የክርስቲያን ድምጽ

የክርስቲያን ድምጽ " ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም "
(የማቴዎስ ወንጌል 4:4)

------   የወንጌል ባላደራነት  ----የወንጌል ባላደራነትን ለመወጣት በመጀመሪያ ማንነታችንን ማወቅ ያስፈልጋል። ማወቅ መሰረታዊ ነገር ነው። ሰው የሚያምነው የሚያውቀን ያህል ነው። ሮሜ ...
19/02/2024

------ የወንጌል ባላደራነት ----

የወንጌል ባላደራነትን ለመወጣት በመጀመሪያ ማንነታችንን ማወቅ ያስፈልጋል። ማወቅ መሰረታዊ ነገር ነው። ሰው የሚያምነው የሚያውቀን ያህል ነው። ሮሜ 10:14

ከየት መጥሁ? ለምን መጣሁ? ወዴት እሄዳለሁ? ብልን እንጠይቅ

ማን ነበርኩ?

በአዳም አለመታዘዝ ምክንያት ከአግዚአብሔር የተለየሁ (ኤፌ 2:1) ፣ አጢአተኛ ነበርኩ (ሮሜ 3:23፣) የሰይጣን ልጅ ነበርኩ (ዮሐ 8:44)

በዚህ ምክንያት የነበረኝ States ወይም ቦታ፥-

1) የሰይጣን ባሪያ ነበርኩ ዮሐ 8:44

2) ጣዖትን አምላኪ ነበርኩ መንፈሳዊ ችግር (ዘጸ 20:4-5)

3) የአእምሮ ችግር ያለበት ሰው ነበርኩ ጭንቀት፣ ፍርሃት፣ ስጋት ወዘተ (ማቴ 11:21)

4) አካላዊ ችግር የነበረብኝ ነበርኩ-ቤተሰብ ችግር፣ ከአጋንንት የሚላክ በሽታ (ሐዋ 8: 4-8)

5) ከሞት በኋላ የዘላለም ሞት የተገባኝ የተፈረደብኝ ነበርኩ ሉቃ 16: 19-31 ዕብ 9:27

6) ከዘር የሚተላለፍ መንፈስ ወይም መርገም ወስጥ ነበርኩ (ማቴ 27:25)

ሰው ከዚህ ችግር ለመውጣት የራሱን ዘዴ ሞክሯል ግን አልሆነም። የሞከራቸው ነገሮች በጥቂቱ

1) ሀይማኖት፥- የሰው ሰርዓት፣ ደንብ፣ ወግ፣ ህግ (ማቴ 12:43-45)
2) መልካም ስራ (ኢሳ 64:6)
3) ፍልስፍና (ቆላ 2:8)

ይሄ ሁሉ ግን ሰውን ሊያድን አልቻለም ስለዚህም እግዚአብሔር ለእኛ የተገለጠው የድነት መንገድ፥-

1) ወደደን (ዮሐ 3:16)

2) ክርስቶስ ስለ እኛ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሞተ (ሮሜ 5:8)

3) መንገድ እውነት ሕይወት ሆነልን (ዮሐ 14:6)

4) ደም አፍስሶ አስታረቀን (ሮሚር 8:2)

5) ከሰይጣን እስራት አውጥቶ ስልጣን ሰጠን (1ዮሐ 3:8)

6) ይህ ሁሉ መስዋእትነት የተከፈለበት ቢሆንም እንዲሁ በጸጋውና በእምነት መዳን ሆነልን (ኤፌ 2:8-9)

አሁን እኛ ጌታ ያደረገልንን ያመንን

1) መንፈስ ቅዱስን ተቀበልን (1ቆሮ 2:12)

2) የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ቤተመቅደስ ሆንን 1ቆሮ 3:16

3) በመንፈስ ቅዱስ መመራትን አገኘን ዮሐ 14: 16-17

4) በመንፈስ ቅዱስ ተሞላን ሐዋ 1:8

5) የልጅነት ስልጣን አገኘን ዮሐ 1:12

6) የሰይጣንን ስራ የማፍረስ ስልጣን አገኘን ሉቃ 10:19

7) የመልአክቶች ጥበቃ አገኘን ዕብ 1:14

8) የሰማዊ ዜግነትን አገኘን ፊልጵ 3:20

9) ታላቁ ተልዕኮን በመፈጸም ዓለምን የማሸነፍ የመማረክ መብት አገኘን ማቴ 28: 18-20

10) ለጸሎታችን ምላሽ የማግኘት ስልጣን አገኝን ዮሐ 14:14, ማቴ 7:7-11, ኤር 33:3, ሉቃ 18:1-8

11) የአጢአት ይቅርታ አገኘን ሮሜ 8:1-2, 1ዮሐ 1:9

12) በየቀኑ በድል የመመላልስ የአሸናፊነት መብት አገኘን 1ቆሮ 10:13,

------ የፍቅር ዕዳ አለብን -----

ወንጌልን ባልሰብክ ወዮልኝ ያለው ጳውሎስ ይህ ገብቶት ነው። እውነተኛ ወንጌል ሲገባን ብቻ በረከታችንን እና ማንነታችንን እናውቃለን። በዚህ ጊዜ እንደ ጳውሎስ እውነተኛ ወንጌልን ለመስበክ የሕይወታችን ዋና እሴት እናደርገዋለን።

እግዚአብሔር ጸጋና ሀይሉን የልብ አይኖቻችንን የልብ ጆሮዋችንን ይክፈትልን። እኛ ያገኝነውን ሌሎቹም እንዲያገኙ ወንጌልን መስበክ ስራችን ይሁን።

“ የወንጌል ሰባኪነትን ሥራ አድርግ፥ አገልግሎትህን ፈጽም።”

— 2ኛ ጢሞቴዎስ 4፥5

ብሩካን ናችሁ!

“የእግዚአብሔርን መልካምነት እናያለን. . .”በዙሪያችን እየተፈጠረ ያለውን ማወቅ ራሳችንን ለመጠበቅ የሚጠቅም ቢሆንም፣ በፍርሃት እንዳንዋጥ መጠንቀቅ ይኖረብናል። ትኩረታችንን ግን ምን ላይ ...
10/06/2021

“የእግዚአብሔርን መልካምነት እናያለን. . .”

በዙሪያችን እየተፈጠረ ያለውን ማወቅ ራሳችንን ለመጠበቅ የሚጠቅም ቢሆንም፣ በፍርሃት እንዳንዋጥ መጠንቀቅ ይኖረብናል። ትኩረታችንን ግን ምን ላይ እንደሆነ ማስተዋል አለብን።

ዳዊት በመዝሙር 27 እኛ ያለንበት ዓይነት አደገኛ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ እንኳን “እግዚአብሔር ብርሃንኔና መድሀኒቴ ነው የሚያስፈራኝ ማነው” ሲል እናየዋለን። እንዲህ ዓይነት ንግግር በኛ ቋንቋ ‘ዘራፍ’ እንደማለት ነው።

ዳዊት በፍርሃት ተውጦ ሲዋጋ ወይንም ሲገስፅ አናየውም፥ ይልቁን ትኩረቱን ሁሉ በትክክለኛው ስፍራ አኖረ። ቁጥር 4 ላይ “እግዚአብሔርን አንዲት ነገር ለመንኩት እሷንም እሻለሁ . . . በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ፣ ደስ የሚያሰኘውንም አይ ዘንድ፣ መቅደሱንም እመለከት ዘንድ።" እነዚህ በደማቅ የተፃፉት ቃላት ትኩረት በሚለው ቃል ልንተካቸው እንችላለን። ዳዊት ፍርሀትን ያላስተናገደበት ምክንያት ትኩረቱን በዙሪያው በተፈጠረው ቀውስ ላይ ስላላደረገው ነው። ትኩረቱን በሙሉ በአምላኩ መልካምነትና ታማኝነት ላይ በማድረጉ ፍርሃትን መዋጋት ችሏል።


