Quba Tube - ቁባ ትዩብ

Quba Tube - ቁባ ትዩብ እዚህ ድረስ ከመጡ በውዱ ላይ ሰለዋት ሳያወርዱ አይውጡ❤️፣ إن أتيت إلى هنا فلا تخرج قبل أن تصلي
على الغالي❤️ .https://heylink.me/qubatube/

اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا محمد وعلى آله وصحبه أجمعين . صلوا على الحبيب ❤️Link on the first Comment👇 ****************...
21/05/2026

اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا محمد وعلى آله وصحبه أجمعين . صلوا على الحبيب ❤️
Link on the first Comment👇
******************************************
❤️ #ሰላም

ይድረስ ለመላው ክርስቲያን ወገኖች**************************** ● ምን በደል ፈጸምን!? ይህ...ጸጥ ባለ ህመም ከሚሰቃይ ልብ የተነሳ - አክሱምም ሆነ በመላው ሀገሪቱ ላሉ ለ...
23/04/2026

ይድረስ ለመላው ክርስቲያን ወገኖች
****************************

● ምን በደል ፈጸምን!?

ይህ...ጸጥ ባለ ህመም ከሚሰቃይ ልብ የተነሳ - አክሱምም ሆነ በመላው ሀገሪቱ ላሉ ለእስልምና የከረረ ጥላ*ቻ ላላቸው ክርስቲያኖች ሁሉ የቀረበ ጥያቄ ነው፡-

● ምን በደል ፈጽምን?

እኛ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ፍሱም ሰላምን የምንፈልግ የሰላም ሰዎች ነን።እምነታችንን በውጫዊ መልኩ ከማሳየታችን በፊት በልባችን ውስጥ ይዘን ወደ ጌታችን እዝነት በር ለመቅረብ በአቅማችን ልክ የምንተጋ፣ ደፋ ቀና የምንል ይህችን አለም እንደ ጊዜያዊ መኖሪያ ቤት አድርገን የምናይ ሰዎች ነን።በትእዛዙ መሰረት ለእርሱ እንሰግዳለን፣እንጾማለን።

ምድር ላይ እስካለን ድረስ እዝነቱ ከእኛም አልፎ እናንተንም ጭምር እንዲያቅፍ፣ የእናንተም የእኛም የሆነችዋን ብቸኛዋን ሀገራችንን ዳር ድንበሯን ሰላም እንዲያደርግልን ቢያንስ በቀን አምስቴ እንለምናለን።

ታዲያ...

● ?

በእናንተ ላይ መሳሪያ አላነሳንም፣እናንተን ለመጉዳት አልሞከርንም።መብቶቻችሁን አልጣስንም ወይም እምነታችሁን እንዳትከተሉ አላገደንም።

እኛም እንደ ማንኛውም ቅን ኢትዮጵያዊ የቸገረውን ስናገኝ - ሙስሊም ነው ክርስቲያን- ሳንል የአቅማችንን እንረዳለን፣ የተራበውን እናበላለን፣የተጠማውን እናጠጣለን፣የተራቆተን እናለብሳለን።
ሀገራችን- ሀገራችሁ ኢትዮጵያ ስትፈልገን ላፍታ እንኳ ሳናመነታ "አቤት" ያልን ገንዘብ ጉልበታችን፣ ሲያስፈልግም ነፍሶቻችንን ሳንሰስት እንሰጣለን።

እስኪ ንገሩን ምን በደል ፈጸምን ነው...
አንዴ እምነታችንን፣አንዴ ከገዛ ወላጆቻችን-ነፍሶቻችን አብልጠን የምንወዳቸውን፣
ሌተ-ቀን "ምነው አንዴ እንኳ በህልሜም ቢሆን ባየኋችሀው" እያልን በናፍቆት የምናለቅስላቸውን ውዱን ነብያችንን፣ ሲያሻችሁ ማንነታችንን የምትሰድቡት!
ይህም ሳይበቃን በ #አክሱም እና በአንዳንድ ቦታዎች፣እጅግ መሠረታዊ የሆነውን መብታችንን የምትነፍጉን…
ጌታችንንም በሰላም የማምለክን፣ የመለመንን መብታችንን የምትነጥቁን!!።

በገዛ ላባችን ጥረን ግረን - አንዳንዴም ከእለት ጉርሻችን ላይ ቀንሰ - በምንገዛው፣ በምንገነባው የአሏህ ቤት(መስጂዳችን)፣ በሰላም እንዳንሰግድ...
እንዲሁም የጋራችን በሆነችዋ ምድራችን ኢትዮጵያ "ፈጣሪያችን ረጂያችን፣ጌታችን፣ ሰጪያችን ነው" ብለን ያመነውን አሏህን ዱዓእ(ጸሎት)ማድረግን ለምን ትቃወሙናላችሁ!?
በገዛ ሃይማኖታዊ ልምምዶቻችን ውስጥ ለመንገላታት ምን ስህተት ሠርተናል?

ከእናንተ ጋር በምንጋራው ምድር እንደ እንግዳ እንድታዩን የሚጋብዝ ምን ኃጢአት ሰርተናል?

እስከ መቼ በድርጊታችን ሳይሆን በማንነታችን የምትፈርዱብን!!!?

ሙስሊም ስለተኾነ ብቻ በጥርጣሬ መታየት
ምንም-ማንም ላይ ጉዳት ያላደረሱ እህት-ወንድሞቻችን ላይ ጥላቻ፣ስድብና ትንኮሳ መሰንዘርን እምነታችሁስ ይፈቅዳል!!?

