Quba Tube - ቁባ ትዩብ

Quba Tube - ቁባ ትዩብ እዚህ ድረስ ከመጡ በውዱ ላይ ሰለዋት ሳያወርዱ አይውጡ❤️፣ إن أتيت إلى هنا فلا تخرج قبل أن تصلي
على الغالي❤️ .https://heylink.me/qubatube/

 #محمد :-صلوا عليه كما يصلّي ربنا - إن الصَّلاةَ على الحبيب دواءيا خيرَ مَنْ بَعَثَ الإله لخلقه - من مرسلين بكل خير جاؤو...
25/08/2026

#محمد :-
صلوا عليه كما يصلّي ربنا - إن الصَّلاةَ على الحبيب دواء
يا خيرَ مَنْ بَعَثَ الإله لخلقه - من مرسلين بكل خير جاؤوا
قد كنتَ أمِّياً ولكن قلتَ ما - عن مثل قولهِ يعجزُ البُلغاء
صعْتَ الحياة لنا بأبهى حُلَّةٍ.

اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلم .
************************************************

#አሏህ

      አሰላሙዓለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ ውድና የተከበራችሁ የግሩፓችን ተከታታዮች!እንኳን ለተከበረው ለነብዩ መውሊድ በሰላም አደረሳችሁ!የእስልምናን ጸጋ የሰጠን ቸሩ ጌታችን አሏህ ም...
24/08/2026



አሰላሙዓለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ ውድና የተከበራችሁ የግሩፓችን ተከታታዮች!

እንኳን ለተከበረው ለነብዩ መውሊድ በሰላም አደረሳችሁ!

የእስልምናን ጸጋ የሰጠን ቸሩ ጌታችን አሏህ ምስጋና ይገባው እንድንዋደድም ዘንድ የወንድማማችነትን ጸጋ አድሎን ደግሞ ከኡመቶች ሁሉ በነብዩ ሙሀመድ በርከት በላጭ ኡመቶችም አደረገን ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም።

በነብዩ በርከትም አላህ ወንጀላችንን ምሮ፣ ችግሮችን ከኛና ከወንድሞቻችን ላይ ያንሳልን፣ ጭንቀቶቻችንንም ያስወግድልን፣ እኛንም ወዳጆቻችንንም ከሙሲባዎች፣ከክፉ በሽታዎች ሁሉ ይጠብቀን እያልን አሏህን እንለምነዋለን! ዘላለማዊ በሆነችዋ ሀገር ጀነትም ከነብዩ ጋር ይሰብስበን።

በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ!


******************************

መውሊድን በተመለከተ ጥቂት ማብራሪያ ኮሜንት ስር ይመልከቱት።

ሰሉ ዓለ-ነቢይ
**************
#ቁባትዩብ #ሙስሊሙ #ኢትዮጵያ

اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا محمد وعلى آله وصحبه أجمعين . صلوا على الحبيب ❤️Link on the first Comment👇 ****************...
21/05/2026

اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا محمد وعلى آله وصحبه أجمعين . صلوا على الحبيب ❤️
Link on the first Comment👇
******************************************
❤️ #ሰላም

ይድረስ ለመላው ክርስቲያን ወገኖች**************************** ● ምን በደል ፈጸምን!? ይህ...ጸጥ ባለ ህመም ከሚሰቃይ ልብ የተነሳ - አክሱምም ሆነ በመላው ሀገሪቱ ላሉ ለ...
23/04/2026

ይድረስ ለመላው ክርስቲያን ወገኖች
****************************

● ምን በደል ፈጸምን!?

ይህ...ጸጥ ባለ ህመም ከሚሰቃይ ልብ የተነሳ - አክሱምም ሆነ በመላው ሀገሪቱ ላሉ ለእስልምና የከረረ ጥላ*ቻ ላላቸው ክርስቲያኖች ሁሉ የቀረበ ጥያቄ ነው፡-

● ምን በደል ፈጽምን?