በዚህ ምክንያት ቁጥር 3 ላይ ልዩ ነገር ሲፈጠር እናያለን ". . . በድንኳኑም የእልልታ መሥዋዕትን ሰዋሁ፥ ለእግዚአብሔር እቀኛለሁ እዘምርለታለሁ”። ዳዊት በጠላቶቹ ተከብቦ ማምለክ ጀመረ፤ እግዚአብሔርን ያየ ሰው የሚሰጠው ምላሽ ይህ ነውና።

አምልኮ ሰማያትን ይከፍታል። ሰማያት ሲከፈቱልን የእግዚአብሔርን ፈቃድ እና አላማ የማየት ዕድል ይሰጠናል። ለዚህም ነው በቁጥር 13 ዳዊት “የእግዚአብሔርን ቸርነት በሕያዋን ምድር አይ ዘንድ አምናለሁ” የሚለው። ተስፋ በሚያስቆርጥ ጊዜ እንኳን ዳዊት በአምልኮ ስለነበር እግዚአብሔር ‘ፍጻሜና ተስፋ ይሰጠው ዘንድ የሰላም አሳብ’ እንዳለው ማየት ችሏል። ኤር 29:11

የሕይወት ተዛምዶ
በዚህ ወቅት ምን እንደምሰማ፣ እንዴት እንደምሰማና ምን ያህል እንደምሰማ እንዴት ልጠንቀቅ?

ፀሎት
ጌታ ሆይ፣ ከምንም እና ከማንም በላይ ቀልቤን እንድታቀና፣ ፍርሃት ሁሉ ከውስጤ እንዲወገድ እለምንሃለሁ። በእምነት መበርታት እንድችል ለእኔ፣ ለቤተሰቤ እና ለምድሬ ያለህን መልካም ሃሳብ እንድታሳየኝ እለምንሃለሁ።

“ከዚህም በኋላ ሞትና ጭንገፋ አይሆንበትም አለ።”  — 2ኛ ነገሥት 2፥21
30/05/2020

“ከዚህም በኋላ ሞትና ጭንገፋ አይሆንበትም አለ።”
— 2ኛ ነገሥት 2፥21

“በዚያም የሚቀመጥ፦ ታምሜአለሁ አይልም፥ በእርስዋም ለሚቀመጡ ሰዎች በደላቸው ይቅር ይባልላቸዋል።”  — ኢሳይያስ 33፥24
26/04/2020

“በዚያም የሚቀመጥ፦ ታምሜአለሁ አይልም፥ በእርስዋም ለሚቀመጡ ሰዎች በደላቸው ይቅር ይባልላቸዋል።”
— ኢሳይያስ 33፥24

“እነዚያ በሰረገላ እነዚያም በፈረስ ይታመናሉ፤ እኛ ግን በአምላካችን በእግዚአብሔር ስም ከፍ ከፍ እንላለን።”  — መዝሙር 20፥7
08/04/2020

“እነዚያ በሰረገላ እነዚያም በፈረስ ይታመናሉ፤ እኛ ግን በአምላካችን በእግዚአብሔር ስም ከፍ ከፍ እንላለን።”
— መዝሙር 20፥7

መዝሙር 46¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¹ አምላካችን መጠጊያችንና ኃይላችን፥ ባገኘን በታላቅ መከራም ረዳታችን ነው።² ስለዚህ ምድር ብትነዋወጥ፥ ተራሮችም ወደ ባሕር ልብ ቢወሰዱ አንፈራም።³ ውኆቻቸው ጮ...
02/04/2020

