ኢንሻ አላህ ለኢስላም መስዕዋት ለመሆን ዝግጁ ነኝ

ኢንሻ አላህ ለኢስላም መስዕዋት ለመሆን ዝግጁ ነኝ ለአለማችን ሰላም ማን እንደ ኢስላም። ኢስላም ትክክለኛው ሀይማኖት ለሰላም

ለአላህ ብሎ መዋደድ ሙስሊሞች እንደ ማህበረሰብ ብሎም እንደ ኡማ ጥንካሬያቸውንና የተሟላ ማንነታቸውን አስጠብቀው ዘውታሪ ወደሆነ ስኬትና ሀሴት መዝለቅ እንዲችሉ ሊከተሏቸው የሚገቡ መርሆዎች አ...
24/05/2026

ለአላህ ብሎ መዋደድ

ሙስሊሞች እንደ ማህበረሰብ ብሎም እንደ ኡማ ጥንካሬያቸውንና የተሟላ ማንነታቸውን አስጠብቀው ዘውታሪ ወደሆነ ስኬትና ሀሴት መዝለቅ እንዲችሉ ሊከተሏቸው የሚገቡ መርሆዎች አሉ። ከነዚህ ወሳኝ መርሆዎች መካከል መልካም የሆነ የእርስ በርስ ትስስር እና መለኮታዊ መስፈርት ላይ የተገነባ ግንኙነት መሆኑ ግልጽ ነው። በተለይም የሙስሊሞች ህይወት ምንጭ ኢስላም እንደመሆኑ የህይወታቸው መልካም ዋስትና
ለአላህ ብለው መዋደዳቸው እና መረዳዳታቸው ነው።

በአላህ መንገድ ወንድማማችነት እጅግ የተቀደሠ የአላህ ሱብሃሁ ወተዓላ ስጦታ፣ አንፀባራቂ የሆነ የጌታ ሽልማት እና ታላቅ አምላካዊ ፀጋም ነው። ይህን ፀጋ ማንም ተራ ሰው አያገኘውም። የትኛውም ሰው በቀላሉ አይታደለውም። አላህ ሱብሀነሁ ወተዓላ ከባሮቹ መካከል እሱን አጥርተው ለሚገዙ የሚሠጠው ነው። ከወዳጆቹም መካከል ለመረጣቸው የሚያወርሰው እንጂ ሌላ አይደለም። ከፍጥረታቱም ውስጥ እጅግ ፅዱ
ልቦና ባላቸው ሰዎች ቀልብ ውስጥ ይህ ችሮታ ያኖረዋል።
አላህ ሱብሀነሁ ወተዓላ በሱረቱል ዓሊ ዒምራን
ላይ እንዲህ ይለናል
ﻭَﺍﻋْﺘَﺼِﻤُﻮﺍ ﺑِﺤَﺒْﻞِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺟَﻤِﻴﻌًﺎ ﻭَﻟَﺎ ﺗَﻔَﺮَّﻗُﻮﺍ
ﻭَﺍﺫْﻛُﺮُﻭﺍ ﻧِﻌْﻤَﺖَ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻋَﻠَﻴْﻜُﻢْ ﺇِﺫْ ﻛُﻨﺘُﻢْ ﺃَﻋْﺪَﺍﺀً
ﻓَﺄَﻟَّﻒَ ﺑَﻴْﻦَ ﻗُﻠُﻮﺑِﻜُﻢْ ﻓَﺄَﺻْﺒَﺤْﺘُﻢ ﺑِﻨِﻌْﻤَﺘِﻪِ
ﺇِﺧْﻮَﺍﻧًﺎ ﻭَﻛُﻨﺘُﻢْ ﻋَﻠَﻰٰ ﺷَﻔَﺎ ﺣُﻔْﺮَﺓٍ ﻣِّﻦَ ﺍﻟﻨَّﺎﺭِ
ﻓَﺄَﻧﻘَﺬَﻛُﻢ ﻣِّﻨْﻬَﺎ ۗ ﻛَﺬَٰﻟِﻚَ ﻳُﺒَﻴِّﻦُ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻟَﻜُﻢْ ﺁﻳَﺎﺗِﻪِ
ﻟَﻌَﻠَّﻜُﻢْ ﺗَﻬْﺘَﺪُﻭﻥَ