እኛ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ፍሱም ሰላምን የምንፈልግ የሰላም ሰዎች ነን።እምነታችንን በውጫዊ መልኩ ከማሳየታችን በፊት በልባችን ውስጥ ይዘን ወደ ጌታችን እዝነት በር ለመቅረብ በአቅማችን ልክ የምንተጋ፣ ደፋ ቀና የምንል ይህችን አለም እንደ ጊዜያዊ መኖሪያ ቤት አድርገን የምናይ ሰዎች ነን።በትእዛዙ መሰረት ለእርሱ እንሰግዳለን፣እንጾማለን።

ምድር ላይ እስካለን ድረስ እዝነቱ ከእኛም አልፎ እናንተንም ጭምር እንዲያቅፍ፣ የእናንተም የእኛም የሆነችዋን ብቸኛዋን ሀገራችንን ዳር ድንበሯን ሰላም እንዲያደርግልን ቢያንስ በቀን አምስቴ እንለምናለን።

ታዲያ...

● ?

በእናንተ ላይ መሳሪያ አላነሳንም፣እናንተን ለመጉዳት አልሞከርንም።መብቶቻችሁን አልጣስንም ወይም እምነታችሁን እንዳትከተሉ አላገደንም።

እኛም እንደ ማንኛውም ቅን ኢትዮጵያዊ የቸገረውን ስናገኝ - ሙስሊም ነው ክርስቲያን- ሳንል የአቅማችንን እንረዳለን፣ የተራበውን እናበላለን፣የተጠማውን እናጠጣለን፣የተራቆተን እናለብሳለን።
ሀገራችን- ሀገራችሁ ኢትዮጵያ ስትፈልገን ላፍታ እንኳ ሳናመነታ "አቤት" ያልን ገንዘብ ጉልበታችን፣ ሲያስፈልግም ነፍሶቻችንን ሳንሰስት እንሰጣለን።

እስኪ ንገሩን ምን በደል ፈጸምን ነው...
አንዴ እምነታችንን፣አንዴ ከገዛ ወላጆቻችን-ነፍሶቻችን አብልጠን የምንወዳቸውን፣
ሌተ-ቀን "ምነው አንዴ እንኳ በህልሜም ቢሆን ባየኋችሀው" እያልን በናፍቆት የምናለቅስላቸውን ውዱን ነብያችንን፣ ሲያሻችሁ ማንነታችንን የምትሰድቡት!
ይህም ሳይበቃን በ #አክሱም እና በአንዳንድ ቦታዎች፣እጅግ መሠረታዊ የሆነውን መብታችንን የምትነፍጉን…
ጌታችንንም በሰላም የማምለክን፣ የመለመንን መብታችንን የምትነጥቁን!!።

በገዛ ላባችን ጥረን ግረን - አንዳንዴም ከእለት ጉርሻችን ላይ ቀንሰ - በምንገዛው፣ በምንገነባው የአሏህ ቤት(መስጂዳችን)፣ በሰላም እንዳንሰግድ...
እንዲሁም የጋራችን በሆነችዋ ምድራችን ኢትዮጵያ "ፈጣሪያችን ረጂያችን፣ጌታችን፣ ሰጪያችን ነው" ብለን ያመነውን አሏህን ዱዓእ(ጸሎት)ማድረግን ለምን ትቃወሙናላችሁ!?
በገዛ ሃይማኖታዊ ልምምዶቻችን ውስጥ ለመንገላታት ምን ስህተት ሠርተናል?

ከእናንተ ጋር በምንጋራው ምድር እንደ እንግዳ እንድታዩን የሚጋብዝ ምን ኃጢአት ሰርተናል?

እስከ መቼ በድርጊታችን ሳይሆን በማንነታችን የምትፈርዱብን!!!?

ሙስሊም ስለተኾነ ብቻ በጥርጣሬ መታየት
ምንም-ማንም ላይ ጉዳት ያላደረሱ እህት-ወንድሞቻችን ላይ ጥላቻ፣ስድብና ትንኮሳ መሰንዘርን እምነታችሁስ ይፈቅዳል!!?