መዝሙር 46
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ አምላካችን መጠጊያችንና ኃይላችን፥ ባገኘን በታላቅ መከራም ረዳታችን ነው።
² ስለዚህ ምድር ብትነዋወጥ፥ ተራሮችም ወደ ባሕር ልብ ቢወሰዱ አንፈራም።
³ ውኆቻቸው ጮኹ ተናወጡም፥ ተራሮችም ከኃይሉ የተነሣ ተናወጡ።
⁴ የወንዝ ፈሳሾች የእግዚአብሔርን ከተማ ደስ ያሰኛሉ፤ ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።
⁵ እግዚአብሔር በመካከልዋ ነው አትናወጥም፥ እግዚአብሔርም ፈጥኖ ይረዳታል።
⁶ አሕዛብ ተናወጡ መንግሥታትም ተመለሱ፤ እርሱ ቃሉን ሰጠ፥ ምድርም ተንቀጠቀጠች።
⁷ የሠራዊት ጌታ ከእኛ ጋር ነው፤ የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው።

አዲስ አመትን አዲስ የሚያሰኝው የኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ ነው ለናንተ ደግማ ሁሉንም ቀን እና አመት አዲስ ማድረግ የቻለውን ኢየሱስ ክርስቶስን የምትቀበሉበት አመት ይሁንላችሁ።   2012 ን...
11/09/2019

አዲስ አመትን አዲስ የሚያሰኝው የኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ ነው ለናንተ ደግማ ሁሉንም ቀን እና አመት አዲስ ማድረግ የቻለውን ኢየሱስ ክርስቶስን የምትቀበሉበት አመት ይሁንላችሁ።
2012 ን ከኢየሱስ ጋር አዲስ ያድርጉት
መልካም አዲስ ዓመት

የኔ አሳቢ ኢየሱስ ነው ።ጭንቀቴን የሚረዳኝ ። እንድጨነቅበት የማይፈልግ ።የኔ ጌታ ። እወድሃለሁ ።ከኔ በላይ ለኔ የሚያስብልኝ እርሱ ነው ።  እግዚአብሔር የተመሠገነ ይሁን።
26/08/2019

የኔ አሳቢ ኢየሱስ ነው ።ጭንቀቴን የሚረዳኝ ። እንድጨነቅበት የማይፈልግ ።የኔ ጌታ ። እወድሃለሁ ።
ከኔ በላይ ለኔ የሚያስብልኝ እርሱ ነው ።
እግዚአብሔር የተመሠገነ ይሁን።

30/05/2019

ጊዜው ይመችም አይመችም ዘመኑ ደግ ይሁንም ክፉ ሕይወታችንን እየቆረስንለት ጠዋትና ማታ የምናነሳው ባገኘነው አጋጣሚ ሁሉ የምናወራለት ከጓደኞቻችን ጋር የምንወያይበት ትልቅ ያልሆነ ግን ያተለቅነው ዋና ያደረግነው ነገር በሁላችንም ልብ ጓዳ መኖሪያውን ሰርቶ ሳናውቅ እደውሃ ይዞን እኛ ወደፈለግነው ሳይሆን እሱ ወደወደደው ይመራን ጀምሯል፡፡ መልካም ወይም እውነት ከሆነው ይልቅ ክፉ የሆነው ፈጥኖ ይጠመጠምብናል በቀላሉም ልናወርደው እንዳንችል አቅም እስክናጣ ድረስ ከኛ ጋር እንዲቆይና እንዲኖር ፈቅደንለታል፡፡ ዘመኑ አጭር ነው በጣም አጭርና የቀረንም ከጥቂት ያነሰ ነው እድል ካገኘንና ምቹም ይሁን ምቹ ያልሆነ አጋጣሚ ከተፈጠረልን ኢየሱስን እንስበክበት፡፡ ሁሉ ፖለቲከኛ ፤ ሁሉ ዘማሪ፤ ሁሉ አራሚ፤ ሁሉ ልክ ነኝ ባይ፤ ሁሉ ጠ/ሚንስትር ሊሆን አይችልም ለሁላችንም የተሰጠን ማድረግ የምንችለው ነገር ቢኖር ኢየሱስን መስበክ ነው፡፡ ጊዜው ደግሞ አሁን ነው!
# ኢየሱስን እንስበክ
@ ኢየሱስ ይመጣል!

Address

AYAT
Addis Ababa

Telephone

+251911901126

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የክርስቲያን ድምጽ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to የክርስቲያን ድምጽ:

Share