረ በሶስተኛው ዕለት በመንፈቀ ለሊት ልክ በዝች ሰዓት ሲነሣ የመቃብር ጠባቂዎች ደነገጡ በድንም ሆኑ። ክርስቶስን ከልደት እስከ መስቀል ሞት ድረስ በደካማነት መልክ እንደ ሰው ይመለከቱት ነበር ነገር ግን ትንሣኤው እፁብ አምላክነቱን አሸናፊነቱን አሳመነ ሞት በእርሱ ላይ ሥልጣን የለውምና ይዞም ሊያስቀረው አልቻለም።

በክርስቶስ ኢየሱስ ሞት ያዘኑት ሐዋርያት ቅዱሳት አንስትም ፀጥታ ሳያገኙ ሰንብተው ነበር በዚህ ቀን ግን በየበኩላቸው ወደ መቃብር እየሄዱ ከመቃብር አካሉን ስላጡ በበለጡ አዘኑ ሴቶች ደግሞ ከመመላለሳቸው የተነሣ መልእኩ እንዴት ሕያውን ከሙታን ጋር ትፈልጉታላችሁ እርሱ #ተነስቷል ከዚህ የለም የሚል የሚያስደስትም የሚያስደንቅም የሚያሳዝንም በቃል ሰምተው ተመለሱ። እያዘኑም ሲሄዱ ክርስቶስ ኢየሱስን በመንገድ አገኙት እጅም ነሱት ሰገዱለትም እርሱ ግን ሂዱና ለደቀመዛሙርቱ እንደተነሣሁ ንገሯቸው አላቸው።በክርስቶስ መነሣት በደቀ መዛሙርቱ በኩል ፍጹም ደስታ ሲሆን በሊቃነ ካሕናቱ በጻሕቱ በኩል ደግሞ ሀዘንና ፍርሃት ሆነ። ስለዚህም ትንሣኤው ለሕዝብ እንዳይነገር እኛ ተኝተን ሳለ ደቀ መዛሙርቱ መጥተው ወሰዱት ተብሎ እንዲነገር አስደረጉ እንዲሁም ከእርሱ ጋር እየወጣና እየወረደ እንደቀድሞው እየበላና እየጠጣ አርባ ቀን አብሯቸው ቆየ። በእውነት በሞቱ ሞትን የሻረልን ከድቅድቅ ጨለማ ከዳቢሎስ ከሰይጣን ስራ ነጻ ያወጣን የቅድስት ድንግል ማርያም ልጅ ሥለማይነገር ውብ እና ድንቅ ሥጦታው የተመሰገነ የከበረ የተወደሰ ይሁን፦

የሄዋን አምላክ ሙታንን ሊያስነሣ
በእኩለ ለሊት ክርስቶስ ተነሣ

➕➕➕    ➕➕➕ከጌታችን ከአባታችን ከአዳኛችን ከመድኃኒታችን ከአምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከስቅለቱ ብኋላ ያለው ይህ የዛሬዋ ቅዳሜ በተለያየ ስያሜ ይጠራል ይኸውም    ዐብይ ሰንበት ቅዱስ ...
11/04/2026

➕➕➕ ➕➕➕

ከጌታችን ከአባታችን ከአዳኛችን ከመድኃኒታችን ከአምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከስቅለቱ ብኋላ ያለው ይህ የዛሬዋ ቅዳሜ በተለያየ ስያሜ ይጠራል ይኸውም ዐብይ ሰንበት ቅዱስ ቅዳሜ እየተባለ ይጠራል፦

1ኛ/ ይባላል፦ ይህ ስያሜ ሰንበት በአይሁድ መሻሩን ያመለክታል

2ኛ/ ይባላል፦ ሰንበት እረፍት ማለት ስለሆነ ይህም ቀን ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ሁሉንም ሥራ ፈጽሞ በመቃብር አርፎበታልና ትልቁ ሰንበት ለማለት ተብሏል፦

