ልሳነ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ/yetwahdo page

ልሳነ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ/yetwahdo page የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ኣስተምህሮዎች

+ ቅዳሴ የማይችሉት ካህን + ታሪኩ የኾነው በግብጽ ሀገር ነው። የተወሰኑ ምዕመናን ተሰብስበው ቀሲስ ዳንኤል ዮሐና የተሰኙትን ካህን ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ከሰሷቸው። የክሱ ጭብጥ "ካህኑ...
29/08/2025

+ ቅዳሴ የማይችሉት ካህን +

ታሪኩ የኾነው በግብጽ ሀገር ነው። የተወሰኑ ምዕመናን ተሰብስበው ቀሲስ ዳንኤል ዮሐና የተሰኙትን ካህን ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ከሰሷቸው። የክሱ ጭብጥ "ካህኑ የቅዳሴውን ጸሎት በቅብጥ ቋንቋ ለማለት ተቸግረዋል፤ በአግባቡ በቃላቸው ማድረስ አይችሉበትም" የሚል ነበር። መቼም "ቅዳሴ መቀደስ አይችልም" የሚል ክስ በካህን ላይ ሲመጣ ከባድ ነውና፤ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ቶማስ ጉዳዩን እንደሰሙ ካህኑ በአስቸኳይ እንዲመጡ መልእክት ላኩባቸው። ቀሲስ ዳንኤል ዮሐናም ጥሪው በደረሳቸው በማግስቱ ለጉዞው መዘጋጀት ጀመሩ። አህያቸውን እየጫኑ እያለም ባለቤታቸው በመንገድ ላይ ረሃብ ከጸናባቸው እንዲበሉት በሚል የጋገረችላቸውን ኅብስት በመሀረብ ጠቅልላ ሰጠቻቸው። ካህኑ ቀሲስ ዮሐናም ኅብስቱን ተቀብለው የሀገረ ስብከቱ መቀመጫ ወደ ሆነው አል-ሚኒያ ጉዞ ጀመሩ።

በመንገድ ላይ እየሄዱ ሳለም ሊቀ ጳጳሱ ሊጠይቁኝ ይችላሉ ብለው ያሰቧቸውን የቅዳሴ ክፍሎች በቅብጥ ቋንቋ እያዜሙ መለማመድ ጀመሩ። በዚህ ሁኔታ ተጉዘውም ወደ አል-ሚኒያ ደረሱ።

ቀሲስ ዳንኤል ዮሐና ወደ ሊቀ-ጳጳሱ ብጹዕ አቡነ ቶማስ ቢሮ ሲገቡ ግን ሊቀ-ጳጳሱ ባዩት ሁኔታ ተደናገጡ። ቀሲስ ዳንኤል በእጃቸው በመሃረብ የተጠቀለለ እና በደም የራሰ ኅብስት ይዘዋል። ሊቀ ጳጳሱም በመንገዳቸው ምን እንዳጋጠማቸው ቀሲስ ዳንኤልን ጠየቁ። ቀሲስ ዳንኤልም በትህትና መንፈስ ኾነው "በዚህ መሀረብ የተጠቀለለው ኅብስት ነው። በመንገድ እየመጣሁ እያለሁ ቅዳሴውን በቅብጥ ቋንቋ እየተለማመድኩ ነበር" ብለው መለሱ። ብጹዕ አቡነ ቶማስ በሁኔታው ተደነቁ። ለካስ በካህኑ ጸሎት ኅብስቱ የጌታችንን አማናዊ ቅዱስ ሥጋ ሆኖ ነበር።

ሊቀ ጳጳሱ የጌታችንን አማናዊ ቅዱስ ሥጋ በቦታው ለነበሩት ሰዎች ካቀበሉ በኋላ ወደ ቀሲስ ዳንኤል ዮሐና በመዞር "በሉ ወደመጡበት ቤተክርስቲያን ይመለሱ፤ ከዚህ ቀደም ሲያደርጉ እንደነበረው አገልግሎትዎን ይቀጥሉ" ብለው አሰናበቷቸው። እርሳቸውን ለመፈተን ተሰብስቦ የነበረውም ጉባዔ ተበተነ።

ምንጭ፦ “Mallawy’s Blessed Priest: The Late Hegumen Daniel Youhanna Maqa" by Fr. Youannis Kamal

" እንኳን ለቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ !"በዚህ ዕለት የምንማራቸው በርካታ ቁም ነገሮች  !!     ሐምሌ 7 ቅድስት ሥላሴ ቤተ አብርሃምን መጎብኘታቸው ይታሰብበታል። ከሊቅ እስ...
14/07/2025

" እንኳን ለቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ !
"በዚህ ዕለት የምንማራቸው በርካታ ቁም ነገሮች !!

ሐምሌ 7 ቅድስት ሥላሴ ቤተ አብርሃምን መጎብኘታቸው ይታሰብበታል። ከሊቅ እስከ ደቂቅ “የብዙዎች አባት” ተብሎ የሚጠራውን የአብርሃምን ታሪክ የማያውቅ የለም። ይህ ቅዱስ አባት እንግዶችን የመቀበል ጸጋ የተሰጠውና በዚህም ሳያውቀው በአምሳለ አረጋዊ የተገለጡለትን ቅድስት ሥላሴን በእንግድነት ለመቀበል የበቃ አባት ነው።

በዚህ ዕለት ከምንማራቸው በርካታ ቁም ነገሮች ጥቂቶችን ለመጥቀስ፦

" እንግዶችን መቀበል እንደሚገባና ይህን በማድረጋችንም ሳናውቀው ቅድስት ሥላሴን፣ ቅዱሳን መላዕክትን፣ ድንግል ማርያምን ወይም ቅዱሳንን በእንግድነት የመቀበልና በረከት የማግኘት ዕድል ፈንታ ሊገጥመን እንደሚችል እንማርበታለን።

" አብርሃም እንግዳ የመቀበልን ምግባር ይሰራ የነበረው በእንግድነት በሚኖርባት የከነዓን ምድር እንደ ነበረ ሁሉ እኛም መልካም ሥራ ለመሥራት የተመቻቸ ጊዜና ቦታ ሳንጠብቅ በሁሉም ጊዜና ሥፍራ መልካም ማድረግ እንደሚገባን እንማርበታለን። ኑሮ ባይደላንም እንኳን ከትርፋችን ሳይሆን ከጉድለታችን መስጠትን እንማርበታለን። መስጠት ከማግኘት ሳይሆን ከልማድ መሆኑን እንማርበታለን።

" ዲያብሎስ በሰው አምሳል ራሱን ገምሶ፥ ደሙን አፍስሶ “አብርሃም እንዲህ አደረገኝ” ብሎ እንግዶች ወደ አብርሃም ድንኳን እንዳይሄዱ ቢጥርም ተንኮሉን ያወቁት ቅድስት ሥላሴ ወደ አብርሃም ድንኳን በእንግድነት መሄዳቸው እኛም እንደ አብርሃም አካሄዳችንን ከእግዚአብሔር ጋር ካደረግን የዲያብሎስ ሴራ ሊያሸንፈን እንደማይችል እንማርበታለን።

" አብርሃምና ሣራ ካረጁ በኋላ ልጅ እንደሚወልዱ ቅድስት ሥላሴ መናገራቸው እኛም መካን ብንሆን ወይም በሳይንስ የሚታወቀው የመውለጃ ዕድሜያችን ቢያልፍም እንኳን እምነት ካለን እግዚአብሔር በልጅ ሊባርከን እንደሚችል እንማርበታለን። እግዚአብሔር መካኖችን ወላድ፥ ወላዶችን ደግሞ መካን ማድረግ የሚችል አምላክ ነውና መፍትሔው በርትቶ በእምነት መጸለይ እንጅ መፋታት እንዳልሆነ እንማርበታለን።

የሥሉስ ቅዱስ ቸርነት፥ የአባታችን የአብርሃም በረከት
በሁላችን ላይ ይደር አሜን !