“የአላህንም (የማመን) ገመድ ሁላችሁም ያዙ። አትለያዩም። ጠበኞችም በነበራችሁ ጊዜ በእናንተ ላይ (የዋለውን) የአላህን ጸጋ አስታውሱ።በልቦቻችሁም መካከል አስማማ። በጸጋውም ወንድማማቾች ኾናችሁ። በእሳት ጉድጓድ አፋፍም ላይ ነበራችሁ። ከእርስዋም አዳናችሁ። እንደዚሁ ትመሩ ዘንድ አላህ ለእናንተ አንቀጾቹን ያብራራል።” (አል ኢምራን፤ 103)

ወንድማማችነት ኢስላማዊው የእምነት አመላከከት /ዐቂዳ/፣ የኢማን እና የአላህ ፍራቻ ውጤት ከሚያስተሣስር ማንኛውም ሙስሊም ጋር በጥብቅ የሚያቆራኝ ከውስጥ የሆነ ጥልቅ የመተዛዘን፣ የመዋደድ፣ የመካባበርና የመተማመን ስሜትን የሚያወርስ ኢማናዊ ጥንካሬ ነው። ይህ ወንድማዊ ስሜት እየጎለበተ ሲሄድ በአንድ አማኝ ልብ ውስጥ በጎ የሆነ ጥልቅ ስሜትን ይፈጥራል። መረዳዳትና ሌላውን ከራስ አስበልጦ መውደድ፣ ለሌላው መቆርቆር፣ መተዛዘን፣ ይቅር መባባል፣ በችግር ጊዜ መደራረስ፣ በድካም ጊዜ መተጋገዝና የመሣሰሉት.. ከበጎ ውጤቶቹ መካከል ከብዙ በጥቂቱ የሚጠቀሱ ናቸው። እውነተኛ የወንድማማችነት ስሜት በሰው ልጆች ነፍስ፣ ንብረትም ሆነ ክብር ላይ ከሚደርሰው ማንኛውም ጉዳት አንፃር የተቃዋሚነት አቋምም ለመያዝ ያስችላል። በአላህ መንገድ ወንድማማችነት ከኢማን ጋር እጅግ የተቆራኘ ባህሪ ነው። ከአላህ ፍራቻ ጋርም በእጅጉ የተዛመደ ነው። ያለ ኢማን ወንድማማችነት እንደማይኖር ሁሉ ያለ ወንድማማችነትም ኢማን የለም። ያለ አላህ ፍራቻ የልብ ጓደኝነት እንደማይኖር ሁሉ ያለ የልብ ጓደኝነትም የአላህ ፍራቻ የለም። በሌላ አነጋገር “በአላህ መንገድ ወንድማማችነት ኢማንን መሠረት ያደረገ ነው። ሰዎች ለወንድማማችነታቸው ትኩረት የማይሠጡ ከሆነ ኢማናቸው ያጠራጥራል።” እንደማለት ነው። እንዲሁም “ሰዎች አላህን ፍራቻ መሠረት አድርገው የልብ ጓደኛ መያዝ አለባቸው። የልብ ጓደኝነት ከሌለም የአላህ ፍራቻ የለም” ማለት ነው።

16/05/2026
16/05/2026
24/03/2026

I am also convert to islam before 18 years ago

Converts to Islam

ከዕለታት አንድ ቀን የነብዩ ሙሃመድ (ሶ.ዐ.ወ) ባልደረባ የሆነው ታላቁ አብዱላህ ኢብኑ መስኡድ ለግብይት ወደ ሱቅ ባመራበት አጋጣሚ ገንዘቡ መሰረቁን ያስተውላል ። ከዚያም አንዲህ አለ ፡- ...
24/03/2026