3ኛ/ ይሉታል፦ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ጌታን አምላካችንን አዳኛችንን መድኃኒታችንን በአዲስ መቃብር ያኖሩት በማዘጋጀቱ ቀን አርብ ማታ ሰንበት ሊጀመር ሲል ነበር ቅዳሜም ከገባ ብኋላ እንደ ትዕዛዙ ሰንበት ስለሆነ አረፈ፦

ሐዋርያት ጌታችን አምላካችን አዳኛችን መድኃኒታችን ከተያዘ ጊዜ ጀምሮ እስከ ትንሣኤው ድረስ እህልም ውሃም አልቀመሱም ነበር በዚህ መሰረት ቅድስት በቤተክርስቲያናችን ⛪ ከአርብ ጀምሮ እስከ ትንሣኤ እህል አይበላም ይችንን አምላክን በምትመስለውን ዕምነት ቅድስት ተዋሕዶ ኦርቶዶክስ ሐይማኖት ውስጥ ያደረገን አምላክ እስከ ፍጻሜያችን አይለየን ይህም ከአርብ እስከ ትንሣኤ ድረስ ያለው ቀን አክፍሎት ተብሎ ይጠራል ሕዝቡ ከጾመው ምግብ ውኃ በካሕኑ በኩል ለድሆች ማካፈል እንደሚገባው ያመለክታል ጌታችን አምላካችን ሙሽራውን የሚወስድበት ጊዜ ይመጣል ያን ጊዜ ይጾማሉ ብሎ አስቀድሞ ተናግሯል፦

በዚህ ዕለት ሞት ወለደ እግዚአብሔር የምናስብበት ብርሃነ ትንሣኤውን የምንናፍቅበት ቀን መሆኑን አንዘንጋ ተዋሕዶ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ተሰብስበው ጸሎቱ ሲፈጸም "ገብረ ሰላመ በመስቀሉ" ከርስቶስ በመስቀሉ ሰላምን ፍቅርን ዕምነትን መሰረተ ሰላምን ፈጠረ የምሥራች ይባላሉ።
ለተሰበሰበው ሁሉ የምሥራች ምልክት የሚሆን ቄጤማ ይታደላል ክርስቲያን ምዕምናን ይህንን እየሰነጠቁ በእራስ ግንባራቸው ያስራሉ ወደ ቅድስት ቤተክርስቲያን ላልመጡ ደግሞ ካሕናት አባቶቻችን በየአጥቢያቸው በየበኩላቸው ልብሰ ተክኗቸውን ለብሰው መስቀልና ቃጭል ይዘው እያጠኑ በየቤቱ የምሥራች እያሉ ይሰጣሉ በእውነት እችንን አምላክን ክርስቶስን እናቱን ቅድስት ድንግል ማርያምን የምትመስለውን እናት ቤተክርስቲያንን የሰጠን አምላካችን ክብር ምሥጋና ይግባው በምንም መከራ ስቃይ ችግር ሞት ግድያ ስደት መፈናቃል እርሃብ ጥም ውስጥ ብንሆንም በሞቱ ሞትን ድል አድርጎ የሰጠን አምላካችን እርሱ ከላይ ከጸባዎት ሆኖ ሁሉንም ይመልከትልን ይሄንን የመከራ ጊዜን በቃችው ይበለን እንደ ምህረቱ እንደ ቸርነቱ ኅጥያታችንን ይተውልን በይቅርታው ይቅር ይበለን መልካም የትንሣኤ ዋዜማ ምሽት ይሁንልን! አሜን አሜን አሜን

➕➕➕ ሕማማተ  #ሥቅለት ➕➕➕ይህ ትልቅ ዕለት መሥዋዕት የተከፈለልን ቀን ከሲኦል እስራት ነጻ የወጣንበት የእዳ ደብዳቤያችን የተቀደደበት የሥላሴን ምስጢር ያወቅንበት እነኋት እናትህ ተብለን ...
10/04/2026