ትክክል ነው ብላችሁ ወዳመናችሁት እምነትስ በዚህ መልኩ ነው እንድትጣሩ የሚያዛችሁ!!?

ታዲያ....

● ?

ከ አዕምሮ በፊት የነፍስን ስሜት እናስቀድም ከተባለ እንደ ሰውኛ እኛምኮ ምላስ አለን እንዲሳደብ ከፈለግን፣እኛም ጡንቻ አለን እንዲ*ማታ ከፈለግን፣እኛም ሀይል አለን ማስፈራራት፣መጨቆን ከፈለግን፣
ነገር ግን እምነታችን ሌሎችን እንድናከብር ለሙስሊምም ሆነ ለክርስቲያን ጥሩ ጎረቤት እንድንሆን፣የአብሮነትን ባህል እንድናከብር፣ለራሳችን የምንመኘውን መልካም ነገርን ሁሉ ለሌላውም እንድንመኝ
እና የራሳቸውን መንገድ የመምረጡ ሰዎችን እንዳንገፋ ስለሚያስተምረን፣
እና...
እንደ ሀገር እንደ ዜጋ ያሉብንን የጋራ ችግሮቻችንን ተባብረን ብንቀርፍ፣ከእኛ ወገንም ሆኑ ከእናንተ የተቸገሩትን ብንረዳ፣ የተራቡትን ብናበላ፣እንዲሁም እጅግና ጓንት ሆነን ሀገራችን #ኢትዮጵያን ወደተሻለ ደረጃ ከፍ ብናደርግ.. የተሻለ ስለሆነ እርሱ ላይ ትኩረት እናድርግ ብለን ነው።

ሙስሊም የሀሳብ ልዩነቶች ሲገጥሙት እንደ በሰለ ሰው ተቀራርቦ ሀሳቦቹን አቅርቦ በጥበብ መወያየት እና በሀሳብ ካልተስማሙት ጋር በፍትህ እና በርህራሄ ተቻችሎ እንዲኖር ከእምነቱ በፊት ህሊናው የሚያዘው ምእመን ነው።

ይህ ታዲያ እንዴት ለጥ*ላቻ ምክንያት ይሆናል?

● ?

እኛ ሙስሊሞች ከፍትህና ከእኩልነት በላይ የምንጠይቀው ከሌላው የተለየ ነገር የለንም።በእኩልነት ተከባብሮ መኖርን እንጂ ማንም ላይ መጫን አንፈልግም።

እና ውድ የሀገሬ - በተለይ ለእስልምና ጥራዝ ነጠቅ የሆነ አመለካከት ያላችሁ ወንድሞች እና እህቶች፣ እመኑኝ አክራሪነት ማህበረሰብን ያፈርሰዋል እንጂ አይገነባም።

ኢፍትሃዊነት ጥንካሬን አይፈጥርም። ኢፍትሃዊነት ሁላችንንም የሚጎዳ የጥላቻ ዘርን ከመትከል ውጪ ማናችንንም አይጠቅምም።

ዛሬ #አክሱም ላይ እየሆነ ያለው ነገር መላውን ሀገር ወዳድ - ሙስሊም እና የበሳል አስተሳሰብ አዕምሮ ባለቤት የሆኑ ቅን ክርስቲያን ወገኖች ልብን ጎድቷል፣ አሳዝኗል አዎ።!
ከማሳዘኑም በላይ ደግሞ ሁላችንም የሚያስፈልገንን አብሮ የመኖርን የወደፊት ሁኔታም አደጋ ላይ ይጥላል።
ስለሆነም ከኋላ ቀሩ ጭፍንነት ወጣ ብላችሁ በሰከነ አዕምሮ አስቡበት።
ገላን መሸፈን የክብር መገለጫ እንጂ የነውር አይደለም፣ ገላቸውን በመሸፈን የቅድስት ማርያምን ፈለግ የምትከተልን እንስት እንቅፋት አትሁኗት።

#በመጨረሻም!

የሰው ልጅ ከእንስሳ የሚለየው መሰረታዊው
ነገር አዕምሮ ነው። ለእራሱና ለማንነቱ ክብር የሚሰጥ፣ ይህን የተሰጠውን አዕምሮ በአግባቡ ይጠቀማል።
ስለዚህ ለራሳችን ክብር እንስጥ፣ ንቃተ-ህሊናችንን እናዳብር።

ወደ የጋራ ሰብአዊነታችን፣ወደ የጋራው ሀገራዊ ሰላምና ልማታችን እንመለስ…
ለእርስ በርሳችን በሰላም የመኖርን ጣእም አንምፈግ።

ወገኔ! ይህ ዓለም ለሁላችንም ሰፊ ነውና፣ ከመበዳደል ይልቅ ፍትህን፣ከጥላቻ ይልቅ ርህራሄን መርጠን ኑሯችን ለጊዜያዊ በሆነችው ምድር በሰላም እንኑር።

አሏህ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይጠብቅ።



Quba Tube - ቁባ ትዩብ

ሀሙስ/ሚያዝያ/15/2018

#ሰላም.

ሼር በማድረግ ለሁሉም ታደርሱልን ዘንድ በአሏህ ስም እንጠይቃለን.
*************************
#ሰላም ❤️ #አሏህ #ኢስላም #ሙስሊሙ #ኢስላምጠልነት #አክሱም

 !?🤔👇በአለም ደረጃ  #ዩንቨርስቲ የሚባለውን የትምህርት ስርዓት አስቀድመው የጀመሩት ሙስሊሞች እንደነበሩ ስንቶቻችን እናውቃለን!? 🕌 የአል-ቀረዊዪን ዩኒቨርሲቲ (ሞሮኮ) - በ859 ዓ.ል,...
26/03/2026

!?🤔👇
በአለም ደረጃ #ዩንቨርስቲ የሚባለውን የትምህርት ስርዓት አስቀድመው የጀመሩት ሙስሊሞች እንደነበሩ ስንቶቻችን እናውቃለን!?

