ኢንሻ አላህ ለኢስላም መስዕዋት ለመሆን ዝግጁ ነኝ

ኢንሻ አላህ ለኢስላም መስዕዋት ለመሆን ዝግጁ ነኝ ለአለማችን ሰላም ማን እንደ ኢስላም። ኢስላም ትክክለኛው ሀይማኖት ለሰላም

20/06/2026

የእናቱን አስክሬን ቤት አስቀምጦ
ሚኒስትሪ የተፈተነው የ14 ዓመቱ ካሊድ

በሸገር ከተማ ኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ የሚኖረው የ14 ዓመቱ ታዳጊ ካሊድ፣ ለ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና ሲዘጋጅ እናቱ በድንገት በጽኑ ይታመማሉ። እናቱ ከመሞታቸው ጥቂት ሰዓታት በፊት “እኔ ምንም ብሆን የለፋህበትን ፈተና እንዳታቋርጥ” በማለት ለካሊድ ቃል ያስገቡታል። በሚያሳዝን ሁኔታ፣ ፈተናው ሊጀመር ጥቂት ሰዓታት ሲቀረው የእናቱ ሕይወት ያልፋል። ካሊድ በደረሰበት ከባድ ሐዘን ሳይሰበር፣ ለእናቱ የገባውን ቃል ለማክበር ሲል የእናቱን አስክሬን ቤት ውስጥ አስቀምጦ የጠዋቱን ፈተና ለመፈተን ወደ ትምህርት ቤት ያመራል።

የጠዋቱን ፈተና አጠናቆ ከተመለሰ በኋላ፣ ከሰዓት በልጅነት ዕድሜው ሊሸከሙት የሚከብደውን የእናቱን ለቅሶና ቀብር ሥነ-ሥርዓት ያከናውናል። ይሁን እንጂ ሐዘኑን ውጦና እንባውን አብሶ፣ የእናቱን የመጨረሻ ምኞት ሙሉ በሙሉ ለመፈጸም በዚያው ዕለት ከሰዓት በኋላ ወደ ፈተናው አዳራሽ በመመለስ የቀረውን ፈተና ተፈትኗል። የዚህ ታዳጊ አስደናቂ ጥንካሬ፣ ጽናትና ለእናቱ የነበረው ታማኝነት የብዙዎችን ልብ የነካና ያስለቀሰ ታሪክ ሆኖ አልፏል።

Dagu journal-

#ኢትዮጵያ

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

20/06/2026
ለአላህ ብሎ መዋደድ ሙስሊሞች እንደ ማህበረሰብ ብሎም እንደ ኡማ ጥንካሬያቸውንና የተሟላ ማንነታቸውን አስጠብቀው ዘውታሪ ወደሆነ ስኬትና ሀሴት መዝለቅ እንዲችሉ ሊከተሏቸው የሚገቡ መርሆዎች አ...
24/05/2026

ለአላህ ብሎ መዋደድ

ሙስሊሞች እንደ ማህበረሰብ ብሎም እንደ ኡማ ጥንካሬያቸውንና የተሟላ ማንነታቸውን አስጠብቀው ዘውታሪ ወደሆነ ስኬትና ሀሴት መዝለቅ እንዲችሉ ሊከተሏቸው የሚገቡ መርሆዎች አሉ። ከነዚህ ወሳኝ መርሆዎች መካከል መልካም የሆነ የእርስ በርስ ትስስር እና መለኮታዊ መስፈርት ላይ የተገነባ ግንኙነት መሆኑ ግልጽ ነው። በተለይም የሙስሊሞች ህይወት ምንጭ ኢስላም እንደመሆኑ የህይወታቸው መልካም ዋስትና
ለአላህ ብለው መዋደዳቸው እና መረዳዳታቸው ነው።