ቅዱስ ሚካኤል - መልአከ ምክሩ***በቅዱሳት መጻሕፍት እግዚአብሔር ከቅዱሳን ጋር ስለሚያደርገው የምክር ጉባኤ ተጽፏል። ይህ መለኮታዊ ምክር ( the devine council) እግዚአብሔር ስለ...
19/06/2025

ቅዱስ ሚካኤል - መልአከ ምክሩ
***
በቅዱሳት መጻሕፍት እግዚአብሔር ከቅዱሳን ጋር ስለሚያደርገው የምክር ጉባኤ ተጽፏል። ይህ መለኮታዊ ምክር ( the devine council) እግዚአብሔር ስለሚያደርገው እና ስለፍርዱ ከተመረጡ ቅዱሳን ጋር የሚያደርገው ነው። ይህን የሚያደርገውም ከቅዱሳንም መርጦ ላከበራቸው ያለውን ክብር ያሳይ ዘንድ ከሥልጣኑ በጸጋ እያሳተፋቸው እንጂ ከእግዚአብሔር ፍርድ እና ምክር የሚጎድል ኖሮ እነርሱ ሊሞሉለት አይደለም።
የመጀመሪያው ይህን የተመረጡ ቅዱሳን ምክር የሚያሳይ ጥቅስ መዝ. 81/82 ነው፦ “እግዚአብሔር በአማልክት ማኅበር ቆመ፥ በአማልክትም መካከል ይፈርዳል።"
ሌላኛው ደግሞ "እግዚአብሔርን በሰማይ የሚተካከለው ማን ነው? ከአማልክትስ ልጆች እግዚአብሔርን ማን ይመስለዋል? በቅዱሳን ምክር እግዚአብሔር ክቡር ነው፤ በዙሪያው ባሉት ሁሉ ላይ ታላቅና ግሩም ነው፤" የሚለው ነው። (መዝ. 89፥6-7)
***
ቅዱስ ሚካኤል መልአከ ምክሩ የሚባል የመላእክት አለቃ ሆኖ የዚህ መለኮታዊ ምክር አካል ስለሆነ ነው። 'ተሾመ' የሚለው ቃል ይህን መመረጥ ይገልጣል። ከሌሎች መላእክት በተለየ በዙፋን ላይ ተቀምጦ መሳሉም ለዚሁ ነው። ድንግል ማርያምም የዚህ ማኅበር አካል ነች። ቀድሞ የክርስቶስ ምሳሌ የሆነው ሰሎሞን ለእናቱ ያለውን ክብር ይገልጥ በጎኑ ዙፋን አስቀምጦ ያማክራት ነበር። (1ኛ ነገ. 2፥19) ዳዊትም "ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች" ብሎ ተናግሮላታል። (መዝ. 44/45፥9)
ሐዋርያትም እንዲሁ ናቸው፤ ጌታ በ12ቱ የእሥራኤል ነገዶች ላይ ሲፈርዱ በዙፋን እንደሚቀመጡ መናገሩ የመለኮታዊው ምክር አካላት እንዳደረጋቸው ያሳያልና። (ማቴ. 19፥28)
ይህንም ነቢዩ ዳንኤል ቀድሞ ተናግሮታል፦ “ዙፋኖችም እስኪዘረጉ ድረስ አየሁ፥ በዘመናት የሸመገለውም ተቀመጠ፤ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ፥ የራሱም ጠጕር እንደ ጥሩ ጥጥ ነበረ፤ ዙፋኑም የእሳት ነበልባል ነበረ፥ መንኰራኵሮቹም የሚነድድ እሳት ነበሩ።” (ዳን. 7፥9) ነቢዩ 'ዙፋኖች' ያለው እግዚአብሔር ብዙ ዙፋኖች ኑረውት ሳይሆን የተመረጡ ቅዱሳን የሚሳተፉበትን ከእግዚአብሔር ፍርድ ሲወጣ ቀድመው የሚያውቁ እና በባለሟልነት የሚማልዱ የቅዱሳን ጉባኤ ክብራቸውን ለማመልከት ነው።
***
ሰኔ 12 የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል የሚከበረው የዚህ ታላቅ መልአክ ተአምራትና ረድኤት የሚታሰቡበት ቀን ነው።

""አፎምያን ማዳኑ""
የአፎምያ ታሪክ የቅዱስ ሚካኤልን ተአምራዊ ረድኤት ከሚያሳዩ ታላላቅ ገድሎች አንዱ ነው። አፎምያ የምትባል አንዲት ታማኝ ሴት ነበረች። የቅዱስ ሚካኤልን በዓል በየወሩ ትዘክር ነበረ
ይሁን እንጂ ሰይጣን በልዩ ልዩ መንገድ ይፈትናት ነበረ ከዕለታት በአንድ ቀንም ሰይጣን ቅዱስ ሚካኤል መስሎ መጣባት የቅዱስ ሚካኤልን ስዕለ አድኅኖ ይዛ መጣችበት አንቆ ሲይዛት
ቅዱስ ሚካኤል በድንገት በመገለጥ ከሞት አዳናት። ይህ ተአምር የእግዚአብሔርን ታላቅነትና የመላእክቱን ፈጣን ረድኤት የሚያሳይ ነው። ታሪኩ የቅዱስ ሚካኤል የፍትህ ተሟጋችነትና የመከራ ደራሽነት ምሳሌ ሆኖኗል።

""ባህራንን ማዳኑ"
ባህራን በባሕር ውስጥ ለሞት የተቃረበ ሰው ነበር። በዚያን ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል በድንገት ተገልጦ ህይወቱን አድኗታል የሞቱንም ደብዳቤ ዘደ ሕይወት ቀየረለትና አከበረው
ይህ ተአምር ቅዱስ ሚካኤል "ፍጡነ ረድኤት" (ፈጣን ረዳት) መሆኑን ያሳያል። እግዚአብሔር በመላእክቱ አማካይነት ፈጣን እርዳታ እንደሚሰጥና አደጋ ላይ ላሉ ሰዎች ሁልጊዜ ቅርብ እንደሆነ ያመለክታል።
ለኛም ፍጡነ ረድኤት መልአክ መሆኑ
ከላይ ከተጠቀሱት ታሪኮች በመነሳትና ከቅዱስ መጽሐፍና ከሊቃውንት አስተምህሮ በመጣመር፣ ቅዱስ ሚካኤል ለእኛም ፍጡነ ረድኤት መልአክ እንደሆነ እናምናለን። """ በሰማይም ሰልፍ ሆነ ሚካኤልና መላእክቱ ዘንዶውን ተዋጉ።ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋራ ተዋጋ፥አልቻላቸውምም፥ከዚያም ወዲያ በሰማይ ስፍራ አልተገኘላቸውም።ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው፥ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ ርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ ወደ ምድር ተጣለ መላእክቱም ከርሱ ጋራ ተጣሉ።ታላቅም ድምፅ በሰማይ ሰማኹ እንዲህ ሲል፦አሁን የአምላካችን ማዳንና ኀይል መንግሥትም የክርስቶስም ሥልጣን ሆነ፥ቀንና ሌሊትም በአምላካችን ፊት የሚከሳቸው የወንድሞቻችን ከሳሽ ተጥሏልና።እነርሱም ከበጉ ደም የተነሣ ከምስክራቸውም ቃል የተነሣ ድል ነሡት፥ነፍሳቸውንም እስከ ሞት ድረስ አልወደዱም።ስለዚህ፥ሰማይና በውስጡ የምታድሩ ሆይ፥ደስ ይበላችኹ ለምድርና ለባሕር ወዮላቸው፥ዲያብሎስ ጥቂት ዘመን እንዳለው ዐውቆ በታላቅ ቍጣ ወደ እናንተ ወርዷልና።(የዮሐንስ ራእይ12:7-12) ከበዓሉ ረድኤት በረከት እግዚአብሔር ይክፈለት እንደቅዱሳኑ ጥላ ከለላ ይሁነን ያማልደን ያስታርቀን።
በዚህ ሁሉ ታላቁ መልአክ ሚካኤል አለ! ኦ ሚካኤል ኦ ሚካኤል! ከእግዚአብሔር የተሰጠህ ክብር ታላቅ ነው። ለጎስቋሎች ባሮችህ ለምንልን። አሜን።

እንኳን ለበዓለ ጰራቅሊጦስ አደረሰን 🌲🌲🌲🍀🍀🍀 ጰራቅሊጦስ🍀🍀🍀🌲🌲🌲👉 ጰራቅሊጦስ በተለየ አካሉ መንፈስ ቅዱስ የሚጠራበት የመንፈስ ቅዱስ ስም ነው፡፡ ጰራቅሊጦስ ማለት አጽናኝ (መሰተፍሥሒ) የ...
08/06/2025