🕌 የአል-ቀረዊዪን ዩኒቨርሲቲ (ሞሮኮ)

- በ859 ዓ.ል, በፋጢማ አል-ፊህሪ በትምህርት ዘርፍ አቅኚ ሴት የተመሠረተ ሲሆን፣ በዩኔስኮ እና በጊነስ ወርልድ ሪከርድስ በዓለም ላይ በተከታታይ የዲግሪ ሽልማት የሚሰጠው ጥንታዊና ቀደምት ዩኒቨርሲቲ እንደሆነ እውቅና ተሰጥቶታል።

- በታሪክ ለእስልምና ጥናቶች፣ለሂሳብ፣ ለህክምና እና ለሥነ ፈለክ ጥናት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል።

#እድሜው:- 1,167 አመት
---
🕌 የአዝ-ዘይቱና ዩኒቨርሲቲ(ቱኒዚያ)

- በ737ዓ.ል የተመሰረተ ሲሆን
በእስልምና ሥነ-መለኮት፣በአረብኛ ቋንቋ እና በእስልምና ስልጣኔ ላይ በማተኮር፣ በሰሜን አፍሪካ እንደ ዋና የአዕምሮ ማዕከል ሆኖ እያገለገለ ይገኛል።

#እድሜው:- 1,289 አመት
---
🕌 የአል-አዝሃር ዩኒቨርሲቲ (ግብፅ)

- በ970–972 ዓ.ል አካባቢ የተመሰረተ ሲሆን ይህም ከጥንታዊ የእስልምና ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ያደርገዋል።
- በዓለም ላይ ትልቁ የእስልምና ዩኒቨርሲቲ በመባል የሚታወቀው አል-አዝሃር 81 ኮሌጆች፣9 ተቋማት፣ 359 ክፍሎች እና 6 ሆስፒታሎች አሉት።
በታሪክ በእስልምና ሕግ፣ በሥነ-መለኮት፣ በሰዋሰው እና በአጻጻፍ ስልት የተካነ ቢሆንም፣አሁን ላይ ሕክምና፣ምህንድስና እና ዘመናዊ ሳይንስንም አካቶ ያቀርባል።

እነዚህ ሶስቱ እድሜ-ጠገብ ዩኒቨርሲቲዎች
መካከለኛውን የእስልምና አስተሳሰብን በመቅረጽ ረገድ ማዕከላዊ ሚና በመጫወት እና አለም ላይ ላሉ ለእስልምና ምሁራን ማጣቀሻ ሆነው እየቀጠሉ ይገኛሉ።

#እድሜው:- 1,056 አመት
*************************
ስለዚህች ከ3ሺ አመታት በላይ ታሪክ ያላትና እነ ኢማሙ ሙስሊምና ኢማሙ አልቡኻሪይ የመሳሰሉ ዑለሞችን ያፈራችዋ ሀገርስ ምን ያህል ያውቃሉ!!?
👇 👇👇👇
https://youtu.be/MbIeaiFEMO4

አድምጡትና ሀሳብ አስታየታችሁን አካፍሉን እስኪ
*************************

24/03/2026

!??
አለም ላይ ስሟ ከሺዓን ጋር ተያይዞ በስፋት የምትነሳዋ #ኢራን
የእነዚህ ሀያላን ዑለሞች መፍለቂያ እንደነበረች ያውቃሉ!?
1. ኢማሙ ሙስሊም
2. አል-ራዚይ
3. አል-ቡኻሪይ
4. አል-ኸዋሪዝሚይ
5. ዑመሩል ኺያር
6. አ-ጠውሲይ
7. ኢብኑ-ሀያም
8. አል-ፋራቢይ
9. ኢብኑ ሲና
10. ኢማሙ-ቲርሚዚይ
እንዲሁም እጅግ በርካታ ዑለሞች የወጡባት ሀገር ነበረች።
እጅግ አስደናቂ የሆነውን የ3ሺ አመት ታሪኳን አጠር አድርገን አቅርበነዋል እንዳያመልጣችሁ።
ሊንኩን በመጀመሪያው ኮሜንት ላይ አስቀምጠነዋል👇
****************************
❤️ #ኢራን #ሰላም

አሏሁ አክበር,አሏሁ አክበር,አሏሁ አክበር,ላ ኢላሀ ኢለሏሀ አሏሁ አክበር አሏሁ አክበር ወሊላሂል ሀምድ።  Quba Tube - ቁባ ትዩብ *********************************
19/03/2026

አሏሁ አክበር,አሏሁ አክበር,አሏሁ አክበር,ላ ኢላሀ ኢለሏሀ አሏሁ አክበር አሏሁ አክበር ወሊላሂል ሀምድ።
Quba Tube - ቁባ ትዩብ
*********************************

🤐  ፡ሚስጥሮችን መናገር ነው ● ምስጢርን መናገር ወይም ማውጣት:-በጽሑፍ፣በምልክት ወይም በንግግር ሊሆን ይችላል፣ሁሉም ሀራም ነው። ምክንያቱም ጉዳት ስለሚያደርስ እና የጓደኝነትን፣የወንድማማ...
27/01/2026

🤐 ፡
ሚስጥሮችን መናገር ነው

● ምስጢርን መናገር ወይም ማውጣት:-በጽሑፍ፣በምልክት ወይም በንግግር ሊሆን ይችላል፣ሁሉም ሀራም ነው። ምክንያቱም ጉዳት ስለሚያደርስ እና የጓደኝነትን፣የወንድማማችነት መብቶች ላይ ቸልተኝነት ስለሚያሳይና የእርስ-በርስ መተማመንን ስለሚያሳጣ ጭምር ፍጹም የተከለከለ ነው።

፡ 🤐

● ጃቢር ኢብኑ ዓብዲላህ እንደተዘገቡት የአሏህ መልእክተኛ (ﷺ)፡- "አንድ ሰው አንድን ነገር ተናግሮ፣ከዚያም ዘወር ካለ (የተናገረው ነገር)እምነት ነው"። ብለዋል.