➕➕➕ ሕማማተ #ሥቅለት ➕➕➕

ይህ ትልቅ ዕለት መሥዋዕት የተከፈለልን ቀን ከሲኦል እስራት ነጻ የወጣንበት የእዳ ደብዳቤያችን የተቀደደበት የሥላሴን ምስጢር ያወቅንበት እነኋት እናትህ ተብለን በቅዱስ መሥቀሉ ሥር ቤዛዊት ዓለምን እመ ብርኅሃንን እመ ብዙኅንን ኪዳነምህረትን ቅድስት ድንግል ማርያምን እናት እንድትሆነን በቅዱስ ዮሐንስ ሥም የተቀበልንበት ከቅዱስ እግዚአብሔር አምላክ የታረቅንበት በቅዱስ መሥቀሉ የዳንበት በመሥቀሉ ከቅዱሣኑ ጋር የተገናኘንበት በመሥቀሉ ላይ በተቆረሰው ሥጋ በፈሠሰው ደሙ ከበደላችን የዳንበት የነጻንበት በመሥቀሉ ለዘለዓለም ፍጹማን የሆንበት ዕለት #ሥቅለቱ እንኳን አደረሣችሁ አደረሰን ሣይገባን ለዚህ ቀን ዕለት ዓመት ያደረሰን አምላካችን መድኃኒታችን መድኃኔዓለም ሥለማይነገረው ሥጦታው ሁሉ የተመሰገነ የተከበረ የተወደሰ ይሁን፦

እውነተኛ ፍቅርህን ቀምሻለሁ
የቆሰሉ እጆችህን አይቻለሁ
የተወጋ ጎንህንም ዳስሻለሁ
ስለዚህም ጌታዬ አምላኬ ብዬሃለሁ
ጌታዬ አምላኬ እልኃለሁ 😭😭

ጌታችን አምላካችን አባታችን መድኃኒታችን እኛን ለማዳን በመሥቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈጸሙ ሰባቱ ተአምራቶች፦
1ኛ/ ፀሐይ ጨለመች
2ኛ/ ጨረቃ ደም ሆነች
3ኛ/ ከዋክብት ብርሃናቸውን ነሱ
4ኛ/ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ለሁለት ተከፈለ
5ኛ/ ዐለቶች ተሰነጣጠቁ
6ኛ/ መቃብራት ተከፈቱ
7ኛ/ የሞቱት ተነሡ

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቸነከሩበት ቦታዎች:-
1/ ሳዶር= ቀኝ እጁን የቸነከሩት
2/አላዶር= ግራ እጁን የቸነከሩት
3/ ሮዳስ= ከወገቡ (እምብርቱን) አጥብቆ እንዲይዘው የቸነከሩት
4/ ዳናት= እግሮቹን የቸነከሩት
5/= አዴራ= ደረቱን አጥብቀው የቸነከሩበት:- እነዚህ አካሎቻችን እንኳን በሚስማር ተቸንክረው ጥፍራችን ሲያመን የሚሰማንን ስሜት እናውቀዋለን ጌታችን መድኀኒታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ስለእኛ ፍቅር እንዲህ ሆነ እንደምን ያለ ፍቅር ነው,,,,,,,,,,,,

"ሞቱን በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመሥል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን"

አምላካችን አዳኛችን አባታችን ጌታችን መድኃኒታችን የድንግል ማርያም ልጅ ለእኛ ለልጆችህ ስትል እንዲህ ባለ ሞት እራስህን መሥዋት አድርገህ ሰዋሕልን #ያመናችሁ ሁኑ እንጂ ያላመናችሁ አትሁኑ ያልከንን ቃል እንድናከብር በቅድስት እናትህ ድንግል ማርያም በቅዱሣን በጻድቃን ሰማዕታት መላእክት ብለህ ይሄንን የመከራ የሥቃይ የዋይታ የስደት የግድያ የርሃብ የጥም ዘመነንን አሳጥርልን ፍቅርን አብዛልን ትህትናን የተላበስን አድርገን በቅዱስ ስቅለተ ሞትህ ብለህ ከጥፋት አድነን ቅድስት እናት መሸሸጊያችን መጽናኛችንን ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን አንተ ጠብቅልን አጥሯን ሊደፍር የመጣውን ሁሉ ቅዱስ ሚካኤልን ልከህ በሰይፍ ይጣልልን በሞትክህ የሞትክለት ሰው አይሙት በደም የዋጀሃት እናት ቤተክርስቲያንን አስባት ሰላምህ ምህረትህ ቸርነትህ ይቅርታህ አይለየን፦ አሜን አሜን አሜን 😭😭😭👏👏👏 ✝️✝️✝️መስቀለ ኢየሱስ ክርስቶስ ✝️✝️✝️