እንኳን ለበዓለ ጰራቅሊጦስ አደረሰን
🌲🌲🌲🍀🍀🍀 ጰራቅሊጦስ🍀🍀🍀🌲🌲🌲

👉 ጰራቅሊጦስ በተለየ አካሉ መንፈስ ቅዱስ የሚጠራበት የመንፈስ ቅዱስ ስም ነው፡፡ ጰራቅሊጦስ ማለት አጽናኝ (መሰተፍሥሒ) የሚያስደስት (ከሳቲ) የሚገልጽ (መስተሥርዩ) ኃጢአትን የሚያስተሰርይ የሚል ትርጓሜ አለው፡፡

👉 ከጌታችን ትንሣኤ ከሃምሳኛው ቀን ጀምሮ እስከ ሰኔ አስራ ሰባት ድረስ ያለው ጊዜ ዘመነ ጰራቅሊጦስ ይባላል፡፡ በዚህ ዘመን የሚዘመሩት መዝሙራት የመንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት መሰጠትንና የጌታችንንም ትንሣኤና ዕርገት የሚመለከቱ ናቸው፡፡

👉 እሥራኤላውያን የፋሲካን በግ ካደረጉ በኋላ ከግብጽ ባርነት ነጻ ወጥተዋል ከግብጽ ባርነት እግዚአብሔር ነጻ እንዳወጣቸው ለማዘከርም በየዓመቱ የፋሲካን በዓል ያከብራሉ ከዚህ በዓል ቀጥሎ ሰባት ሱባኤ ሲፈጸም ማለትም በ50ኛው ቀን በዓለ ሰዊት / የእሸት በዓል / ያከብራሉ መከር በደረሰ ጊዜ በመጀመሪያ ከሚወቁት እህል ለእግዚአብሔር መሥዋዕት የሚያቀርቡበት ነው፡፡ (ዘሌ.23፤1-39) እነዚህንም በዓላት ለማክበር በዓለም ዙሪያ ተበትነው የሚኖሩት ሳይቀሩ ወደ ኢየሩሳሌም ይመጡ ነበር፡፡

👉 ሐዋርያት ዕርገቱን ዐይተው ነገረ ምጽአትን ከመላእክትም ተረድተው ወደ ማደሪያቸው ተመልሰው የተሰጣቸውን ተስፋ ይጠባበቁ ጀመር፡፡ የተሰጣቸው ተስፋ ‹‹ እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለው እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ቆዩ ›› ሉቃ 24፡49 የሚል ነበር ፡፡ ተስፋውም መንፈስ ቅዱስ በወረደላቸው ጊዜ ሰማያዊ ሃብትን እውቀትን ገንዘብ ታደርጋላችሁ በአራቱ ማዕዘን ትመሰክሩልኛላችሁ የሚል ነው፡፡ (የሐዋ.1፤8-12)

👉 ? ሉቃ 24፡49

1. ከሃይማኖት ከምግባር እንዳይወጡ መንፈስ ቅዱስ ከመቀበላቸው በፊት ፈሪዎች የሚረሱ ነበሩና ፍርሃታቸው እስከ መካድ እንዳያድርሳቸው ፡፡ በኢየሩሳሌም ቆዩ ባይላቸው ኖሮ ሲገቡ ሲወጡ አይሁድ ያገኟቸውና መከራ ቢያጸኑባቸው ሃይማኖት መካድ ከምግባር መውጣት ይመጣልና ፡፡

2. ለመነኮሳት ለገዳማውያን ( ለባህታውያን ) በገዳማቸው ጸንተው መኖር እንዳለባቸው ሲያስተምር ነው ፡፡ ለጊዜው ለ120 ቤተሰብ ሲሆን ፍጻሜው ለመነኮሳት ነው ኢየሩሳሌም የገዳም ምሳሌ ናት ርግብ የታቀፈችውን እንቁላል ትታ በሔደች ዙረት ባበዛች ጊዜ እንቁላሉ እንዳይፈለፈል እንደምታደርግ ሁሉ ባዕቱን ትቶ የሚሔድ መነኩሴ ፍሬ አያፈራምና፡፡

3. በሃይማኖት መጽናት እንደሚገባ ለማጠየቅ ነው ፡፡ ምሥጢረ ሥላሴ ምሥጢረ ሥጋዌ ምሥጢረ ጥምቀት ምሥጢረ ቁርባን ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን ሁሉ በኢየሩሳሌም ስለተገለጸ ኢየሩሳሌም በሃይማኖት ትመሰላለች በኢየሩሳሌም በሃይማኖት ብትጸኑ ሐዋርያት ያገኙትን ክብር ታገኛላችሁ ሲል ነው አንድም ኢየሩሳሌም በቤተክርስቲያን ትመሰላለች ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተክርስቲያን ይፈጸምባታልና በቤተክርስቲያን ብትጸኑ ሐዋርያት ያገኙትን ክብር ታገኛላችሁ ሲል ነው ፡፡

4. መንፈስ ቅዱስ ዝርው በሆነ ልቦና እንደማያድር ለማጠየቅ ልቡናው በሃይማኖት በትህትና በፍቅር በጸና ላይ እንደሚያድር ለማጠየቅ
ተናግሮ የማያስቀር ምሎ የማይከዳ ልዑል አምላክ ነውና በገባላቸው ቃል መሠረት ሞትን ድል አድርጎ በተነሳ በ50ኛው ቀን ባረገ በ10ኛው ቀን ለሐዋርያት ፀጋ መንፈስ ቅዱስ በእሳት አምሳል ሰደደላቸው ፡፡

👉 ከላይ እንደተጠቀሰው መቶ ሃያው ቤተሰብ የሚባሉት 12ቱ ሐዋርያት 72ቱ አርድእት 36ቱ ቅዱሳት አንስት በማርቆስ እናት ቤት በጸሎት ላይ ሳሉ ጌታ ከሙታን ከተነሳ በሃምሳኛው ባረገ በአስረኛው ቀን ተስፋው ተፈጸመ፡፡ ሐዋ.2፡1 ድንገት ከወደ ሰማይ እንደ ዐውሎ ነፋስ ድምጽ ያለ ነጎድጓድ ተሰማ ያሉበትን ቤት መላው፡፡ ላንቃ ላንቃ ያለው እሳት ሆኖ ታያቸው፡፡ በሁሉም አደረባቸው ኃይል የሚሆናቸውን ሀብት እውቀት ገንዘብ አደረጉ፡፡ የማያልቅ ሃብቱን ጸጋውን ለመቶ ሃያው ቤተሰብ አደላቸው ከዚህም በኋላ ‹‹ 5500 ዘመን ሲፈጸም በሥጋዊ በደማዊ ሰው ሁሉ የባህርይ ሕይወቴን መንፈስ ቅዱስን አሳድርበታለሁ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁ / 12ቱ ሐዋርያትና 36ቱ ቅዱሳት አንስት/ ራዕይ ያያሉ ጎበዛዞቻችሁም / 72ቱ አርድእት / ራዕይ ያያሉ›› ተብሎ በነቢዩ ኢዮኤል የተነገረው ቃል ተፈጸመ (ትን. ኢዮ 2፤28-32

👉 ?

በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስ ሲወርድላቸው እመቤታችን ከሐዋርያት መካከል ነበረች ፡፡ በዛ የተገኘችው እንደ ሐዋርያት ከፍርሃታቸው እንዳላቀቃቸው ፣ ምሥጢርን እንደገለጸላቸው በዓለም ሁሉ ቋንቋ እንዲናገሩ እንዳደረጋቸው ለእመቤታችንም አስፈልጓት አይደለም ። የሃይማኖት ምልክት ማረጋገጫ እሷ የሌለችበት ምንም ነገር ስለሌለና ስለማይጥም እንጂ እርሷማ የመንፈስ ቅዱስ ቤቱ ማደሪያው ነች እንጂ አዲስ እንዲያድርባት አይደለም፡፡

➛ እመቤታችን ከሴት ሐረግ ስለምትገኝ ስለ እመቤታችን የአቤል ምትክ ሴት ተወለደ ፣ እንዲሁም ኖኅ ከእነ ቤተሰቡ ያልጠፋው በዘራቸው እመቤታችን ስላለች ነው፣ በአስቴር ጸሎት እሥራኤላውያን የዳኑት እመቤታችን ስለምትገኝ ነው ፡፡ እመቤታችን በቃና ዘገሊላ ፣ በእግረ መስቀሉ ፣ የሌለችበት ቦታ ስለሌለ በዚህም ታላቅ ቀን ከሐዋርያት መካከል ተገኝታለች ፡፡