🚫 ሚስጥርን መናገር የከሀዲነት ምልክት ነው፡-

ሐሰኑል-ብስሪይ(አላህ ይዘንላቸውና)እንዳሉት፡- "በእርግጥም ከክህደት መካከል አንዱ የወንድምህን ምስጢር አደባባይ አውጥቶ መናገር ነው።"

● ምስጢሮችን የመግለጥ ክልከላና ማስጠንቀቂያ ከዓለማቱ ጌታ አሏህ የተሰጠ ቀጥተኛ ትእዛዝ ነው። አሏህ በቁርኣኑ፡-
﴿يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ لَا تَخُونُوا۟ ٱللَّهَ وَٱلرَّسُولَ وَتَخُونُوٓا۟ أَمَٰنَٰتِكُمْ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ﴾
"{እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አሏህንና መልክተኛውን አትክዱ፡፡ አደራዎቻችሁንም እናንተ እያወቃችሁ አትክዱ፡፡"} አል-አንዓም 27

🏠 የቤት ውስጥ ሚስጥሮች ክብርና ክልከላ፡-

ከታማኝነትና ከሚስጥር ጠባቂ ማንነት ምልክቶችና ትርጉሞች መካከል አንዱ የቤትን ምስጢር መጠበቅ ነው።

● ኢማሙ ሙስሊም ከአቡ ሰዒድ አል-ኹድሪይ እንደተረኩት የአሏህ መልእክተኛ(ﷺ)፡- {"በእርግጥም በትንሣኤ(ቂያማ)ቀን አሏህ ዘንድ ከሚቆሙት በጣም መጥፎ ሰዎች መካከል፣"ባል ማታ ከሚስቱ ጋር ግንኙነት ያደርግና፣ሚስትም ከባሏ ጋር ግንኙነት አድርጋ ታድርና ከዚያም ጠዋት እሷም ሚስጥሯን እሱም ሚስጥሩ ለሌላ የሚያሰራጭ ሰው ነው።"} ብለዋል.

⚖️ ሸሪዓዊ እና ሰባዊ ፍርዱ፡

የሌሎችን ሚስጥሮችን መግለጥና መናገር ክህደት ነው፣
የታማኝነትን ስብእና የማጣት ባህሪም ነው። በሚስጥሩ ባለቤት ላይ ጉዳት አደረሰም አላደረሰ፣ሀራም(ክልክል) ነው።

● ትልቁ ሰው(ﷺ):-{"በአሏህ እና በመጨረሻው ቀን የሚያምን፣መልካም ነገርን ይናገር አልያም ዝም ይበል"} ባሉት መሰረት የምንናገረው ነገር ለአድማጩ ጠቃሚ ከሆነ በቀር ዝምታን ማዘውተር ጸጋ ነውና እንላበሰው።
ዝምታን ማዘውተር ከብዙ ጸጸቶች፣ጥፋቶች ይጠብቃል።

:-በሳል ሰው ማለት የሚያውቀውን ሁሉ የሚናገር ሳይሆን የሚናገረው ነገር ትክክልና ጠቃሚ መሆን አለመሆኑን ለይቶ የሚያውቅ ነው።

#ሰላም.

t.me/QubaTube

*********************************
#ቁባትዩብ #ተሰዉፍ #ኢስላም ❤️ #ሰላም

20/01/2026

ኢኽዋኖች VS ሱኒ|| ሙሉውን ቪዲዮ ኮሜንት ስር ባለው ሊንክ ያገኙታል።
**************************************
#ቁባትዩብ #ኢስላም #ሙስሊሙ #ሙስሊሙን #ኢኽዋን

የኢስላምን ታሪክ የቀየረው ታላቁ ጉዞ  #ክፍል2ከፍል አንድን ያላነበበ ሊንኩን ኮሜንት ላይ ያገኘዋል**********************   ክፍል 2 ..ነቢዩ ﷺ ከመስጂደል ሀርም ወደ የሌሊቱ...
16/01/2026

የኢስላምን ታሪክ የቀየረው ታላቁ ጉዞ #ክፍል2
ከፍል አንድን ያላነበበ ሊንኩን ኮሜንት ላይ ያገኘዋል
**********************

ክፍል 2
..ነቢዩ ﷺ ከመስጂደል ሀርም ወደ የሌሊቱ ጉዞ ከመወሰዳቸው በፊት፣መካ "ኡም ሃኒእ ቤት፣እያሉ ጅብሪል መጥቶ ደረታቸውን ከፍቶ አጥቦላቸው ነበር።

አነስ ኢብኑ ማሊክ እንደዘገበው አቡ ዘር የአሏህ መልእክተኛ ﷺ የሚከተለውን ይነግሩን ነበር ይላል፡-

“በመካ ሳለሁ የቤቱ ጣራ ተከፈተ።ጅብሪልም ወርዶ ደረቴን ከፈተ፣በዘምዘም ውሃ አጠበው፣ከዚያም በጥበብና ኢማን የተሞላ የወርቅ እቃ አምጥቶ ደረቴ ውስጥ አፈሰሰው፣ ከዚያም አሸገው።”
(ሙስሊም)