ከዕለታት አንድ ቀን የነብዩ ሙሃመድ (ሶ.ዐ.ወ) ባልደረባ የሆነው ታላቁ አብዱላህ ኢብኑ መስኡድ ለግብይት ወደ ሱቅ ባመራበት አጋጣሚ ገንዘቡ መሰረቁን ያስተውላል ። ከዚያም አንዲህ አለ ፡- “ አምላኬ ሆይ ! ገንዘቤን የሰረቀው ግለሰብ ቸግሮት ከሆነ ባርክለት ፥ ከዚያ ውጭ ከሆነ ደግሞ ይህንን ወንጀል የመጨረሻው አድርግለት ” ።
==================================
ያ እንደ ምንጭ ውሃ ኮለል ብሎ የጠራ ትውልድ ሲታወሰኝ እደነቃለሁ ። የእነኛን መሰል ድንቅ ስብዕናዎች ንብረት የሚዘርፍ ሌባ እንኳን በምርቃት ነው የሚሸኘው ። ከሩቁ በሚተኮስ ዱዓ ከነበረበት አስከፊ የህይወት ዓለም ተላቆ እነርሱ ሰልጥነው ባለፉበት የህወት መድረሳ እንዲሻገር እገዛ ያደርጉለታል ። እዝነታቸው ከሃብት እና ንብረታቸው በላይ የነገሰ ነው ። ይቅር ባይነታቸው ጎትጓች ስሜታቸውን ድባቅ የመታ ነው ። < ገንዘቤን የሰረቀው ግለሰብ ቸግሮት ከሆነ > በማለት ብሩህተኛ (optimist) እይታቸው የቀደመ ነው ።የሰዎች በሃጥያት አረንቋ መዘፈቅ ጭንቀትን እንጂ ደስታን አያከናንባቸውም ። ይባስ ብሎ ሃጥያት በሰራው ግለሰብ ተጎጂዎቹ እነርሱ መሆናቸውን ከተገነዘቡ ሳይሆን ፍቅር ይቀናቸዋል ። የሚያሳስባቸው በእጃቸው ያለው ጥሪታቸውን ማጣታቸው ሳይሆን ከእጃቸው የጠፋውን ንብረት ያወደመው አካል የወደፊት እጣ ፈንታ ነው ። ቀዳሚ ጭንቀታቸውም እርሱ ነው ። ለሰው ውድመት እንጂ ለገንዘብ ውድመት እንቅልፍ አያጡም ። ተጎጂ ሆነው ሳለ እግራቸው እስከሚያብጥ ድረስ ለጎዳቸው አካል እውነተኛ ዱዓ ያደርጋሉ ። የሰው ልጅ ነፃ ሲወጣ መንፈሳቸው ታርጋለች ። የሰው ልጅ በሃጥያት አዘቅት ሲንሸራተት እራሳቸውን የችግሩ መንስኤ አድርገው የሚመለከቱበትን መነፅር ነው የሚያጠልቁት ። < ሃጥያቱ በዚሁ ይብቃው > እያሉ በማሰብ በእንቅልፍ እጦት ይሰቃያሉ ። ራሳቸውንም ተጠያቂ በማድረግ ለሌላው ሰው ወንጀል ይርዳሉ ።
እነኛ ሰዎች እንዲህ ነበሩ … አዎ እንዲያ ነበሩ !!!
------------------------------------------

https://www.facebook.com/share/19vy5Nrqxf/
08/03/2025

https://www.facebook.com/share/19vy5Nrqxf/

WANTED‼️
ግለሰቡ አዳማ እንደነበረ እና አዲስ አበባም በመምጣት ብርጭቆ አከባቢ እንደታየ እዚሁ ሶሻል ሚዲያ ላይ አነበብኩ ፣

ግለሰቡ ሆን ብሎ ለፈጠረውና በየጊዜው
የሃይማኖት ግጭት ለመፍጠር የሚያሳየው ትንኮሳና የአለም ፈርጡን ነብዬን የአላህ ሰላምና እዝነት በሳቸው ላይ ይስፈን በጠነ ባ አፉ መሳደብ የዘውትር ስራው ነው።

ይህን መታገስና ማሳለፍ በሰፊው ማህበረሰብና ስብስብ መካከል ትልቅ የሆነ ሽንቁር ይተዋል፣ ሀገርንም ዋጋ ያስከፍላል ፣ ይህን ግለሰብ ዋጋ መስጠት ብዙ አንደበቶችን መስመር ያሲዛል አየህ ያንንም ይህንንም ዝም በማለታችን ህግም ተቋም ዝም በማለታቸው ትልቁን ዋጋ እያስከፈለን ነው።

ይህን ግለሰብ አግኝቶ ዋጋ ማስከፈል የማይችል ተቋምም ሆነ ያለበትን የሚያውቅ ስብስብ ዝምታ እንደትብብር የሚቆጠር ነው።

የማህበረሰቡን ሰላም ሆነ የሀገር ደህንነት የሚያሳስባችሁ ከሆነ ግለሰቡ በየትኛው መልኩ ያዙት እንደሱና መሰል በካዮች መፈልፈያው ሜዳ ይታወቃልና አንድ በሉልን።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
Ethiopian Federal Police

01/03/2025

አህለን ያ ረመዳን!