➕➕➕ ህማማተ ጸሎተ ሐሙስ ➕➕➕ይህ ዕለተ ቀን በቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አስተምሮ   ይባላል ለተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ሁሉ እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን ሣይገባን...
09/04/2026

➕➕➕ ህማማተ ጸሎተ ሐሙስ ➕➕➕
ይህ ዕለተ ቀን በቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አስተምሮ ይባላል ለተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ሁሉ እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን ሣይገባን ለዚህ ያደረሰን አምላካችን ክብር ምስጋና ይግባው ፦
ይህ ታላቅ በዓል አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሥጋውን ቆርሶ ቅዱስ ደሙን አፍሥሶ ከባርነት ቀንበር ያሻገር ዕለት ነው ህብሥቱን ቆርሶ እንካችው ብሎ ጽዋውን አንሥቶ እንካችሁ ጠጡ ይህ ስለዕናንተ የሚፈሰው ደሜ ነው ብሎ የሰጠን ትልቅ የመዳናችን ምክንያት የሆነ በዓል ነው በመቀጠልም ደቀ መዛሙርቱን የሰማይ የምድር አምላክ ገዢ ዝቅ ብሎ የደቀ መዛሙርቱ እግር ያጠበበት የትህትና ቀን ነው ትህትና ባለቤት ገንዘቡ የሆነ አምላክ እኛም እንድንዋደድ እንዲ እንድንፋቃር ያስተማረን ታላቅ ቀን ዕለት ነው፦

በመሸም ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት ጋር በማዕድ ተቀመጠ ሲበሉም እውነት እላችኋለሁ ከእናንተ እኔን አንዱ አሣልፎ ይሰጣል አለ እጅግ አዝነው እያንዳንዱ ጌታ ሆይ እኔ እሆንን ይሉት ጀመር እርሱም መልሶ ከእኔ ጋር እጁን በወንጭት ያጠለቀ እኔን አሣልፎ የሚሰጥ እርሱ ነው የሰው ልጅስ ስለ እርሱ እንደ ተጻፈ ይሄዳል ነገር ግን የሰው ልጅ አልፎ ለሚሰጥበት ለዚያ ሰው ወዮለት ያ ሰው ባልተወለደ ይሻለው ነበር አለ አሣልፎ የሚሰጠው ይሁዳም መልሶ መምህር ሆይ እኔ እሆንን? አለ አንተ አልህ አለው፦ አሣልፎ እንደሚሰጠው እያወቀ ግን ዝም ብሎ ሄደ ልክ ዛሬ በእኛ ዘመን እንዳለነው ትውልድ ስንቶቻችንን ነን በስሙ እየነግድን እያታለልን እያጭበረበርን #የካድነው ያለነው? ስንቶቻችንን ነው ለገንዘብ ነገ ለሚያልቅ ንብረትና ዕቃ ዕምነታችንን ሐይማኖታችንን #የካድነው? ሥንቶቻችንን ነን አምላክ ያከበራትን ክብርት ቅድስት ድንግል ማርያምን ሥሟን መደበቂያ እያደረግን #እየከዳን እያንጓጠጥን እየተሣደብን ያለነው ሥንቶቻችንን ነን በቅዱስ መንበሩ ታቦቱ ፊት የተዳፈርነው #የካድነው ቅድስት ቤተክርስቲያን ውስጥ ሆነን መሥለን ገብተን እየበደልን #እየካድን ያለነው ቅዱስ ቅዱስ ብለው ያመሰገኑት ካህናት ዲያቆናትን የገደልነው የተዋህዶ ኦርቶዶክስ ልጆችንስ ያሣደድነው በተወለዱበት አካባቢ እየመዘንን መከራ ስቃይ የምናሣያቸው ወላድ እናቶች ሁለት ነፍሠጡር የሆኑትን ክርስቲያን አትወልዱም እያላን የገደልን ቅድስት ቤተክርስቲያንን #የካድነው ይሄ ዕለተ ይሄንን ሁሉ ያስተምረናል በእውነት እንድናገናዝብ ልቦና ሕሊናችንን ይመልሥልን፦