አሏህ ለሰዪዲ መሐመድ (ﷺ) ነቢያትን ሁሉ - {ሰላትና ሰላም በእነርሱ ላይ ይሁንና} - ከአዳም ጀምሮ በቁድስ ሰብስቦላቸው ሰላትን ኢማም ሆነው መርቷቸዋል።

👉ይህ ክስተት፣ነቢያት ከሞቱ በኋላ በአሏህ ፈቃድ ተሰሩፍ ሊያደርጉ እንደሚችሉ የሚያሳይ ነው።ነብያት እንደ ተራ ሰዎች ስላይደሉ።

አል-በዛር፣አል-በይሃቂይ እና ሌሎችም እንደዘገቡት የአላህ መልእክተኛ (ﷺ)፡- “ነቢያት በመቃብራቸው ውስጥ ሕያው ናቸው ለጌታቸውም ይሰግዳሉ።” ብለዋል.

...

የአላህ መልእክተኛ (ﷺ) ስለ ኢስራእና ሚዕራጅ መንገራቸውን ቀጠሉ፡-
“....ከዚያም ወደ ቁድስ ገባሁ፣ነቢያትም ለእኔ ተሰበሰቡ። ጅብሪል እኔን ወደፊት አመጣኝና ኢማም ሆኜ መራኋቸው። ከዚያም ወደ ሰማይ ይዞኝ ወጣ።”
(አል-ነሳኢይ)

ነቢዩ(ﷺ)በኢስራእ ጉዟቸው ያዩዋቸው ድንቃ-ድንቆች፣

● ዓለም(ዱንያ)፡-

ወደ ቁድስ ሲሄዱ፣ ዓለምን(ዱንያን)በአንዲት አሮጊት ሴት መልክ አዩዋት።

(ዑለሞች በአሮጊት መልክ ያዩዋት ምክንያት ዱንያ ማለቂያዋ መቃረቡን ያሳያል ይላሉ።)

●ኢብሊስ፡

ሰዪዲ ﷺ ከመንገድ ዳር ቆሞ የሚጠራ ነገር አዩ። ያ ተጣሪ ኢብሊስ ነበር።
ኢብሊስ መጀመሪያ ላይ ከአማኞች ጂኖች መካከል ነበር፣ከዚያም አሏህን በመቃወም ካደ።

● የፊርዓውን ልጅ የፀጉር አስተካካይ፡-

ከሳሊሀት (ሴት ጻድቃን)ከነበረችው የፊርዓውን ሴት ልጅ የፀጉር አስተካካይ መቃብር የሚወጣ ውብ መዓዛ አሸተቱ።

[ ታሪኳ ባጭሩ እንዲህ ነው:- የፊርዓውንን ልጅ ፀጉር እያበጠረች ሳለ ድንገት ማበጠሪያው ከእጇ ሲወድቅ “በአሏህ ስም-ቢስሚላህ” አለች። የፊርዓውን ልጅ ሰማቻትና “ከአባቴ ሌላ አምላክ አለሽ እንዴ?” ብላ ጠየቀቻት። እሷም “አዎ፣ ጌታዬ የአባትሽም(ፊርዓውን) ጌታ የሆነው አሏህ ነው” ብላ መለሰች። ጉዳዩ ለፊርዓውን ተነገረው። እሱም እምነቷን እንድትክድ አዘዛት፣ግን እምቢ አለች።

ፊርዓውንም እጅግ ተቆጥቶ በአሰቃቂ ሁኔታ ሊገድላት ውሃ አግለው እንዲያፈሉለት አዘዘ፣ አፍልተውም አመጡለት፣ ከዚያም አይኗ እያየ ልጆቿን ወደ ሚንተከተከው ውሀ አንድ በአንድ ጣላቸው። ከሁሎቹም ታናሽ የነበረው ሕፃን ልጇ ከመጣሉ በፊት፡-

“እናቴ ሆይ፣ ታገሺ፣ጽኚ የኋለኛው ዓለም ቅጣት ከዚህ ዓለም ቅጣት የበለጠ ከባድ ነው። አትጨነቂ፣ አንቺ በእውነት ላይ ነሽ።” አላትና እሱንም ወረወረው ።

በመጨረሻም የእናትየው ተራ መጣ፣እሷንም ሊወረውራት
ሲል “እባክህን አንድ ነገር ብቻ ልለምንህ፤የእኔም፣የልጆቼ
አጥንቶቹ ሁሉም በአንድ ላይ ሰብስበውና በአንግ ጉድጓድ ቅበረን” ብላ ጠየቀችው። እሱም “ተቀብዬሻለሁ” አላትና ወደ ውስጥ ወረወራት፣ ከእነ ልጆቿ ጋር ሸሂድ (ሰማዕት)ሆና ሞተች።]

●በአሏህ መንገድ ላይ ያሉ ታጋዮች፡-

ሰዎች በሁለት ቀናት ውስጥ ሲተክሉና ሲሰበስቡ አዩ። ጅብሪል “እነዚህ በአሏህ መንገድ ላይ ያሉ ሙጃሂዶች ናቸው” አለ።

በአሏህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሃድ ሁለት አይነት ነው፡- በጦር መሳሪያ የሚደረግ ጂሃድ እና በንግግር እና በማብራሪያ የሚደረግ ጂሃድ። የሁለተኛው ሽልማት ልክ እንደ ጦር መሳሪያ የሚደረገው አይነት ሽልማት ነው። ዛሬ በመልካም ነገር የሚያዝ እና ክፉን በቅንነት የሚከለክል በአሏህ መንገድ ላይ ያለ ሙጃሂድ ነው።