➛ በዓላቸው ‹‹በዓለ ሰዊትን›› ለማክበር በኢየሩሳሌም የተሰበሰቡ አይሁድና ወደ አይሁድነት የተመለሱ የተለያዩ ሀገር ሰዎች ድምጽን በሰሙ ጊዜ የሆነውን ለማለየት ለማወቅ ሐዋርያት ወዳሉበት ተሰበሰቡ፡፡ የጌታችን ደቀመዛሙርት በተሰጣቸው የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ፈሪዎች የነበሩ ደፋሮች ሆኑ፤ ፍጹም እውቀት ተሰጣቸው ከኃጢአትና ከእርጅና ታደሱ፡፡ በ72ቱ ቋንቋ ለየሀገሩ ሰው ሁሉ የእግዚአብሔር ቸርነት አስተማሩ፡፡ ሐዋ.2፤7-12 ‹‹ ጉሽ የወይን ጠጅ ጠጥተው ሰክረው ነው ›› እያሉ በሚያላግጡባቸው አይሁድ ፊት እነ ቅዱስ ጴጥሮስ ቆመው በማስተማር ሦስት ሺህ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ፡፡

➛ ዘመነ ጰራቅሊጦስ በተለይም በ50ኛው ቀን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ‹‹ የቤተክርስቲያን የልደት ቀን ›› ሲል ጠርቶታል፡፡ በጌታችን በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደም የተመሰረተችው ቅድስት ቤተክርስቲያን በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ ተመልታ ለሰው ልጆች ሁሉ የድህነት ጥሪን ማሰማት የጀመረችበት ዕለት ስለሆነ ይህ ስም ተሰጥቷታል፡፡

➛ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ባደረገው ስብከት የሕዝቡ ልብ በቃለ እግዚአብሔር ተሞልቶ ሦስት ሺ የሚያህሉ በአንድ ቀን ሰዎች ክርስትናን ተቀብለው በማመን ተጠምቀዋል የሐዋ ሥራ 2፡37 -42

➛ ይህም የሆነው ግንቦት 18 እለት ነው ይህ ቀን ጥንተ ጰራቅሊጦስ ሲሆን በቅዱስ ዴሜጥሮስ ቀመር መሠረት ትንሣኤ ከዋለ በኋላ በሃምሳኛው ቀን ወይም ዕርገት በዋለ በ10ኛው ቀን እንዲውል ተወስኗል ፡፡ሐዋርያት መልካሙን የምሥራች ተስፋ መድረሱን ቃል ሥጋ መዋሐዱን መከራ ተቀብሎ የሞትን ሥልጣን ሽሮ ከሙታን ተለይቶ በሥልጣኑ መነሳቱ በፍቅርና በድፍረት ይመሰክሩ ዘንድ ይህ ጸጋ ተሰጣቸው፡፡

👉 ?

1. ከ10ኛው ማዕረግ የገባን ነበርንና ወደ ቀድሞ ክብራችን እንደተመለስን ለማጠየቅ

2. 10ቱን ትእዛዛት ብንጠብቅ ብንፈጽም ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እንደሚበዛልን ለማጠየቅ

3. 10 ቁጥር የምሉነት የፍጹምነት ምሳሌ እንደሆነ ሁሉ እውነተኛ መንፈስ ቅዱስ እንዳደረባቸው ለማጠየቅ :: ዘፍ 31፡7 ፣ ት.ዳን 1፡12

👉 ዛሬም ቢሆን ይህ ጸጋ እግዚአብሔርን እንደ እግዚአብሔርነቱ በንጽህና በቅድስና ለሚያመልኩት ይሰጣል፡፡ ኤፌ 4፡30 ይህ ማለት ለሁሉም የተለያዩ ቋንቋዎች የመናገር ሃብት ይሰጣል ማለት አይደለም፡፡ ሃብቱ ብዙ የሆነ መንፈስ ቅዱስ በሥላሴ አንድነትና ሦስትነት አምነን የኢየሱስ ክርስቶስ የባህርይ አምላክነት ተገንዝበን የእመቤታችንን ዘለዓለማዊ ድንግልና፣ የቅዱሳንን ክብር ተረድተን ስንጠመቅ እንደፈቃዱ ለአንዱ ማስተማርን ለሌላው መዘመርን ለተቀረው እንደወደደ ይሰጣል፡፡ 1ኛ ቆሮ 12፡4

👉 ይህም እያንዳንዱ ምዕመን በተሰጠው ጸጋ ቤተክርስቲያንን እንዲያገለግል ይረዳዋል፡፡ በጽርሐ ጽዮን በሐዋርያት ላይ የወረደው መንፈስ ቅዱስ ጸጋውን ሰላሙን ያድለን፡፡ አሜን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር

 #ትንሳኤ"ትንሳኤከ ለእለ አመነብርሐነከ ፈኑ ዲበነ"እንኳን ለጌታችንና ለመድሐኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል አደረሠን
19/04/2025

#ትንሳኤ
"ትንሳኤከ ለእለ አመነ
ብርሐነከ ፈኑ ዲበነ"
እንኳን ለጌታችንና ለመድሐኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል አደረሠን

የሕማማት ጥያቄዎችና መልሶቻቸው1 በሕማማት ለምን መስቀል አንሳለምም ወይም አናማትብም ?የመስቀል ክብር እና ኃይል የታወቀው ጌታ በመስቀለ ከተሰቀለ በኋላ ነው በሰሞነ ሕማማት ከሰኞ እስከ አር...
13/04/2025

የሕማማት ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
1 በሕማማት ለምን መስቀል አንሳለምም ወይም አናማትብም ?የመስቀል ክብር እና ኃይል የታወቀው ጌታ በመስቀለ ከተሰቀለ በኋላ ነው በሰሞነ ሕማማት ከሰኞ እስከ አርብ ያሉት ቀናት የዓመተ ፍዳ መታሰቢያ ናቸው በነዚህ ዘመናት ሰዎች የመስቀልን አገልገሎት እንዳልጀመሩ ለማሳየት በሰሞነ ሕማማት በቤተክርስተያን ስርዓት መሰረት መስቀል መሳለምም ሆነ የማማተብ ስርዓት የለም
2 በሰሞነ ሕማማት ለምን አንንሳሳምም?
ይሁዳ ጌታውን በመሳም አሳልፎ ሰጥቶአል እኛም እንደ ይሁዳ ክፋት ካለው መሳሳም መለየታችችንን ለማሰረዳት ከዚሀ በተጨማሪም ፍፁም ሰላም በዘመነ ፍዳ እንዳልነበረ ለማሳየት በሰሞነ ሕማማት እሰከ ምሳሳም የደረሰ ጥብቅ ሰላምታ የለም
3 በሰሞነ ሕማማት የማይፈቀዱ ሌሎቸ ነገሮች ምን ምን ናቸው ? ማንኛውም ለስጋ የሚያደሉ ተግባሮችን መቀነስ እና ቢቻለን አበዛኛውን ጊዜአችንን በቤተ እግዚአብሔር የጌታን መከራ ሕማም በማሰብ በፆም በስግደት በጸሎት ማሳለፍ
በትዳር ያሉ በመኝታ ከመተዋወቅ መታቀብ
ቢቻል አመጋገባችንን ከወትሮው መቀነስ
4 ስለ ሰሞነ ሕማማት በመጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈ አለን?
ነብዩ ኢሳይያስ "በእውነት ደዌአችንን ተቀበለ ሕማማችንንም ተሸክሞአል " ኢሳ53፤4 ይላል ሕማማት የሚለው ቃለ በቀጥታ ከመጽሐፍ ቅዱስ ተወሰደ ሲሆን የጌታን መከራ የምናስብበት ሳምንት ነው የጌታችንን ሞቱን ሕማሙን ማሰብ መዘከር እንደሚገባ ቅዱስ ጳውሎስ እነዲህ ይላል
" ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና" 1ቆሮ11፤26
ይህ ሳምንት ለአይሁድና ለመሰሎቻቸው የደስታ ወቅት ቢሆንም ለክረስትያኖች በጥልቅ ኅዘን ውስጥ የሚገቡበት ሳምንት ነው እንዲሀ ተብሎ እንደተጻፈ'' እናንተ ታለቅሳላችሁ ሙሾም ታወጣላችሁ ዓለም ግን ደስ ይለዋል እናንተም ታዝናላችሁ ነገር ግን ኃዘናችሁ ወደ ደስታ ይለወጣል'' ዮሐ16፤20
በእርግጥ ኃዘናችን ትንሳኤውን እሰክናይ ለጥቂት ጊዜ ቢሆንም ግን እናዝናለን በትነሳኤው ደግሞ ደስታውን እንካፈላለን።
ሰኞ አይሁድ እንዴት እንደሚይዙት ለመማከር ክፉ ጉባኤያቸውን ጀመሩ
''በዚያን ጊዜ የካህናት አለቆች የሕዝብም ሽማግሎች ቀያፋ በሚባለው በሊቀ ካህናቱ ግቢ ተሰበሰቡ ጌታ ኢየሱስንም በተንኮል ሊያስይዙት ሊገሉትም ተማከሩ" ማቴ26፡3_4
ይህንን ጉባዔ ቅዱሰ ዳዊት የከፉዎቸ ጉባዔ እያለ ይጠራዋል
"ብዙ ውሾች ከበውኛልና የክፋተኞች ጉባኤም ያዘኝ" መዝ21፤16
አይሁድ ሰኞ የጀመሩትን ዕረቡ ውሳኔአቸውን አጠናቀው በምሴተ ሐሙስ ከዕራትና ከቁርባን በኋላ ሰይፍና ጎመድ ይዘው መጡ በፈቃዱ ራሱን አሳልፎ ሰጣቸው ያዙትም እስከ አርብ ስድስት ሰአት ሲያንገላቱት ቆይተው ከበዙ መከራ በኋላ ሰቀሉት ዘጠኝ ሰአት ላይ ቅድስት ነፍሱን በፈቃዱ ከቅዱስ ስጋው ለየ ከአሰራ አንድ ሰአት በፊት ዮሴፍና ኒቆዲሞስ በምስጋና ገንዘው ቀበሩት ።
ከሕማሙ ከመከራው በረከት ያሳትፈን
ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን

በሰሞነ ሕማማት የሚጸለዩት እና የማይጸለዩት ጸሎቶች የትኞቹ ናቸው? ሼር በማድረግ ለወዳጆቻችሁ አድርሱ አሳውቁ! ተወዳጆች ሆይ ዛሬ የጌታችንን ሕማም የምናስብበት ሰሞን ነው። እንደ ቅድስት ቤ...
13/04/2025

በሰሞነ ሕማማት የሚጸለዩት እና የማይጸለዩት ጸሎቶች የትኞቹ ናቸው?

ሼር በማድረግ ለወዳጆቻችሁ አድርሱ አሳውቁ!

ተወዳጆች ሆይ ዛሬ የጌታችንን ሕማም የምናስብበት ሰሞን ነው። እንደ ቅድስት ቤተ-ክርስትያናችን ሥርዓት በዚህ በሰሞነ ሕማማት የምንጸልያቸውና ለጊዜው የምንታቀባቸው ጸሎቶች አሉ።

በሰሞነ ሕማማት የምንጸልያቸው ጸሎቶች የትኞቹ ናቸው?

☑️በሰሞነ ሕማማት አጥብቀን የምንጸልያቸው ጸሎቶች ውዳሴ ማርያም:መዝሙረ ዳዊት:ድርሳነ መድኃኔዓለም :ሰይፈ ሥላሴ:ሰይፈ መለኮት:ድርሳነ ማሕየዊ :ውዳሴ አምላክ :ግብረ ሕማማት: ሕማማተ መስቀል :መልክአ መድኃኔዓለም መልክአ ኢየሱስናቸው።

☑️ወለላይቱ እመቤት በዚህ በሰሞነ ሕማም በልጅዋ ምክንያት ብዙ እንግልት ስለደረሰባት የእሷን ምስጋና የሆነውን ውዳሴ ማርያም አናስታጉልም። ውዳሴ ማርያም ማመስገኛ መማጸኛ ስለሆነ እንጸልያለን። ምክንያቱም በዚህ በሰሞነ ሕማማት መከራ ተቀብሎ ሞቶ ሕይወቱን የሰጠንን ጌታ በሥጋ ወልዳለችን በውዳሴዋ እናስባታለን።

☑️የቅዱስ ዳዊት ድርሰት የሆነው ታላቁ መዝሙረ ዳዊት በትንቢት ክፍሉ ስለ ጌታችን ሕማም ስቃይ እና ሞት የሚናገርና በዳዊት ምስጋና በምድር የሰው ልጆች በሰማይ ቅዱሳን መላእክት ስለሚያመሰግኑ እንጸልየዋለን።

☑️ሰይፈ ሥላሴ ከሦስቱ አካላት እግዚአብሔር ወልድን የሚያመሰግን አምላክነቱን የሚመሰክር እና የሚመሰጥር በመሆኑ እንጸልየዋለን።

☑️ሰይፈ መለኮት ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ስለ ምስጢረ መለኮት እና ስለ ጌታችን አምላክነት ስለሚናገር እንጸልየዋለን።

☑️በቅዱስ ዮሐንስ ወልደ-ነጎድጓድ የዓይን እማኝነት እና የቃል ምስክርነት የተጻፈና ድርሳነ ማሕየዊ:ግብረ ሕማማት: ሕማማተ መስቀል የጌታችንን መከራ ስቃይ እንግልት እና ሞት በልዩ ሁኔታ የሚናገሩ በመሆናቸው ብንጸልያቸው በዓይነ ሕሊና ቀራንዮ ወሰዶ በነፍሳችን የጌታችንን ሰማያዊ ውለታ የሚስልብንና በመጸለያችን ልዩ ጸጋና ክብር የሚያሰጡን የቃል-ኪዳን ጸሎቶች በመሆናቸው በዚህ በሰሞነ ሕማማት ብንጸልያቸው እጅጉን እንጠቀምበታለን።
ውዳሴ አምላክም መልክአ መድኃኔዓለም መልክአ ኢየሱስ እና ድርሳነ መድኃኔዓለም የጌታችን ምስጋና በመሆኑ መጸለይ እንችላለን። ከዚህ በተጨማሪ አርጋኖንና ጸሎተ ባርቶስን ልዩ ፈተና ያለብንና እመቤታችንን የምንወድ መጸለይ አንከለከልም። ዋናው ትኩረታችን የጌታ መከራ ስቅለት እና ሞት ላይ ማድረጉን ሳንረሳ።

🔘በሰሞነ ሕማማት የማይጸለዩት ጸሎቶች የትኞቹ ናቸው?

☑️በሰሞነ ሕማማት የማይጸለዩትን ጸሎቶች ጠቅለል አድርገን ስናያቸው ድርሳናት ገድላት እና መልክአ መልኮች ናቸው። ይህም የሆነው በሰሞነ ሕማማት ጌታችን ለእኛ ለሰው ልጆች ብሎ የተቀበላቸውን ስቃይ እና መከራ ሞት የምናስብበት እና የምናለቅስበት እንጂ ሌሎቹን በድርሳናቸው በገድላቸው በመልካቸው የምናመሰግንበት ጊዜ ስላልሆነ ነው። ከስሙ እንደተረዳችሁት ሰሞኑ ሰሞነ ሕማማት የተባለው የጌታ ስቃይና ሞት መታሰብያ ስለሆነ ነው።

የጌታችን ወለታ በሁላችን ላይ ይሳልብን

✝✝✝ የካቲት ➊➏ ኪዳነ ምህረት ✝✝✝                      ➣እንኳን አደረሰን!!!ኪዳነ ምህረት ማለት የምህረት መሐላ ማለት ነው።ከ 33 ቱ በዓላተ እግዝእትነ ድንግል ማርያም አ...
22/02/2025