ትክክል ነው ብላችሁ ወዳመናችሁት እምነትስ በዚህ መልኩ ነው እንድትጣሩ የሚያዛችሁ!!?

ታዲያ....

● ?

ከ አዕምሮ በፊት የነፍስን ስሜት እናስቀድም ከተባለ እንደ ሰውኛ እኛምኮ ምላስ አለን እንዲሳደብ ከፈለግን፣እኛም ጡንቻ አለን እንዲ*ማታ ከፈለግን፣እኛም ሀይል አለን ማስፈራራት፣መጨቆን ከፈለግን፣
ነገር ግን እምነታችን ሌሎችን እንድናከብር ለሙስሊምም ሆነ ለክርስቲያን ጥሩ ጎረቤት እንድንሆን፣የአብሮነትን ባህል እንድናከብር፣ለራሳችን የምንመኘውን መልካም ነገርን ሁሉ ለሌላውም እንድንመኝ
እና የራሳቸውን መንገድ የመምረጡ ሰዎችን እንዳንገፋ ስለሚያስተምረን፣
እና...
እንደ ሀገር እንደ ዜጋ ያሉብንን የጋራ ችግሮቻችንን ተባብረን ብንቀርፍ፣ከእኛ ወገንም ሆኑ ከእናንተ የተቸገሩትን ብንረዳ፣ የተራቡትን ብናበላ፣እንዲሁም እጅግና ጓንት ሆነን ሀገራችን #ኢትዮጵያን ወደተሻለ ደረጃ ከፍ ብናደርግ.. የተሻለ ስለሆነ እርሱ ላይ ትኩረት እናድርግ ብለን ነው።

ሙስሊም የሀሳብ ልዩነቶች ሲገጥሙት እንደ በሰለ ሰው ተቀራርቦ ሀሳቦቹን አቅርቦ በጥበብ መወያየት እና በሀሳብ ካልተስማሙት ጋር በፍትህ እና በርህራሄ ተቻችሎ እንዲኖር ከእምነቱ በፊት ህሊናው የሚያዘው ምእመን ነው።

ይህ ታዲያ እንዴት ለጥ*ላቻ ምክንያት ይሆናል?

● ?

እኛ ሙስሊሞች ከፍትህና ከእኩልነት በላይ የምንጠይቀው ከሌላው የተለየ ነገር የለንም።በእኩልነት ተከባብሮ መኖርን እንጂ ማንም ላይ መጫን አንፈልግም።

እና ውድ የሀገሬ - በተለይ ለእስልምና ጥራዝ ነጠቅ የሆነ አመለካከት ያላችሁ ወንድሞች እና እህቶች፣ እመኑኝ አክራሪነት ማህበረሰብን ያፈርሰዋል እንጂ አይገነባም።

ኢፍትሃዊነት ጥንካሬን አይፈጥርም። ኢፍትሃዊነት ሁላችንንም የሚጎዳ የጥላቻ ዘርን ከመትከል ውጪ ማናችንንም አይጠቅምም።

ዛሬ #አክሱም ላይ እየሆነ ያለው ነገር መላውን ሀገር ወዳድ - ሙስሊም እና የበሳል አስተሳሰብ አዕምሮ ባለቤት የሆኑ ቅን ክርስቲያን ወገኖች ልብን ጎድቷል፣ አሳዝኗል አዎ።!
ከማሳዘኑም በላይ ደግሞ ሁላችንም የሚያስፈልገንን አብሮ የመኖርን የወደፊት ሁኔታም አደጋ ላይ ይጥላል።
ስለሆነም ከኋላ ቀሩ ጭፍንነት ወጣ ብላችሁ በሰከነ አዕምሮ አስቡበት።
ገላን መሸፈን የክብር መገለጫ እንጂ የነውር አይደለም፣ ገላቸውን በመሸፈን የቅድስት ማርያምን ፈለግ የምትከተልን እንስት እንቅፋት አትሁኗት።

#በመጨረሻም!

