24/10/2020
በድፍረት እንስበክ!
“ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በሚወርድበት ጊዜ ኀይልን ትቀበላላችሁ፤ በኢየሩሳሌም፣ በይሁዳና በሰማርያ ሁሉ፣ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ።”” ሐዋርያት 1፥8
ኢየሱስ ክርስቶስ መንገድ፣ እውነትና ሕይወት ነው። በእርሱ በኩል ካልሆነ በቀር ወደ አብ የምንደርስበት መንገድ የለም። ስለዚህ በዚህ እውነት በመተማመን የመስበክ ኃላፊነታችንን እንወጣ። የእርሱንም ስም በምናውጅበት ጊዜ ሊደርስብን የሚችለውን ስደት አንፍራ።
፪ጢሞ.3:12 እንዲህ ይላል፤ “በርግጥም በክርስቶስ ኢየሱስ በእውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወት መኖር የሚወዱ ሁሉ ይሰደዳሉ።” የቀደሙት ሐዋሪያት የኢየሱስን ስም ፈጽመው እንዳያውጁ ተገርፈዋል፣ ዛቻና ማስፈራሪያም ደርሶባቸዋል። ነገር ግን እምነት ለሌላቸው ለኃይማኖታዊና ለመንግሥት ባለሥልጣናት እጅ ከመስጠት ይልቅ በላቀ ድፍረት ክርስቶስን ሰበኩ። መላ ኢየሩሳሌምንም በትምህርታቸው ሞልዋት (ሐዋ.5:28)።
የወንጌልን ስርጭት ለማክሸፍ የሚሠራ የክርስቶስ ተቃዋሚ መንፈስ ዛሬም በዓለም ላይ አለ። ነገር ግን ይህ ለእኛ ግድ ሊለን አይገባም። ምክንያቱም እኛ በክርስቶስ ቀድመን አሸንፈናል። “ልጆች ሆይ፤ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ፤ እነርሱንም አሸንፋችኋቸዋል፤ ምክንያቱም በእናንተ ውስጥ ያለው በዓለም ካለው ይበልጣል” (1ኛ ዮሐንስ 4፥4)።
ለክርስቶስ ካለው ፍቅርና ለወንጌል ካለው መሰጠት የተነሳ ለምንም ነገር ወደ ኋላ የማይለውን የሐዋርያው ጳውሎስን አርዓያ እንከተል። እርሱ በሐዋ.20:22-24 ላይ እንዲህ ብሏል፤“አሁንም እዚያ ስደርስ የሚደርስብኝን ባላውቅም፣ መንፈስ ቅዱስ ወደ ኢየሩሳሌም እንድሄድ ግድ እያለኝ ነው። ነገር ግን በምሄድባቸው ከተሞች ሁሉ እስራትና መከራ እንደሚጠብቀኝ መንፈስ ቅዱስ ይመሰክርልኛል። ይሁን እንጂ ከጌታ ከኢየሱስ የተቀበልሁትን ሩጫዬንና የእግዚአብሔርን የጸጋ ወንጌል የመመስከር አገልግሎቴን ብፈጽም፣ ለእኔ ሕይወቴ ከምንም እንደማይቈጠር እንደ ከንቱ ነገር ናት"።
እንዲህ ዓይነት ጽኑ እምነት ይኑረን። ይህ ለእኛ ታምኖ የተሰጠን ወንጌል ዋጋው እጅግ የከበረ ነው። ስለዚህ በሁሉም ሥፍራ በድፍረት እንስበከው።