✝✝✝ የካቲት ➊➏ ኪዳነ ምህረት ✝✝✝
➣እንኳን አደረሰን!!!
ኪዳነ ምህረት ማለት የምህረት መሐላ ማለት ነው።
ከ 33 ቱ በዓላተ እግዝእትነ ድንግል ማርያም አንዱ ነው።
✔ እመቤታችንም ከጌታችን መቃብር እየሄደች በምትለምንበት ጊዜ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና ምን ልታመጣብን ነው በማለት ሊጣሏት ሲመጡ ጌታችንም ከዓይናቸው ሰውሯታል አይሁድም ጠባቂ ቢያቆሙ እመቤታችን ዕለት ዕለት መሄዷን አላቋረጠችም እመቤታችንም እንዲህ ብላ ስትጸልይ ልጄ ወዳጄ ሆይ ከስጋዬ ስጋ ከነፍሴ ነፍስ ነስተህ ሰው በመሆንህ
ዘጠኝ ወር ከ 5 ቀን በማኅጸኔ ያደረክ።
ከአንተ ጋር ሀገር ለሀገር ስለ መሰደዴ መጥተህ ልመናዬን ትሰማኝ ዘንድ እለምንሃለሁ አለች ።
✔ በዚህ ጊዜ ንውጽውጽውትል ሆነ መቃብራት ተሰነጣጠቁ ጌታሽንም እልፍ ከእልፍ መላእክቱ ጋር መጥቶ ሰላም ለኪ ማርያም ምን እንዳደርግልሽ ትለምኚኛለሽ አላት ።
✔ እርሷም መታሰቢያዬን ያደረገውን ስለ ስሜ ለችግረኛ
የሚራራውን በስሜ ቤተክርስቲያን ያነጸወን መባዕ የሰጠውን
ከሃይማኖት ከፍቅር ጽናት ልጁን በስሜ የጠራውን ሁሉ ማርልኝ ከሞተ ስጋ ከሞተ ነፍስ አድንልኝ አለችው ።
✔ ጌታችንም ይህን ሁሉ እንዳደርግልሽ መሐልኩ ለኪ በርእስየ ወበ አቡየ ህያው ወበመንፈስ ቅዱስ ብሎ ቃል ገብቶላት አርጓል ።
✔ ከመረጥኳቸው ጋራ ቃል ኪዳኔን አደርጋለሁ ተብሎ በዳዊት መዝሙር እንደተጻፈ እግዚአብሔር ከመረጣቸው ሁሉ ጋር ቃል ኪዳን አድርጓል ፤ወደፊትም ያደርጋል ።[
መዝ 89፥3 ] ቃል ኪዳኑም የምህረት ቃል ኪዳን ነው ።
ቅዱሳኑ
ወስበሀት ለእግዚአብሔር ከእመቤታችን ረድኤት በርከት ይክፈለን ✔✔~~ አሜንንንንንንንንንንንንንን

💒 አስተሪዮ ማርያም 💒 #እጅግ አብዝቶ የሚገርመው ሞት ለአዳም የተነገረው ቃል የማይፈጸምበት ሰብአዊ ፍጡር የለም፡፡ መሬትነትና ወደ መሬት መመለስ ኃያላን በጉልበታቸው፣ ነገስታት በሰራዊታቸው...
28/01/2025

💒 አስተሪዮ ማርያም 💒

#እጅግ አብዝቶ የሚገርመው ሞት

ለአዳም የተነገረው ቃል የማይፈጸምበት ሰብአዊ ፍጡር የለም፡፡ መሬትነትና ወደ መሬት መመለስ ኃያላን በጉልበታቸው፣ ነገስታት በሰራዊታቸው፣ ሌላው ቀርቶ አማላካችን እግዚአብሔር በቅድስናቸው ከፍ ያደረጋቸው ቅዱሳን ነቢያት፣ ሐዋርያት፣ ጻድቃንና ሰማዕታት ሁሉ ስጋዊ ሞትን ቀምሰዋል፡፡ እነርሱ ግን በስጋዊ ሞታቸው ወደ ዘለዓለማዊ የክብር እረፍታቸው ነው የሔዱት፡፡ የሕይወትና የሞት ባለቤት እርሱን ወለደችው የቅድስት ድንግል ማርያም ሞት ግን ከሁሉ ይገርማል፡፡ የአምላክ እናቱ ስትሆን ሞትን ግን ቀምሳለች፡፡ ሞትስ ለሟች ይገባዋል የእመቤታችን የቅድስት ማርያም ሞት ግን አስደናቂ ነው፡፡

በምድር ላይ 64 ዓመት የኖረችው ቅድስት ድንግል ማርያም በአባት በእናቷ ቤት ሦስት ዓመት፤ በቤተ መቅደስ ዐሥራ ሁለት ዓመት፤ ከልጇ ጋር ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወራት፤ ከጌታ ስቅለት በኋላ በመስቀል ላይ ሳለ አደራ በሰጠው፣ ጌታ በሚወደው ሐዋርያ፣ በወንጌላዊው በቅዱስ ዮሐንስ ዐሥራ አምስት ዓመታት ኖራለች፡፡ ጌታን የፀነሰችበትን ወራት ስንጨምር እመቤታችን በዚህ ዓለም በሥጋ የቆየችበት ጊዜ ስድሳ አራት ዓመት ይሆናል፡፡ ልጇ ወዳጇ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምታርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ሲነግራት ሞትን መቅመስ እንደማትፈልግ ነገረችው፡፡ እርሱም ስጋን የለበሰ የአዳም ዘር ሁሉ ሞትን እንደሚያይ ነገራት፤ በመላእክት ምስጋና፣ በዳዊት ዝማሬ ቅድስት ነፍሷ ከቅድስት ስጋዋ ተለየች፡፡

የቅድስት ድንግል ማርያም ሞት በሁለት ምክንያት እንደሆነ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ትውፊት ያስረዳል፡፡ የመጀመሪያው “ዓለሙን ሁሉ ፈጥሮ ለሚገዛው ለመለኮት ማደሪያ ለመሆን የበቃችው ከሰማይ የመጣች ብትሆን ነው እንጂ የሰው ልጅስ አይደለችም፤” በማለት የሚነሱ መናፍቃን እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጆችን ለማዳን የሰውን ባሕርይ አለበሰምና ያልተቀበልነው ለዚህ ነው እንዳይሉ ነው፡፡ ሞቷ ግን የሰው ልጅ እጣ ፈንታ የሆነውን ጽዋ እንድትቀበል አድርጓታል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ይህን ሲያስረዳ ለዕብራውያን ሰዎች በላከው መልዕክቱ ዕብ 2÷14-15 “የአብርሃምን ዘር ይዟል እንጂ የያዘው የመላእክትን አይደለም›› አለ፡፡ በዚህም ድንግል ማርያም የአዳም ዘር መሆኗ ታወቀ፡፡

ሁለተኛው ጌታችን በፍርዱ አድልዎ የሌለበት አምላክ መኾኑ ይታወቅ ዘንድ ሥጋ የለበሰ ዅሉ በለበሰው ሥጋ ሞትን ይቀምስ ዘንድ ግድ ነውና ቅድስት ድንግል ማርያም ሞትን ቀመሰች፡፡ ይህን ቅዱስ ያሬድም መስክሯል፡፡ በበዓለ አስተርዕዮ ጥር 21 ቀን ቅድስት ድንግል ማርያም በክብር አርፋለች፡፡ አስተርእዮ ማለት መታየት፣ መገለጥ ማለት ነው። ቃሉ አስተርአየ ታየ፣ ተገለጠ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ነው። ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገባው ቃል ኪዳን መሠረት በሥጋ የተገለጠበት የታየበት፣ አንድነት ሦስትነቱም የተገለጠበት ወቅት በመሆኑ ከልደት በዓል እስከ ጥር መጨረሻ በሙሉ ዘመነ አስተርእዮ በመባል ይታወቃል። የእመቤታችን በዓለ ዕረፍት በዘመነ አስተርእዮ ውስጥ ስለሚከበር “አስተርእዮ ማርያም” ተብሏል።

ፀሎት ልመናዋ ፍቅርዋና በረከትዋ በሁላችን ይደር

እንኳን  ለከተራ  ክብረ በዓል  በሰላም እና በጤና   አደረሳችሁ ❗ከተራ  ምን ማለት ነው?  “ ከተራ”   ከተረ  ከሚለው  የግዕዝ ቃል   የተወረሰ  ሲሆን   አለቃ ኪዳነ  ወልድ ክፍሌ ...
17/01/2025

እንኳን ለከተራ ክብረ በዓል በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ ❗

ከተራ ምን ማለት ነው?