የሰው ልጅ ከእንስሳ የሚለየው መሰረታዊው
ነገር አዕምሮ ነው። ለእራሱና ለማንነቱ ክብር የሚሰጥ፣ ይህን የተሰጠውን አዕምሮ በአግባቡ ይጠቀማል።
ስለዚህ ለራሳችን ክብር እንስጥ፣ ንቃተ-ህሊናችንን እናዳብር።

ወደ የጋራ ሰብአዊነታችን፣ወደ የጋራው ሀገራዊ ሰላምና ልማታችን እንመለስ…
ለእርስ በርሳችን በሰላም የመኖርን ጣእም አንምፈግ።

ወገኔ! ይህ ዓለም ለሁላችንም ሰፊ ነውና፣ ከመበዳደል ይልቅ ፍትህን፣ከጥላቻ ይልቅ ርህራሄን መርጠን ኑሯችን ለጊዜያዊ በሆነችው ምድር በሰላም እንኑር።

አሏህ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይጠብቅ።



Quba Tube - ቁባ ትዩብ

ሀሙስ/ሚያዝያ/15/2018

#ሰላም.

ሼር በማድረግ ለሁሉም ታደርሱልን ዘንድ በአሏህ ስም እንጠይቃለን.
*************************
#ሰላም ❤️ #አሏህ #ኢስላም #ሙስሊሙ #ኢስላምጠልነት #አክሱም

 !?🤔👇በአለም ደረጃ  #ዩንቨርስቲ የሚባለውን የትምህርት ስርዓት አስቀድመው የጀመሩት ሙስሊሞች እንደነበሩ ስንቶቻችን እናውቃለን!? 🕌 የአል-ቀረዊዪን ዩኒቨርሲቲ (ሞሮኮ) - በ859 ዓ.ል,...
26/03/2026

!?🤔👇
በአለም ደረጃ #ዩንቨርስቲ የሚባለውን የትምህርት ስርዓት አስቀድመው የጀመሩት ሙስሊሞች እንደነበሩ ስንቶቻችን እናውቃለን!?

🕌 የአል-ቀረዊዪን ዩኒቨርሲቲ (ሞሮኮ)

- በ859 ዓ.ል, በፋጢማ አል-ፊህሪ በትምህርት ዘርፍ አቅኚ ሴት የተመሠረተ ሲሆን፣ በዩኔስኮ እና በጊነስ ወርልድ ሪከርድስ በዓለም ላይ በተከታታይ የዲግሪ ሽልማት የሚሰጠው ጥንታዊና ቀደምት ዩኒቨርሲቲ እንደሆነ እውቅና ተሰጥቶታል።

- በታሪክ ለእስልምና ጥናቶች፣ለሂሳብ፣ ለህክምና እና ለሥነ ፈለክ ጥናት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል።

#እድሜው:- 1,167 አመት
---
🕌 የአዝ-ዘይቱና ዩኒቨርሲቲ(ቱኒዚያ)

- በ737ዓ.ል የተመሰረተ ሲሆን
በእስልምና ሥነ-መለኮት፣በአረብኛ ቋንቋ እና በእስልምና ስልጣኔ ላይ በማተኮር፣ በሰሜን አፍሪካ እንደ ዋና የአዕምሮ ማዕከል ሆኖ እያገለገለ ይገኛል።

#እድሜው:- 1,289 አመት
---
🕌 የአል-አዝሃር ዩኒቨርሲቲ (ግብፅ)

- በ970–972 ዓ.ል አካባቢ የተመሰረተ ሲሆን ይህም ከጥንታዊ የእስልምና ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ያደርገዋል።
- በዓለም ላይ ትልቁ የእስልምና ዩኒቨርሲቲ በመባል የሚታወቀው አል-አዝሃር 81 ኮሌጆች፣9 ተቋማት፣ 359 ክፍሎች እና 6 ሆስፒታሎች አሉት።
በታሪክ በእስልምና ሕግ፣ በሥነ-መለኮት፣ በሰዋሰው እና በአጻጻፍ ስልት የተካነ ቢሆንም፣አሁን ላይ ሕክምና፣ምህንድስና እና ዘመናዊ ሳይንስንም አካቶ ያቀርባል።