ሲበሉም ኢየሱስ ክርስቶስም እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቆርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና እንካችሁ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው አለ ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈሥ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው ነገር ግን እላችኋለሁ በአባቴ መንግሥት ከእናንተ ጋር ከዚህ ከወይን ፍሬ አዲሱን እስከምጠጣበት እስከዚያ ቀን ድረስ ከዛሬ ጀምሬ አልጠጣውም፦

መዝሙርም ከዘመሩ ብኋላ ወደ ደብረ ዘይት ወጡ በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ክርስቶስ በዚች ለሊት ሁላችሁ በእኔ ትሰናከላላችሁ እረኛውን እመታለሁ የመንጋውም በጎች ይበተናሉ የሚል ተጽፎአልና ከተነሣሁ ብኋላ ግን ወደ ገሊላ እቀድማችኋለሁ አላቸው ጴጥሮስም መልሶ ሁሉም በአንተ ቢሰናከሉ እኔ ከቶ አልሰናከልም አለው ኢየሱስ ክርስቶስም መልሶ እውነት እልሃለሁ በዚች ለሊት ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ አለው ጴጥሮስም ከአንተ ጋር መሞት እንኳ የሚያስፈልገኝ ቢሆን ከቶ አልክድህም አለው ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ እንደዚሁ አሉ፦

በእውነት አምላካችንን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዕምነታችንን ሐይማኖታችንን እስከመቀየር እስከመካድ ከሚያደርስ ፈተና መከራ ውስጥ አይክተተን አስተውለን እንድንጓዝ በክርስቶስ ኢየሱስ በመሰረታት ዕምነት ጸንተን ለመኖር ያብቃን ይሄን ዕለት አዘጋጅታና አክብራ የሰጠችን ቅድስት ቤተክርስቲያናችንን ይጠብቅልን መልካም በዓል ይሁንልን በያለንበት፦

አሜን አሜን አሜን!

➕➕➕ ህማማተ  #ረቡዕ ➕➕➕ሦስት ነገሮች የተፈጸሙበት ቀን:-ይህ ዕለት በቅድስት ቤተክርስቲያን አስተምሮ  #የምክር ቀን ይባላል ምክንያቱን የአይሁድ ሊቀ ካህናት ጻሐፍት ፈሪሳውያን ጌታ አም...
08/04/2026