“ ከተራ” ከተረ ከሚለው የግዕዝ ቃል የተወረሰ ሲሆን አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ “ከተረ” ፣ ወሃ ገደበ፣ ውሃ አገደ፣ ውሃ ዘጋ በማለት ወደ አማርኛ ተርጉመውታል ።

“ከተራ” በአጼ ይኩኑ አምላክ መንግስት በ12ኛው ክፍለ ዘመን የተጀመረው እና በአጼ ገብረ መስቀል መንግስት በ15ኛው ክፍለ ዘመን በአደባባይ እንዲከበር የታወጀው የጥምቀት ክብረ በዓል ከመከበሩ አንድ ቀን ቀደም ብሎ የሚከበር ራሱን የቻለ ሰፋ ያለ እምነታዊ ታሪክ ያለው በጥንታዊት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናን በደመቀ ሁኔታ የሚከበር ክብረ በዓል ነው ።

ታዲያ በየአመቱ ጥር 10 የጥምቀት ዋዜማ ዕለት ጀምበር ከመጥለቋ በፊት ቀደም ብለው የቤት ክህነት አገልጋዮች ተሰባስበው ጊዜዊ ውሃ ማጠራቀሚያ ገንዳ በመቆፈር ወይም በአቅራቢያቸው ያለውን ጅረት በመገደብ ለሚቀጥለው ጥር 11 የጥምቀትን ክብረ በዓል ለማክበር የሚሰበሰቡት ምዕመናን እንዲጠመቁ የመጠመቂያ ስፋራ የሚያዘጋጁበት ዕለት ነው።

በተጨማሪ በአቅራቢያ የሚገኙት ቤተክርስቲያናት ተሰብስበው ከዚሁ ከተቆፈረው ገንዳ ወይም ከተገደበው ጅረት አጠገብ ዳስ ወይም ድንኳን ጥለው ታቦቶቻቸውን ያሳድራሉ።

ቅዱሳን አባቶቻችንም በየአመቱ በከተራ ዕለት በዚሁ በአዘጋጁት የመጠመቂያ ስፋራ አጠገብ በጣሉት ጊዚያዊ ዳስ ወይም ድንኳን ውስጥ አንድ ላይ ተሰባስበው እየጸለዩ በማደር እግዚአብሔር ለነብዩ ሙሴ “የታቦት መኖር የእኔ ከአናንተ ጋር የመኖሬ ምልክት ነው” ብሎ የገለጸለትን ቃል ይፈጽማሉ።

የተባረከ ዕለተ ከተራ (የጥምቀት ዋዜማ) ይሁንላችህ።

ጥምቀት ረቡዕ/ ዐርብ ባይውልም ዋዜማው (ጾመ ገሃድ) ይጾማል ?†††ጾመ ገሃድ/ጋድ†††ገሃድ ማለት ለውጥ ወይም ልዋጭ ማለት ነው። በርግጥ የቃሉ ፍቺ ከዘይቤው ጋር አይገናኝም። ይህ ማለት “...
17/01/2025

ጥምቀት ረቡዕ/ ዐርብ ባይውልም ዋዜማው (ጾመ ገሃድ) ይጾማል ?
†††ጾመ ገሃድ/ጋድ†††

ገሃድ ማለት ለውጥ ወይም ልዋጭ ማለት ነው። በርግጥ የቃሉ ፍቺ ከዘይቤው ጋር አይገናኝም። ይህ ማለት “ገሃድ” የሚለውን ቃል ቀጥተኛ ትርጉም ከተመለከትን “ግልጥ” ማለት ነውና። ለምሳሌ በግልጽ ለማለት በገሃድ እንላለን። የቃሉን ፍቺ በዚህ ገትተን ወደ ጾምነቱ ስንመለስ ቤተ ክርስቲያናችን ከሏት አጽዋማት አንዱ “ጾመ ገሃድ” መሆኑን እናገኛለን።

የገሃድ ጾም የሚጾመው በጥምቀት ዋዜማ ብቻ ነው። አንዳንድ ሰዎች ግን ባለማወቅ የልደትን ዋዜማም “ገሃድ” ብለው ይጾማሉ። ነገር ግን የልደት (ገና) ዋዜማ መጀመሪያውኑ በጾመ ነቢያት ውስጥ ያለ በመሆኑ ድርብ ጾም የለምና ለብቻው አይጾምም። በተለምዶ ግን ጾመ ነቢያትን ሳይጾሙ ቆይተው ዋዜማዋን ብቻ የሚጾሙ አሉ። ጾመ ገሃድ ግን የጥምቀት ዋዜማ ብቻ መሆኑን መረዳት ይገባናል። ጥምቀት ረቡዕና ዐርብ በሚውሉበት ጊዜ ቀድመው ያሉት ማክሰኞና ሐሙስ የፍስክ ቀንነታቸው ወደ ጾምነት ተለውጦ ይጾማሉ። በነሱ ለውጥ ጥምቀት የሚውልባቸው የጾም ቀናት (ረቡዕና ዐርብ) የፍስክ ቀን ሆነው ይከበራሉና።

ገሃድ የረቡዕና ዐርብ ለውጥ ነው ብለናል። ነገር ግን ጥምቀት በሌላም ቀን ቢውል የጥምቀት ዋዜማ ይጾማል። በዓለ ጥምቀት እሑድ ቢውል ቅዳሜ ጥሉላት አይበላም። ጥምቀት ሰኞ ቢውል እሑድ ጥሉላት አይበላም። እንደሌሎች የአጽማዋት ቀናት እህልና ውሃ ግን አይጾሙም። አንዳንድ ሰዎች ግን ጥምቀት ሰኞ ሲውል ከቅዳሜና እሑድ አዋጥተው በመጾም ቅዳሜና እሑድ ጥሉላት አይበላባቸውም ይላሉ። ነገር ግን “ገሃድ” አንድ ስለሆነ (ስንክሳር ጥር 10 “ሰላም ለዕለት ዋሕድ ዘስሙ ገሃድ” እንዲል) ጥምቀት ሰኞ ሲውል ቅዳሜን መጾም አጉል የገባ ልማድ ነው።

ምንጭ፦ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ታላቁ ያዘጋጁት “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ” መጽሐፍ፤ ገጽ 130።

💒የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት💒♥    💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐    ✅♥እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡     ✅♥የጌታችን የኢየሱ...
06/01/2025

💒የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት💒♥
💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐
✅♥እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡

✅♥የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውኃ ፈሳሽ አይደለም፡፡ ከጥንት ከመሠረት ጀምሮ በመላእክት፤ በነቢያት ሲነገር፤ ሲሰበክ የመጣ ነው እንጂ፡፡ {{ማቴ.1፥18}}፡፡

✅♥ሰው የመሆኑን ምሥጢር ለመጀመሪያ ጊዜ በማእከለ ገነት የተናገረ እርሱ እግዚአብሔር ነው፡፡

✅♥አባታችን አዳም ከእግዚአብሔር ትእዛዝ ወጥቶ ዕፀ በለስን በልቶ ከጸጋ እግዚአብሔር በተራቆተ ጊዜ /አዳም ኮነ ከመ አሐዱ እምኔነ/ አዳም ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ {{ዘፍ.3፥22}} ብሎ ከሦስቱ ቅዱስ አንዱ ቅዱስ እግዚአብሔር ወልድ በተለየ አካሉ ከእመቤታችን ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው እንደሚሆን ተናግሯል፡፡

✅♥በዚህ ቃል መሠረት /መሪነት/ ቅዱሳን መላእክት ምሥጢረ ትንቢት ተገልጾላቸዋል፡፡ እነሱም የተገለጸላቸውን ምሥጢረ ትንቢት ኀላፍያትንና መጻእያትን ለሚናገሩ ነቢያት ነግረዋቸዋል፡፡

✅♥ቅዱሳን ነቢያትም ከእግዚአብሔር ያገኙትን ከመላእክት የሰሙትን መነሻ አድርገው በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ምሳሌያት በተለያዩ ዘመናት የወልደ እግዚአብሔርን ሥጋዌ ሰብከዋል /ገልጸዋል/ {{ዕብ.1፥1}}፡፡

✅♥ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ፥ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን፡፡
===================================
💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒
♥💒የጌታችን ልደት በትንቢተ ነቢያት💒♥

✅♥ከዓበይት ነቢያት መካከል አንዱ የሆነው ነብየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ የሚከተለውን ትንቢት ተናግሯል፡፡

✅♥እነሆ ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ትለዋለች {{ኢሳ.7፥14 ፣ ሕዝ.44፥1}} ፡፡ በኅቱም ድንግልና ተፀንሶ በኅቱም ድንግልና የተወልደው አማኑኤል ጌታ ነው፡፡ ትርጉሙም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው፡፡

✅♥ነቢዩ በጎላና በተረዳ ነገር “ሕፃን ተወልዶልናል ወልድም ተሰጥቶናል አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፡ ስሙም ድንቅ መካር ኀያል አምላክ የዘለዓለም አባት የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል“ በማለት የሚወለደው ሕፃን የባሕርይ አምላክ የዘለዓለም አባት የሰላም አለቃ ሥልጣን የባሕርይ ገንዘቡ እንደሆነ እና ለሥልጣኑም ወሰን ድንበር እንደሌለው ተናግሯል፡፡
===================================
💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒
♥💒ከደቂቀ ነቢያት መካከል አንዱ ሚክያስም በቤተልሔም ስለመወለዱ፡-💒♥

