04/11/2025
አሳዛኝ ዜና እና ጥሪ ለፍትህ!
ተወዳጁ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ በኦሮሚያ ክልል በአርሲ በተለይም ገጠራማ አካባቢዎች በኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ላይ እየደረሰ ያለውን ተደጋጋሚ ግድያና ስጋት በተመለከተ ጠንካራ መልዕክት አስተላልፏል።
በመልእክቱም
"ይኼንን ጽሑፍ ቁጭ ብለህ እያነበብህ ያለኸው በዚህ ሰዓት ምሥራቅ አርሲ ገጠር ውስጥ ስላልተገኘህ ብቻ ነው:: በዚህች ቅጽበት በሥጋት ውስጥ ሆነው "ከአሁን አሁን ምን ይመጣብን ይሆን?" እያሉ ያሉ የኦሮሚያ ምእመናን ቁጥራቸው ብዙ ነው::"
ከቀናት በፊት የተገደሉትን እየተናገርን ሳለ አሁን ደግሞ ሌላ ቦታ አምስት ሰዎች እንደተገደሉ እየሰማን ነው ብሏል።
ከሰይፍ ልጅዋን ማስጣል ያልቻለች የአርሲዋን እናትስ እንዴት ዝም እንበላት? ይህንን የማያቆም ሞት ዜና ሰምተን ወደ ጉሮሮአችን የሚወርድ ምግብና መጠጥ የምንተኛውም እንቅልፍ የለም::
የእነርሱ ሞት የእኛ ሞት ነው:: የእነርሱ መቁሰል የእኛ ቁስል ነው::" በማለት የችግሩን አስከፊነት ገልጿል።
1. ምሕላ እንዲታወጅ፣
ለተሠዉት ተገቢው ክብር እና ጸሎተ ፍትሐት እንዲደረግላቸው ጠይቋል።
2. ቤተ ክርስቲያን በአስተዳደራዊ መዋቅሯ መንግሥት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድ በሙሉ ትኩረት እንድትሠራበት ጊዜው አሁን መሆኑን አሳስቧል።
3. ቅዱስ ሲኖዶስ በዚህ ዓይነት ጊዜ የሚያሳየው ምላሽ ከሌለ... ቤተ ክርስቲያን አልባ ክርስቲያን በራሱ ላይ ይፈጥራል::" በማለት የኃላፊነት ስሜት እንዲሰማው አሳስቧል።
ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ይህን ጊዜ ለመካሰስ፣ አባቶችን ለመሳደብ፣ አንዱ ሌላውን ለማስጠቆርና ለመናቆር ሳይሆን፦
* ለጸሎት፣
* ለምሕላ፣
* ለሰብአዊ ሥራ፣ እና
* ችግሮችን የሚፈቱ ዘላቂ መፍትሔዎች ላይ በትብብር ለመሥራት ምክንያት እንዲያደርጉት ጥሪ አቅርቧል።
ጉዳዩን "በኦርቶዶክሳውያን ላይ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያውያን ላይ የተቃጣ ጥቃት" ብለው ያወገዙ የሌላ እምነት ተከታዮችን አክብሯል።
በክፉ ቀን ክፋታቸውን ላሳዩ ደግሞ "ለሰማያዊው ዳኛ ሠጥተናቸዋል::" ብሏል።
Via ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