➕➕➕ ህማማተ #ረቡዕ ➕➕➕
ሦስት ነገሮች የተፈጸሙበት ቀን:-

ይህ ዕለት በቅድስት ቤተክርስቲያን አስተምሮ #የምክር ቀን ይባላል ምክንያቱን የአይሁድ ሊቀ ካህናት ጻሐፍት ፈሪሳውያን ጌታ አምላከ ኢየሱስ ክርስቶስን እንዴት መያዝ እንደሚገባቸው ምክር የጀመሩበት ወይም የያዙበት ቀን ስለሆነ ነው በዚህ ምክራቸው ላይ በጣም ትልቅ ጭንቀት ነበር ምክንያቱም የእነሱ የፋሲካ( የቂጣ) በዓላቸው የሚያከብሩበት በመሆኑ ብዙ ሕዝብም በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርት የተማሩ ተአምራቱን የሚያደንቁ ስለነበር ኹከት እንዳይፈጠር ነው ዕውነተኛ #ፋሲካቸው በመካከላቸው ሆኖ እነርሱ ግን እራሳቸው ፋሲካ ብለው ለራሳቸው ስም ሰተው ያከብራሉ ልክ ዛሬ በእኛ የትውልድ ዘመን እንዳለንበት አንዳንዶቹ በክርስቶስ ስም ሲነግዱ አንዳንዶቹ ደግሞ ቅድስት እናቱን ድንግል ማርያም አንተርሰው ይቀልዳሉ በያራሳቸው ቀን እና ዕለት እየተረጎሙ የእኛ ፋሲካ ይላሉ ልክ እንደ አይሁድ ካህናትና ጻህፍት ፈሪሳውያን በእውነት ለእርሱ እንድንገዛ ልቦናችንን ያብራል በዚህ ጭንቀት ሣሉ ከደቀ መዛሙርርምቱ አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ በመካከላቸው በመገኘት የምክራቸው ተባባሪ ሆኖ ጭንቀታቸውን አስወገደላቸው ሠይጣን ዳቢሎስ የሰውን ልጅ ሲቆጣጠረው እንደዚህ ለገንዘብ ለተራ ነገር አምላኩን ዕምነቱን ሐይማኖቱን ይሸጣል፦

ኢየሱስ ክርስቶስም እነዚህን ቃሎች ሁሉ በፈጸመ ጊዜ ለደቀ መዛሙርቱ ከሁለት ቀን ብኋላ ፋሲካ እንደሆነ ታውቃላችሁ የሰው ልጅም ሊሰቀል አልፎ ይሰጣል አለ አሳልፎ የሚሰጠው በመካከሉ አለና ይሄንን ተናገረ በዚያን ጊዜ የካህናት አለቆች የህዝብም ሽማግሌዎች ቀያፋ በሚባለው በሊቀ ካህናቱ ግቢ ተሰበሰቡ ኢየሱስንም በተንኮል ሊያሲዙት ሊገድሉትም ተማከሩ ነገር ግን በህዝቡ ዘንድ ሁከት እንዳይነሣ በበዓል አይሁን አሉ፦

የድንግል ማርያም ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስም በቢታንያ በለምጻሙ በስምዖን ቤት ሳለ አንዲት ሴት ዋጋው እጅግ የበዛ ሽቱ የሞላው የአልባስጥሮስ ብልቃጥ ይዛ ወደ እርሱ ቀረበች በማእድም ተቀምጦ ሳለ በራሱ ላይ አፈሰሰችው ደቀ መዛሙርቱም ይህን አይተው ተቀጡና ይህ ጥፋት ለምንድር ነው? ይህ በብዙ ዋጋ ተሸጦ ለድሆች ሊሰጥ ይቻል ነበርና አሉ ኢየሱስ ክርስቶስም ይህን አውቆ እንዲ አላቸው መልካም ስራ ሠርታልኛለችና ሴቲቱን ስለምን ታዳክሙአታላችሁ? ድሆች ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ይኖራሉና እኔ ግን ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር አልኖርም እርስዋ ይህን ሽቱ በሰውነቴ ላይ አፍስሳ ለመቃብሬ አደረገች እውነት እላችኋለሁ ይህ ወንጌል በዓለን ሁሉ በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል ምን ያለ መታደል ነው ማንንም የማይንቅ አምላክ ይችህን ሴት እንደዚህ አከበራት በእውነት ከነሃጥያታችን የምትወደን አምላክ የማርያም መቅደላዊትን ዕምነት አድለን፦

በመቀጠልም በዚያን ጊዜ የአስቆሮቱ ይሁዳ የሚባለው ከአሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት አንዱ ወደ ካህናት አለቆች ሄዶ፦ ምን ልትሰጡኝ ትወዳላችሁ እኔም አሳልፌ እሰጣችኋለሁ? እነርሱም ሠላሳ ብር መዘኑለት ከዚያችም ሰዓት ጀምሮ አሳልፎ ሊሰጠው ምቹ ጊዜ ይሻ ነበር ያም ጊዜ እችህ የዛሬዋ እምናከብራት ረቡዕ ነበረች በእውነት ከእርኩስ መንፈስ ከሰይጣን ዳቢሎስ ይጠብቀን፦

አሜን አሜን አሜን!