በአላህ መንገድ ወንድማማችነት እጅግ የተቀደሠ የአላህ ሱብሃሁ ወተዓላ ስጦታ፣ አንፀባራቂ የሆነ የጌታ ሽልማት እና ታላቅ አምላካዊ ፀጋም ነው። ይህን ፀጋ ማንም ተራ ሰው አያገኘውም። የትኛውም ሰው በቀላሉ አይታደለውም። አላህ ሱብሀነሁ ወተዓላ ከባሮቹ መካከል እሱን አጥርተው ለሚገዙ የሚሠጠው ነው። ከወዳጆቹም መካከል ለመረጣቸው የሚያወርሰው እንጂ ሌላ አይደለም። ከፍጥረታቱም ውስጥ እጅግ ፅዱ
ልቦና ባላቸው ሰዎች ቀልብ ውስጥ ይህ ችሮታ ያኖረዋል።
አላህ ሱብሀነሁ ወተዓላ በሱረቱል ዓሊ ዒምራን
ላይ እንዲህ ይለናል
ﻭَﺍﻋْﺘَﺼِﻤُﻮﺍ ﺑِﺤَﺒْﻞِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺟَﻤِﻴﻌًﺎ ﻭَﻟَﺎ ﺗَﻔَﺮَّﻗُﻮﺍ
ﻭَﺍﺫْﻛُﺮُﻭﺍ ﻧِﻌْﻤَﺖَ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻋَﻠَﻴْﻜُﻢْ ﺇِﺫْ ﻛُﻨﺘُﻢْ ﺃَﻋْﺪَﺍﺀً
ﻓَﺄَﻟَّﻒَ ﺑَﻴْﻦَ ﻗُﻠُﻮﺑِﻜُﻢْ ﻓَﺄَﺻْﺒَﺤْﺘُﻢ ﺑِﻨِﻌْﻤَﺘِﻪِ
ﺇِﺧْﻮَﺍﻧًﺎ ﻭَﻛُﻨﺘُﻢْ ﻋَﻠَﻰٰ ﺷَﻔَﺎ ﺣُﻔْﺮَﺓٍ ﻣِّﻦَ ﺍﻟﻨَّﺎﺭِ
ﻓَﺄَﻧﻘَﺬَﻛُﻢ ﻣِّﻨْﻬَﺎ ۗ ﻛَﺬَٰﻟِﻚَ ﻳُﺒَﻴِّﻦُ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻟَﻜُﻢْ ﺁﻳَﺎﺗِﻪِ
ﻟَﻌَﻠَّﻜُﻢْ ﺗَﻬْﺘَﺪُﻭﻥَ

“የአላህንም (የማመን) ገመድ ሁላችሁም ያዙ። አትለያዩም። ጠበኞችም በነበራችሁ ጊዜ በእናንተ ላይ (የዋለውን) የአላህን ጸጋ አስታውሱ።በልቦቻችሁም መካከል አስማማ። በጸጋውም ወንድማማቾች ኾናችሁ። በእሳት ጉድጓድ አፋፍም ላይ ነበራችሁ። ከእርስዋም አዳናችሁ። እንደዚሁ ትመሩ ዘንድ አላህ ለእናንተ አንቀጾቹን ያብራራል።” (አል ኢምራን፤ 103)

ወንድማማችነት ኢስላማዊው የእምነት አመላከከት /ዐቂዳ/፣ የኢማን እና የአላህ ፍራቻ ውጤት ከሚያስተሣስር ማንኛውም ሙስሊም ጋር በጥብቅ የሚያቆራኝ ከውስጥ የሆነ ጥልቅ የመተዛዘን፣ የመዋደድ፣ የመካባበርና የመተማመን ስሜትን የሚያወርስ ኢማናዊ ጥንካሬ ነው። ይህ ወንድማዊ ስሜት እየጎለበተ ሲሄድ በአንድ አማኝ ልብ ውስጥ በጎ የሆነ ጥልቅ ስሜትን ይፈጥራል። መረዳዳትና ሌላውን ከራስ አስበልጦ መውደድ፣ ለሌላው መቆርቆር፣ መተዛዘን፣ ይቅር መባባል፣ በችግር ጊዜ መደራረስ፣ በድካም ጊዜ መተጋገዝና የመሣሰሉት.. ከበጎ ውጤቶቹ መካከል ከብዙ በጥቂቱ የሚጠቀሱ ናቸው። እውነተኛ የወንድማማችነት ስሜት በሰው ልጆች ነፍስ፣ ንብረትም ሆነ ክብር ላይ ከሚደርሰው ማንኛውም ጉዳት አንፃር የተቃዋሚነት አቋምም ለመያዝ ያስችላል። በአላህ መንገድ ወንድማማችነት ከኢማን ጋር እጅግ የተቆራኘ ባህሪ ነው። ከአላህ ፍራቻ ጋርም በእጅጉ የተዛመደ ነው። ያለ ኢማን ወንድማማችነት እንደማይኖር ሁሉ ያለ ወንድማማችነትም ኢማን የለም። ያለ አላህ ፍራቻ የልብ ጓደኝነት እንደማይኖር ሁሉ ያለ የልብ ጓደኝነትም የአላህ ፍራቻ የለም። በሌላ አነጋገር “በአላህ መንገድ ወንድማማችነት ኢማንን መሠረት ያደረገ ነው። ሰዎች ለወንድማማችነታቸው ትኩረት የማይሠጡ ከሆነ ኢማናቸው ያጠራጥራል።” እንደማለት ነው። እንዲሁም “ሰዎች አላህን ፍራቻ መሠረት አድርገው የልብ ጓደኛ መያዝ አለባቸው። የልብ ጓደኝነት ከሌለም የአላህ ፍራቻ የለም” ማለት ነው።

16/05/2026
16/05/2026

Address

Addis Ababa
ADDISABABA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኢንሻ አላህ ለኢስላም መስዕዋት ለመሆን ዝግጁ ነኝ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ኢንሻ አላህ ለኢስላም መስዕዋት ለመሆን ዝግጁ ነኝ:

Shortcuts

Share