እንኳን ለ1446ኛው የታላቁ የረመዳን ወር በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!

የአላህ እዝነቱ ሆኖ ለተከበረው የረመዳን ወር ፆም ደርሰናል። በነገው እለት ቅዳሜ የካቲት 22 የረመዳን ወር ፆምን አንድ ብለን እንጀምራለን:: ይህ ትልቅ እድል በእኛ አቅም ሳይሆን በአላህ መልካም ፈቃድ መሆኑን አውቀን ሁላችንም ምስጋና ማድረስ ይኖርብናል… አልሐምዱሊላህ!

ከረመዳን እስከ ረመዳን በአለማችንም በሀገራችንም ብዙ ጉዳዮች ተስተናግደዋል። በሰው ልጆች ላይ በጎ ለውጥን ያመጡ፣ ተስፋን የሰጡ ሂደቶች አልፈዋል። በተቃራኒው ደግሞ የሰው ልጆችን ህይወት ያከበዱ፣ እርስ በእርሳቸው ያጋጩና ነገን ተስፋ ማድረግ ከባድ እንዲመስል ያደረጉ ሂደቶችም አልፈዋል። ሀገራችንም ከዚሁ የተለየች አይደለችም።

የአላህ ማስጠንቀቂያ ደወል የሆነው የመሬት መንቀጥቀጥ በሀገራችን ባልተለመደ መልኩ እጅግ የተደጋገመበትን፣ በጦርነት ብዙዎች የተፈናቀሉበትን እና ህይወታቸውን ያጡበትን ሁኔታ እያስተናገድን ይህን የእዝነት ወር ለመቀበል ከደጃፉ ደርሰናል።

ታላቁ የረመዳን ወር ወደ አላህ የምንቃረብበት፣ ከጌታችን ማርታን፣ እዝነትን እና ችሮታን የምንከጅልበት ወር ነው። ከጌታችን እዝነትን ስንከጅል ደግሞ እኛም የአላህ መልእክተኛ (ሰዐወ) እንዳስተማሩን ሁሉ ይበልጥ ቸር እና ለጋስ መሆን፣ በተፈጥሮ አደጋና ሰው ሰራሽ ግጭቶች ከቀያቸው ተፈናቅለው የሚገኙ ወገኖቻችንን በኢፍጣርና ሱሁር ማሰብ፣ በቻልነው ከጎናቸው መሆን ይጠበቅብናል። ምክንያቱም ረመዳን የእዝነት እና የመረዳዳት ወር ነው። ወሩን በኸይር ስራ ማሳለፍም እስላማዊ ግዴታችን ነው።

የወንጀሎቻችን ክምር ተንዶ ምድሪቱን ሳያጠፋ ወደ ጌታችን አላህ ይበልጥ ምህረትን በመለመን ወደሱ ለመመለስ ከዚህ ውድ የረመዳን ወር የተሻለ ዕድል አይገኝም። በመሆኑም በሀገራችንም ሆነ በመላው አለም እየደረሰ ላለው እልቂት፣ መጠፋፋትና መገፋፋት የማብቂያው በር እንዲከፈት አላህን አብዝተን የምንለምንበት ወር ሊሆን ይገባል። ሰላምና አብሮነትን፣ መከባበርን እና መተጋገዝን የምንጎናፀፍበት ወር እንዲሆን አላህን ይበልጥ በመማጸን አደራ ልንባባል ይገባል።

እናም ከባለፈው ዓመት ረመዳን ወደዛሬ ያሻገርናቸውን በጎ ፀጋዎች ጠብቀን፣ በዚህ ረመዳን የሚኖሩንን የፆምና ኢባዳ እድሎች እንደ ትልቅ እድል ተጠቅመን የምናሳልፍው የፆም ወር እንዲሆንልን እመኛለሁ!

በድጋሚ ረመዳን ሙባረክ!
ኡስታዝ አቡበክር አህመድ
ሻዕባን 29/1446

Address

Addis Ababa
ADDISABABA

Telephone

+251946241674

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኢንሻ አላህ ለኢስላም መስዕዋት ለመሆን ዝግጁ ነኝ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ኢንሻ አላህ ለኢስላም መስዕዋት ለመሆን ዝግጁ ነኝ:

Share