➕➕➕ ህማማተ  #ማክሰኞ ➕➕➕+++የጥያቄና መልስ ዕለተ ማክሰኛ+++እምንጠይቀውንም እምንመልሰውንም እምንናገረውንም አተውለን እንናገር ዘንድ እግዚአብሔር አምላክ አስተዋይ የነቃ ልቦናን ከእው...
07/04/2026

➕➕➕ ህማማተ #ማክሰኞ ➕➕➕

+++የጥያቄና መልስ ዕለተ ማክሰኛ+++
እምንጠይቀውንም እምንመልሰውንም እምንናገረውንም አተውለን እንናገር ዘንድ እግዚአብሔር አምላክ አስተዋይ የነቃ ልቦናን ከእውነተኛ ክርስትና ጋር ይሥጠን፦

ወደ ቅዱስ መቅደሱም ገብቶ ሲያስተምር የካሕናት አለቆችና የሕዝብ ሽማግሌዎች ወደ እርሱ አምላክ ቀገቡና በምን ሥልጣን እነዚህን ታደርጋለህ? ይሄንንስ ሥልጣን ማን ሰጠህ? አሉት ኢየሱስ ክርስቶስም መልሶ እኔ ደግሞ አንዲት ነገር እጠይቃችኋለው እናንተም ያቺን ብትነግሩኝ እኔ ደግሞ እነዚህን በምን ሥልጣን እንዳደርግ እነግራችኋለሁ የዮሐንስ ጥምቀት ከወዴት ነበረች? ከሰማይ ወይንስ ከሰው? አላቸው እነርሱም እርስ በራሳቸው ሲነጋገሩ ከሰማይ ብንል እንግዲያስ ስለምን አላመናችሁበትም? ይለናል ከሰው ነው ግን ብንል ዮሐንስን ሁሉም እንደ ነብይ ያዩታልና ሕዝቡን እንፈራለን አሉ ኢየሱስ ክርስቶስም መልሰው አናውቅም አሉት እርሱም ደግሞ እኔም በምን ሥልጣን እነዚህን እንዳደርግ አልነግራችሁም አላቸው፤

ዛሬም በእኛ ትውልድ ትውልድ ተፈጥሮን እንኳን አይተን መማር ሲገባን ሰውን እየተከተልን በሰው እንሰናከላለን የሰው ልጅ በደዌ በሽታ ታሞ ስሙ በመጠራበት በሚወደስበት በሚሰገድበት መስዋአት በሚቀርብበት በቅድስት ቤተክርስቲያን መተው በሥሙ በተቀደሰ ጠበል በስሙ በተጸለየ እምነት ሲድኑ ስናይ እሰይ እንኳን ደስ አለህ አለሽ እግዚአብሔር ይመስገን ከማለት ይልቅ እንዴት ወዴት ተረተረት እያለን እንከን እየፈለግን እንናገራለን እናወጣለን እናጓጥጣለን ልክ እንደ ጻሕፍት ፈሪሳውያን ሰዶቃውያን አይሁዳውያን እንሆናለን መመለስም መናገርም ሲያቅተን ስድብን እና አንድም እውቀት ሣይኖረን ከልክ በላይ እናወራለን እርሱን የሚያምኑ ለእርሱ የሚገዙ እርሱን የሚያከብሩ ቅዱሣንን ሁሉ ከፍ እና ዝቅ እያደረግን እንሣደባለን በእውነት በጣም ድፍረታችን ከልክ ያለፈ ነውና ልቦናችንን ይክፈትልን የትንቢት መፈጸሚያ አያድርገን ወደ ቀልባችን ይመልሰን፦ መልካም የበረከት የድሕነት የይቅርታ ጾም ያድርግልን ሐጥያትና ክፋታችንን ሣይመለከት በይቅርታው ኅጥያታችንን ይተውልን፤

አሜን አሜን አሜን! 🙏🙏🙏

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Orthodox tewhado የእመብርሃን ልጅ Page posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share