እነዚህ ሶስቱ እድሜ-ጠገብ ዩኒቨርሲቲዎች
መካከለኛውን የእስልምና አስተሳሰብን በመቅረጽ ረገድ ማዕከላዊ ሚና በመጫወት እና አለም ላይ ላሉ ለእስልምና ምሁራን ማጣቀሻ ሆነው እየቀጠሉ ይገኛሉ።

#እድሜው:- 1,056 አመት
*************************
ስለዚህች ከ3ሺ አመታት በላይ ታሪክ ያላትና እነ ኢማሙ ሙስሊምና ኢማሙ አልቡኻሪይ የመሳሰሉ ዑለሞችን ያፈራችዋ ሀገርስ ምን ያህል ያውቃሉ!!?
👇 👇👇👇
https://youtu.be/MbIeaiFEMO4

አድምጡትና ሀሳብ አስታየታችሁን አካፍሉን እስኪ
*************************

24/03/2026

!??
አለም ላይ ስሟ ከሺዓን ጋር ተያይዞ በስፋት የምትነሳዋ #ኢራን
የእነዚህ ሀያላን ዑለሞች መፍለቂያ እንደነበረች ያውቃሉ!?
1. ኢማሙ ሙስሊም
2. አል-ራዚይ
3. አል-ቡኻሪይ
4. አል-ኸዋሪዝሚይ
5. ዑመሩል ኺያር
6. አ-ጠውሲይ
7. ኢብኑ-ሀያም
8. አል-ፋራቢይ
9. ኢብኑ ሲና
10. ኢማሙ-ቲርሚዚይ
እንዲሁም እጅግ በርካታ ዑለሞች የወጡባት ሀገር ነበረች።
እጅግ አስደናቂ የሆነውን የ3ሺ አመት ታሪኳን አጠር አድርገን አቅርበነዋል እንዳያመልጣችሁ።
ሊንኩን በመጀመሪያው ኮሜንት ላይ አስቀምጠነዋል👇
****************************
❤️ #ኢራን #ሰላም

አሏሁ አክበር,አሏሁ አክበር,አሏሁ አክበር,ላ ኢላሀ ኢለሏሀ አሏሁ አክበር አሏሁ አክበር ወሊላሂል ሀምድ።  Quba Tube - ቁባ ትዩብ *********************************
19/03/2026

አሏሁ አክበር,አሏሁ አክበር,አሏሁ አክበር,ላ ኢላሀ ኢለሏሀ አሏሁ አክበር አሏሁ አክበር ወሊላሂል ሀምድ።
Quba Tube - ቁባ ትዩብ
*********************************

🤐  ፡ሚስጥሮችን መናገር ነው ● ምስጢርን መናገር ወይም ማውጣት:-በጽሑፍ፣በምልክት ወይም በንግግር ሊሆን ይችላል፣ሁሉም ሀራም ነው። ምክንያቱም ጉዳት ስለሚያደርስ እና የጓደኝነትን፣የወንድማማ...
27/01/2026

🤐 ፡
ሚስጥሮችን መናገር ነው

● ምስጢርን መናገር ወይም ማውጣት:-በጽሑፍ፣በምልክት ወይም በንግግር ሊሆን ይችላል፣ሁሉም ሀራም ነው። ምክንያቱም ጉዳት ስለሚያደርስ እና የጓደኝነትን፣የወንድማማችነት መብቶች ላይ ቸልተኝነት ስለሚያሳይና የእርስ-በርስ መተማመንን ስለሚያሳጣ ጭምር ፍጹም የተከለከለ ነው።

፡ 🤐

● ጃቢር ኢብኑ ዓብዲላህ እንደተዘገቡት የአሏህ መልእክተኛ (ﷺ)፡- "አንድ ሰው አንድን ነገር ተናግሮ፣ከዚያም ዘወር ካለ (የተናገረው ነገር)እምነት ነው"። ብለዋል.