ሙጃሂድ በመጨረሻው ዓለም ከፍተኛ ደረጃ አለው። የአሏህ መልእክተኛ (ﷺ) ፡-“ኡመቶቼ በሚበላሹበት (ፈሳድ በሚበዛበት)ወቅት ሱናዬን የሚያድስ ሰው የሰማእትነት ሽልማት ያገኛል።” ብለዋል

[እዚህ ላይ ሱና ማለት የአሏህ መልእክተኛ ያመጡት የእስልምና ዋናዋና ህጎችን ነው።]

● የፊትና ሰባኪዎች፡

ምላሳቸውንና ከንፈራቸውን በእሳት መቀስ የሚቆረጡ ሰዎችን አዩ። ጅብሪልም፡- “እነዚህ የፊትና ሰባኪዎች ናቸው - ክፉንና እርስበርስ ማባላትን የሚሰብኩ፣ ሰዎችን ወደ ጥመት፣ ሙስና፣ ማታለልና ክህደት የሚጠሩ ናቸው።” አለ

● የብልግና ቃላትን የሚናገሩ፡

ከጠባብ ክፍተት የሚወጣና፣ከዚያም ወደወጣበት ለመመለስ የሚሞክር፣ሆኖም ግን የማይችል በሬ አዩ።
ጅብሪልም “ይህ በሰዎች መካከል ጉዳትና መከራን የሚያስከትል የተበላሸ ቃል የሚናገር፣ ከዚያም የተናገውን ቃል ለመመለስ የሚሞክር እና የማይችል ሰው ነው።” አለ።

● ዘካ የማይከፍሉ፡

ብልታቸውን ብቻ የሚሸፍን ብጣሽ ጨርቅ ያደረጉና እንደ ከብቶች የሚሰማሩ እርቃን ሰዎችን አዩ። ጅብሪልም “እነዚህ ዘካ የማይከፍሉ ናቸው” አለ።

●ሰላትን ችላ የሚሉ፡

ራሶቻቸው(ጭንቅላታቸው)እየተቀላ፣ከዚያም ወደነበረበት ሁኔታ የሚመለስ ሰዎችን አዩ። ጅብሪልም “እነዚህ ራሳቸውን ለሰላት ማጎንበስ የከበዱባቸው ሰዎች ናቸው” አለ።

● አመንዝሮች(ዝሙተኞች)፡

ጥሩና ጤናማ የሆነነውን ሥጋ እየተዉ ለበሰበሰ ሥጋ የሚወዳደሩ ሰዎችን አዩ። ጅብሪልም፣ “እነዚህ ከኡማዎችህ የተውጣጡ ሰዎች ናቸው፤ የተፈቀደውን ትተው ለተከለከለው የሚሽቀዳደሙ አመንዝሮች(የዚና ሰዎች) ናቸው።” አለ

● አስካሪ መጠጥ ጠጪዎች፡

ከዝሙት አድራጊዎች የሚወጣ መግል የሚጠጡ ሰዎችን አዩ። ጅብሪልም “እነዚህ በዱንያ ላይ የተከለከለውን (አስካሪ)መጠጥ የሚጠጡ ናቸው” አለ።

● ሐሜተኞች፡

ፊታቸውንና ደረታቸውን በገዛ መዳብ ጥፍሮቻቸው የሚቧጩሩ ሰዎችን አዩ። ጅብሪልም “እነዚህ ሰዎችን የሚያሙ ናቸው” አለ።

[ ሐሜት በመቃብር ውስጥ ከሚከሰቱት ከባድ የቅጣት መንስኤዎች መካከል አንዱ ነው። ሐሜት እና ከሽንት መጽዳትን ችላ ማለት ቀብር ውስጥ ለከፋ ቅጣት ከሚዳርጉ ወንጀሎች መካከል ናቸው።...)

ተአምራቱ በ ...

ሼርና-like እያደረጉ አብረውን ይቆዩ።



t.me/QubaTube

**************************
#ተሰዉፍ #ቁባትዩብ #ኢስላም #ኢትዮጵያ ❤️ #ኢስራእ

የኢስላምን ታሪክ የቀየረው ጉዞ   በአሏህ ስም እጅግ በጣም አዛኝ፣እና ሩህሩህ በሆነው በመቀጠል፡-ክብሩ የላቀው አሏህ በተከበረው ቁርኣኑ፡- سُبْحَٰنَ ٱلَّذِىٓ أَسْرَىٰ بِع...
16/01/2026

የኢስላምን ታሪክ የቀየረው ጉዞ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም አዛኝ፣እና ሩህሩህ በሆነው

በመቀጠል፡-ክብሩ የላቀው አሏህ በተከበረው ቁርኣኑ፡-

سُبْحَٰنَ ٱلَّذِىٓ أَسْرَىٰ بِعَبْدِهِۦ لَيْلًۭا مِّنَ ٱلْمَسْجِدِ ٱلْحَرَامِ إِلَى ٱلْمَسْجِدِ ٱلْأَقْصَا ٱلَّذِى بَٰرَكْنَا حَوْلَهُۥ لِنُرِيَهُۥ مِنْ ءَايَٰتِنَآ ۚ إِنَّهُۥ هُوَ ٱلسَّمِيعُ ٱلْبَصِيرُ
"ያ ባሪያውን ከተከበረው መስጊድ ወደዚያ ዙሪያውን ወደ ባረክነው ወደ ሩቁ መስጊድ በሌሊት ውስጥ ያስኼደው (ጌታ)ጥራት ይገባው፡፡ ከተዓምራቶቻችን ልናሳየው (አስኼድነው)፡፡ እነሆ እርሱ (አላህ) ሰሚው ተመልካቺው ነው፡፡" (አል-ኢስራእ፡1)