✅♥የኤፍራታ ምድር አንቺ ቤተልሔም ከይሁዳ አለቆች ከቶ አታንሽም ሕዝቤን እስራኤልን የሚጠብቅ ንጉሥ ከአንቺ ይወጣልና {{ሚክ.5፥2 ፣ ማቴ.2፥6}} ብሏል፡፡

✅♥ነቢየ እግዚብሔር ቅዱስ ዳዊትም እነሆ በኤፍራታ ሰማነው ዛፍ በበዛበትም ቦታ አገኘነው እንግዲህስ ወደ እግዚአብሔር ማደሪዎች እንገባለን ብሎ የወመለዱን ምሥጢር ተናግሯል {{መዝ.131፥6}}

✅♥ነቢዩ ዕንባቆምም አቤቱ ድምፅህን ሰምቼ ፈራሁ ሥራህንም ዐይቼ አደነቅሁ በሁለት እንስሶች መካከል አየሁህ ዘመኑ እንደደረሰ አድርጌ አውቅህአለሁ ዘመኑም በደረሰ ጊዜ ተገለጥክ ብሎ በቤተልሔም በረት በተወለደ ጊዜ አድግና ላኅም እስትንፋሳቸውን እንደሚገብሩለት {{ዕንባቆም 3፥1}} ተናግሯል፡፡

✅♥ከዚህ በኋላ የዘመኑ ፍጻሜ ሲደርስ እግዚአብሔር መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን ወደ ድንግል ማርያም በመላክ አብሥሯታል፡፡ “ማርያም ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻልና አትፍሪ። እነሆም፥ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፥ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ።እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፥ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል" በማለት፡፡ {{ሉቃ. 1፡32}}

✅♥እመቤታችንም በብዙ ኅብረ አምሳል ትንቢት ሲነገርለት፤ ምሳሌ ሲመሰልለት፤ ሱባኤ ሲቆጠርለት የነበረውን ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በቤተልሔም ግርግም /ዋሻ/ ወለደችው፡፡

✅♥ይህንንም ብስራት በቤተልሔም ዋሻ መንጋቸውን ነቅተውና ተግተው ይጠብቁ ለነበሩ እረኞች መጋቤ ሐዲስ አብሣሬ ትስብዕት ቅዱስ ገብርኤል ፤ እነሆ ዛሬ መድኀኒት በዳዊት ከተማ ተወልዶላችኋል ይኸውም ቡሩክ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የሚያርቅ በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስ የሚያድል ከዓለም በፊት ንጉሥ የነበረ ዛሬም ከዳዊት ባሕርይ /ዘር/ በቤተልሔም ዋሻ ዓለምን ለማዳን የተወለደ የዳዊት ልጅ ንጉሠ ነገሥት ኢየሱስ ክርስቶስ ተወለደ ሲል አበሰራቸው፡፡ {{መዝ.73፥12}}
===================================
💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒

♥💒የጌታችንን ልደት ስናነሣ ሁለት ልደታት እንዳሉት እናምናለን፡፡ እኒሁም ልደታት /ልደት ቀደሚዊና/ /ልደት ደኃራዊ/ ናቸው፡፡💒♥

✅♥ ፡ ቅድመ ዓለም ከአብ አካል ዘእም አካል ባሕርይ ዘእም ባሕርይ ከእግዚአብሔር አብ ያለ እናት የተወለደው ልደት ሲሆን /ነቢዩ ዳዊት እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ ወለድኩከ እምከርሥ እምቅድመ ኮከበ ጽ ባህ {{መዝ.109፥3}} ከአጥቢያ ኮከብ አስቀድሞ ወለድኩህ ፤አንተ ልጄ ነህ እኔም ዛሬ ወለድኩህ {{መዝ.2፥7
}}

✅♥ልደት ደኃራዊ ፤ አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈፀም በሀሙስ ዕለት ወበመንፈቃ ለዕለት እትወለድ እምወለተ ወለትከ እንዲል ቃሉ፡፡ ቅድስት ድንግል ከምትሆን ከእመቤታችን እንበለ ዘርዓ ብዕሲ ያለ አባት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተልሔም የተወለደው ልደት ነው፡፡

✅♥ቀዳማዊ ልደቱ ጥንትና ፍጻሜ የሌለው የማይመረመር ስለሆነ ቀዳማዊ ልደቱን ለመግለፅ ቅድመ ዓለም ያለ እናት ከአብ እንደ ተወለደ ድኅረ ዓለምም ከእመቤታችን /እንበለ ዘርዓ ብዕሲ/ ያለ አባት ተወለደ፡፡ እሱም እመቤታችን ያለ አባት የወለደችው ፤ እግዚአብሔርም ያለ እናት የወለደው ወልድ ዋሕድ ኢየሱስ ክርስቶስ
===================================
💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒💐💒

♥💒በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ሰባቱ መስተጻርራን /ተቃራኒ ነገሮች አንድ ሆነዋል💒♥

✅♥ሕዝብና አሕዛብ፤ በጠብና በክርክር ይፈላለጉ የነበሩ ሕዝብና አሕዛብ በጌታችን ልደት ታርቀዋል፡፡ ይኸውም ሊታወቅ ከዚህ አስቀድሞ ቤተ መቅደሱን ለማፍረስ ንዋየ ቅድሳቱን ለመዝረፍ ሕዝቡን ለመማረክ ምታ ነገሪት ብለው ይመጡ የነበሩ የሩቅ ምስራቅ /የፋርስ የባቢሎን ሰዎች በጌታችን ልደት ምክንያት ወርቅ፣ ዕጣን፣ ከርቤ አይቴ ሀሎ ዘተወልደ ንጉሠ አይሁድ የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው ማቴ.2፥4 እያሉ መጥተው ወርቅ፣ እጣን፣ ከርቤ ገብረውለታል፡፡
✅♥ ፡- በሲዖልና በመቃብር ተለያይተው የነበሩ ነፍስና ሥጋ ከእመቤታችን ከነፍሷ ነፍስ ከሥጋዋ ሥጋ ነሥቶ በተዋሕዶ ሰው በሆነ ጊዜ ነፍስና ሥጋን አስታርቋል፡
✅♥ ፡- አባታችን አዳም አትብላ የተባለውን ዕፀ በለስ በልቶ የሰውና የእግዚአብሔር የፍቅር ግንኙነት ለአምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ተቋርጦ ነበርና ጌታችን የሰውን ሥጋ ተዋሕዶ በተወለደ ጊዜ እርቀ ሰላም ተገኝቷል፡
✅♥ ፡- አባታችን አዳም ከእግዚአብሔር ጋር በተጣላ ጊዜ ቅዱሳን መላእክትም ስለተጣሉት በምትገለባበጥ ሰይፈ እሳት አስፈራርተው ከገነት ከአስወጡት በኋላ ወደ ገነትም እንዳይገባ ገነትን ይጠብቁ ነበር፡፡ ጌታችን በተወለደ ጊዜ አንድ ሆነው ዝማሬ አቅርበዋል፡፡ ይኸውም ዮም አሐደ መርኤተ ኮኑ መላእክት ወሰብእ ከመ ይሰብህዎ ለክርስቶስ እንዲል፡፡ ሰውና መላእክት ክርስቶስን ለማመስገን አንድ ሆኑ እንዳለ ሊቁ፡
✅♥ ፤ ጌታችን የተወለደባት እና ሰባቱ መስተጻርራን አንድ የሆኑባት፤ ሰውና መላእክት የዘመሩባት የብርሃን ጎርፍ የጎረፈባት እንስሳት እስትንፋሳቸውን የገበሩባት ቤተልሔም በቤተ ክርስቲያን ትመሰላለች፡፡

✅♥ #ቤተልሔም፡- ተለያይተው የነበሩ ሕዝብና አሕዛብ ፤ሰውና እግዚአብሔር፤ ነፍስና ሥጋ ፤ሰውና መላእክት አንድ ሆነው በቤተልሔም እንደዘመሩ ዛሬም የፍቅር ተምሳሌትና የአማኞች ሁሉ እናት በሆነችው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በዘር፣ በጎሣ፣ በጥቅም፣ በሥልጣን ሳንከፋፈል አንዲት ቤተ ክርስቲያንን በፍቅር እንድናገለግል በቤተልሔም የተደረገው የልደቱ ምሥጢር ይህን ያስተምረናል፡፡

💐💒ክርስቲያኖች የጌታን መወለድ የምናስበው በዚህ መንፈስ ነው።💐💒💕
==================================

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ልሳነ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ/yetwahdo page posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ልሳነ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ/yetwahdo page:

Share