🚫 ሚስጥርን መናገር የከሀዲነት ምልክት ነው፡-

ሐሰኑል-ብስሪይ(አላህ ይዘንላቸውና)እንዳሉት፡- "በእርግጥም ከክህደት መካከል አንዱ የወንድምህን ምስጢር አደባባይ አውጥቶ መናገር ነው።"

● ምስጢሮችን የመግለጥ ክልከላና ማስጠንቀቂያ ከዓለማቱ ጌታ አሏህ የተሰጠ ቀጥተኛ ትእዛዝ ነው። አሏህ በቁርኣኑ፡-
﴿يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ لَا تَخُونُوا۟ ٱللَّهَ وَٱلرَّسُولَ وَتَخُونُوٓا۟ أَمَٰنَٰتِكُمْ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ﴾
"{እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አሏህንና መልክተኛውን አትክዱ፡፡ አደራዎቻችሁንም እናንተ እያወቃችሁ አትክዱ፡፡"} አል-አንዓም 27

🏠 የቤት ውስጥ ሚስጥሮች ክብርና ክልከላ፡-

ከታማኝነትና ከሚስጥር ጠባቂ ማንነት ምልክቶችና ትርጉሞች መካከል አንዱ የቤትን ምስጢር መጠበቅ ነው።

● ኢማሙ ሙስሊም ከአቡ ሰዒድ አል-ኹድሪይ እንደተረኩት የአሏህ መልእክተኛ(ﷺ)፡- {"በእርግጥም በትንሣኤ(ቂያማ)ቀን አሏህ ዘንድ ከሚቆሙት በጣም መጥፎ ሰዎች መካከል፣"ባል ማታ ከሚስቱ ጋር ግንኙነት ያደርግና፣ሚስትም ከባሏ ጋር ግንኙነት አድርጋ ታድርና ከዚያም ጠዋት እሷም ሚስጥሯን እሱም ሚስጥሩ ለሌላ የሚያሰራጭ ሰው ነው።"} ብለዋል.

⚖️ ሸሪዓዊ እና ሰባዊ ፍርዱ፡

የሌሎችን ሚስጥሮችን መግለጥና መናገር ክህደት ነው፣
የታማኝነትን ስብእና የማጣት ባህሪም ነው። በሚስጥሩ ባለቤት ላይ ጉዳት አደረሰም አላደረሰ፣ሀራም(ክልክል) ነው።

● ትልቁ ሰው(ﷺ):-{"በአሏህ እና በመጨረሻው ቀን የሚያምን፣መልካም ነገርን ይናገር አልያም ዝም ይበል"} ባሉት መሰረት የምንናገረው ነገር ለአድማጩ ጠቃሚ ከሆነ በቀር ዝምታን ማዘውተር ጸጋ ነውና እንላበሰው።
ዝምታን ማዘውተር ከብዙ ጸጸቶች፣ጥፋቶች ይጠብቃል።

:-በሳል ሰው ማለት የሚያውቀውን ሁሉ የሚናገር ሳይሆን የሚናገረው ነገር ትክክልና ጠቃሚ መሆን አለመሆኑን ለይቶ የሚያውቅ ነው።

#ሰላም.

t.me/QubaTube

*********************************
#ቁባትዩብ #ተሰዉፍ #ኢስላም ❤️ #ሰላም

20/01/2026

ኢኽዋኖች VS ሱኒ|| ሙሉውን ቪዲዮ ኮሜንት ስር ባለው ሊንክ ያገኙታል።
**************************************
#ቁባትዩብ #ኢስላም #ሙስሊሙ #ሙስሊሙን #ኢኽዋን

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Quba Tube - ቁባ ትዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Quba Tube - ቁባ ትዩብ:

Shortcuts

Share