በአረብኛ ቋንቋ፣ #السُّبْح_አስ_ሱብህ ማለት መራራቅ ወይም ማስወገድ ማለት ሲሆን ማለት ደግሞ አሏህ ከፍጡሩ ጋር በምንም መልኩ ከመመሳሰል የራቀ(የማይመሳሰል)
መሆኑን የሚገልጽ ነው።

:- ማለት በሌሊት መጓዝ ወይም የሌሊት ጉዞ ማለት ነው።
ስለዚህ፣ኢስራእ እና ሚዕራጅ ሁለቱም በአንድ ሌሊት በተወሰነው ክፍል የተከሰቱ ጉዞዎች ናቸው።

:- የተባለውም ላለው ቅዱስነት እና ከእሱ ጋር የተያያዙ ልዩ ሸሪዓዊ ድንጋጌዎች በመኖራቸው ምክንያት፣ ለምሳሌ:-በዚያ ቦታ ላይ ለሚደረገው ስግደት የሚሰጠውን (አጅር) ሽልማት ከሌላ ቦታዎች በበለጠ ተባዝቶ መሆኑ፣መካ ውስጥ መስጂዱ የሚገኝበት ቦታ በምድር ላይ ምርጡና ይበልጥ ተወዳጅ ቦታ መሆኑ፣ እና መስጂዱ ባለበት መካ ውስጥ እንስሳትን ማደን ክልክል መደረጉ ይገኙበታል።

ማለት:- ቋንቋዊ ፍቺው እሩቅ ማለት ሲሆን አል-አቅሷ የተባለውም ከተቀደሰው መስጊድ ርቆ የሚገኝ በመሆኑ ነው።

#ትንታኔ፣
ከላይ የጠቀስናቸው ሁለቱም መስጂዶች የተገነቡት በአዳም عليه السلام ሲሆን፡ በቅድሚያ ካዕባን ሠራ፣ ከአርባ ዓመታት በኋላ ደግሞ አል-አቅሷ መስጊድ ሠራ።
አሏህም “መስጊድ” ብሎ ሰየመው፣ይህ የሚያመለክተው የሁሉም የነብያት ተከታዮች(ሙስሊሞች)ለአንድ አምላክ
እንደሚሰግዱና ይሰግዱ እንደነበር፣ እንዲሁም የአምልኮ ቦታ ሆኖ እንደሚሠራ፣ በውስጡም ሙስሊሞች ለአሏህ በብቸኝነት የሚሰግዱበት ስፍራ እንደነበር ነው።

የአሏህ “باركنا حوله-ዙሪያውን የባረክነው” የሚለው አገላለጽ የታላቋ -ሶሪያና አጎራባች ሀገራት ፈለስጢንን ጨምሮ - የተባረከች ምድር እንደሆነች ያሳያል።
በሰሂህ አል-ቡኻሪይ ላይ የአላህ መልእክተኛ (ﷺ)፡-

“አላህ ሆይ፣ሻማችንንና የመናችንን ባርክ” ሲሉ፣

አብረዋቸው የነበሩት ሰሀቦች:- “የአሏህ መልእክተኛ ሆይ፣ነጅዳችንንስ?” አሉ።
“እዚያማ የመሬት መንቀጥቀጥና መከራ ይኖራል፤ የሰይጣን ቀንድም ከዚያ ይወጣል” ሲል መመለሳቸውን በትክክለኛ- ሰሂህ ሀዲስ ተዘግቧል።

ስለዚህ የአል-ሻም ምድር የተባረከች ናት፣ፍልስጤም - አል-አቅሷ መስጊድ የሚገኝበት - አንዱ የአል-ሻም ምድር አካል ነው።

● አሏህ ሁሉንም ነቢያትን ለባሪያዎቹ እዝነት አድርጎ ላካቸው፣ምክንያቱም ያለእነሱ አመላካችነት አእምሮ ብቻውን በመጨረሻው ዓለም ወደ መዳን የሚያመሩትን መልካም ስራዎችን እና ወደ ክስረት የሚያመሩ መጥፎ ስራዎችን በተናጥል ማወቅ አይችልም። ስለዚህ አሏህ ነብያትን ለባሮቹ መላኩ ትልቅ ጸጋ።

አሏህ ነቢያትን ሲልክ ለእውነተኝነታቸው ማረጋገጫ እንዲሆን በተአምራት(ሙዕጂዛ) ደግፏቸዋል።

ተአምር ወይም ሙዕጂዛ ማለት:- ተለምዶን የሚጥስ፣ እና ነቢይነትን በሚጣራ ሰው እጅ ላይ የሚታይ፣ እንዲሁም ከሚጣራው መልእክት ጋር የሚስማማ እና ተመሳሳይ በሆነ ነገር ሊቃወሙት የማይቻል ያልተለመደ ክስተት ነው።

ነቢዩ (ﷺ)በተአምራት ከሌሎች ነቢያት ሁሉ ታላቁ ነበሩ።
ኢብኑ አቢ_ኻቲም:-ከኢማሙ-ሻፊዒይ እንደዘገቡት፡-
"አሏህ ለሙሐመድ የሰጠውን አይነት ተአምር ለማንም አልሰጠም" ሲሉ፣
እኔ "ዒሳ ለሙታን ሕይወት የመስጠት ችሎታ ተሰጥቶታል" አልኳቸው፣ እሳቸውም ቀጥለው
«ሙሐመድ ድምፁ እስኪሰማ ድረስ በናፍቆታቸው ተንሰቅስቆ የሚያለቅስ ግንድ ተሰጥቷቸዋል - ይህ ከዚያ የበለጠ ነው» አሉኝ። ይላሉ.

አንዳንድ ገጣሚዎች እንዲህ ሲሉ አወድሰውታል፡-
ሙሳ ለጎሳው ከድንጋይ መጠጥ አፍልቆ ቢሰጣቸው፣
ሙሀመድ ደግሞ ከጣቶቹ መሀል አፍልቆ አጠጣቸው፣ ከድንጋይ መሀል ውሀን ማፍለቁ ቢደንቅም፣
ከጣቶች መሀል ማፍለቅ ግን ከማንም አልታየም።

ዒሳ በጸሎቱ ዕውሮችን ከፈወሰ፣
በእጀዎ እብሳት የስንቱ እይታ ተመልሰ።

● ከነቢዩ ﷺ ተአምራት መካከል ኢስራእ እና ሚዕራጅ ይገኙበታል።

#ኢስራእ

የኢስራእ ተአምር በቁርዓን እና በሐዲስ በግልጽ የተረጋገጠ ነው። ስለዚህ አሏህ ነቢዩንﷺ በሌሊት ከመካ ወደ አል-አቅሷ መስጊድ እንዲጓዙ እንዳደረገው ማመን ሸሪዓዊ (ዋጂብ)ግዴታ ነው።
የኢስላም ምሁራን - የሰለፎች እና የኸለፎች ሊቃውንት፣ ሙሀዲሶች፣ሙፈሲሮች፣ፉቀሀኦች በሙሉ - ኢስራእ እንደተከሰተና የተከስውተውም በህልም ሳይሆን በአካል፣በነፍስ፣ነቅተው እንደሆነ ያለ አንዳች ልዩነት ይስማማሉ።



በይሀቂይ ከሸዳድ ኢብኑ ዓውስ እንደተረኩት፡-

“የአሏህ መልእክተኛ ሆይ፣በሌሊት ጉዞህ አሏህ እንዴት አድርጎ ወሰደህ?” ብለን ጠየቅናቸው፣ እሳቸውም፡-

“በመካ ከጓደኞቼ ጋር የሌሊት ሰላትን ሰገድኩ፤ከዚያም ጅብሪል ነጭ እንስሳ(ቡራቅ)ይዞ መጣ፤ ​(እንስሳውም) ከአህያ የሚበልጥና ከበቅሎ የሚያንስ ነው።ከዛም (ውጣ)አለኝ። እላዩ ላይ ለመውጣት ለእኔ ከባድ ስለነበር (ጅብሪል) ጆሮውን በመያዝ አረጋጋው፤ ከዚያም ወደ ላይ ከፍ አደረገኝና ወጣሁ፣ ጉዞም ጀመርን። ቡራቁ ሲጋልብ እግሮቹ የሚያርፉት አይኖቹ ማየት በሚችሉት ርቀት ቦታ ላይ አድርጎ ነበር። እናም የዘንባባ ዛፎች ያሉበት ምድር እስክንደርስ ድረስ ተጓዝን።
ዛፎቹ ጋር ስንደርስ "እዚህ ጋ ውረድና ስገድ" አለኝ ጅብሪል፤
እኔም ወርጄ ሰገድኩ። ከዚያም ወደኔ መጣና "አሁን የት እንደሰገድክ ታውቃለህ?" አለኝ።"አሏህ ይወቅ" አልኩት። ‘በየስሪብ-ጠይባ ነው የሰገድከው’ አለኝ። ከዚያም ወደ ሌላ ምድር እስክንደርስ ድረስ ቀጠልን። አሁንም ‘ውረድ’ አለኝ፤ እኔም ከነበርኩበት ወረድኩ። ‘ስገድ’ አለኝ፤ ሰገድኩ። ከዚያም ‘የት እንደሰገድክ ታውቃለህ? "አሏህ ሙሳን ባነጋገረበት ጡሪ-ሲናእ ተራራ ነው የሰገድከው’ አለኝ።
ከዚያም ቤተ መንግሥቶች ወደሚታዩበት ምድር እስክንደርስ ድረስ ቀጠልን። ‘አሁንም ውረድ’ አለኝ፣ "እኔም ወርጄ ሰገድኩ"። ከዚያም ‘የት እንደሰገድክ ታውቃለህ?’ አለኝ። ‘አሏህ ያውቃል’ አልኩት። ‘የመርየም ልጅ ዒሳ በተወለደባት በበይት-ለህም(ቤተልሔም) ሰገድክ’አለኝ።ከዚያም ‘የመርየም ልጅ ዒሳ በተወለደባት’
ወደ አል-ቁድስ እስክንገባ ድረስ ወሰደኝ። ከዚያም ከደቡባዊው በር ወደ ቁድስ እስክንገባ ድረስ ወሰደኝ።
ከመስጊዱ በቂብላው አቅጣጫ መጣና፣ መጋለቢያውን እዚያ አስሮ የፀሐይና ጨረቃ ብርሀን በሚያሾልክበት በር በኩል ወደ መስጊዱ ውስጥ ገባን።አሏህ በሻልኝ ቦታ በመስጊዱ ውስጥ ሰገድኩ።...}

...

t.me/QubaTube

#ሼረሼርሼር ይደረግ ጀዛኩሙሏህ።


**************************
#ቁባትዩብ #ተሰዉፍ #ኢስላም #ኢትዮጵያ #ሰላም ❤️

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Quba Tube - ቁባ ትዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Quba Tube - ቁባ ትዩብ:

Share