Excellence Life Faith Church

Excellence Life Faith Church Excellence Life Faith Church

The vision of ELFC is to proclaim to all people the redemptive work accomplished by Jesus Christ, making known His love, sacrifice, and saving grace to every nation and generation.

እሁድ ሚያዝያ.25.2018 ዓ.ም ከሰዓት ከ11:00 ጀምሮ በExcellence Life Faith Church / ቻይና ካምፕ አጥቢያ ለተከታታይ እሁዶች "የመጨመር መንፈስ" በሚል ርዕስ የተዘጋጀ...
01/05/2026

እሁድ ሚያዝያ.25.2018 ዓ.ም ከሰዓት ከ11:00 ጀምሮ በExcellence Life Faith Church / ቻይና ካምፕ አጥቢያ ለተከታታይ እሁዶች "የመጨመር መንፈስ" በሚል ርዕስ የተዘጋጀው መንፈሳዊ ኮንፍራንስ ሁለተኛ ቀን ስለሚሆን እርስዎም በቤተክርስቲያናችን በመገኘት አብረውን እንዲካፈሉ በክብር ጋብዘንዎታል።

:-መፅሀፍ ቅዱስ እና አጀንዳዎትን መያዝ አይዘንጉ!!

አድራሻ :- አየር ጤና,ቻይና ካምፕ ከድልድዩ 100m ወረድ ብሎ በሚገኘው የመጀመሪያ ህንፃ ላይ ወደ ሚካኤል በሚወስደው አቅጣጫ በስተግራ በኩል

እሁድ ሚያዝያ.25.2018 ዓ.ም በEXCELLENCE LIFE FAITH CHURCH/HOUSE OF FAITH/ አጥቢያ ከእግዚአብሔር ቃል የምንማርበት እንዲሁም በአምልኮአችን አምላካችንን ከፍ የም...
30/04/2026

እሁድ ሚያዝያ.25.2018 ዓ.ም በEXCELLENCE LIFE FAITH CHURCH/HOUSE OF FAITH/ አጥቢያ ከእግዚአብሔር ቃል የምንማርበት እንዲሁም በአምልኮአችን አምላካችንን ከፍ የምናደርግበት ጊዜ ስለሚኖረን ከጠዋት 3:00 ሰዓት ጀምሮ በቤተክርስቲያናችን በመገኘት አብረዉን እንዲያመልኩና እንዲማሩ በክብር ጋብዘንዎታል

:-መፅሀፍ ቅዱስ እና አጀንዳዎትን መያዝ አይዘንጉ!!

አድራሻ :- ጀሞ ሚካኤል መብራቱን ተሻግረው ወደ ጀሞ በሚወስደው መንገድ 100 ሜትር እንደተጓዙ ብርሀን ባንክ ያለበት ህንፃ 3ኛ ፎቅ ላይ ያገኙናል

ልዩ የወጣቶች ፕሮግራም በEXCELLENCE LIFE FAITH CHURCH /THE HOUSE OF FAITH/ አጥቢያ ከፊታችን ባለው ቅዳሜ ሚያዝያ.24 ከ10:30 ጀምሮ ለወጣቶች የተዘጋጀ የትምህ...
29/04/2026

ልዩ የወጣቶች ፕሮግራም በEXCELLENCE LIFE FAITH CHURCH /THE HOUSE OF FAITH/ አጥቢያ
ከፊታችን ባለው ቅዳሜ ሚያዝያ.24 ከ10:30 ጀምሮ ለወጣቶች የተዘጋጀ የትምህርትና የአምልኮ ጊዜ ስለሚኖረን ሁላችሁም በቤተክርስቲያናችን በመገኘት አብራችሁን እንድታመልኩና እንድትማሩ በክብር ተጋብዛችዃል

:-መፅሀፍ ቅዱስ እና አጀንዳዎትን መያዝ አይዘንጉ!!

አድራሻ :- ጀሞ ሚካኤል መብራቱን ተሻግረው ወደ ጀሞ በሚወስደው መንገድ 100 ሜትር እንደተጓዙ ብርሀን ባንክ ያለበት ህንፃ 3ኛ ፎቅ ላይ

ከእግዚአብሔር ፍቅር የተነሳ ከእርግማን ነፃ ወጥተናል እኛ አማኞች ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ስንቀበልና ዳግመኛ ስንወለድ ቀድሞ ከነበርንበትና ከምንተዳደርበት መንግስት ወጥተን ወደ አዲሱ የእግዚ...
27/04/2026

ከእግዚአብሔር ፍቅር የተነሳ
ከእርግማን ነፃ ወጥተናል

እኛ አማኞች ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ስንቀበልና ዳግመኛ ስንወለድ ቀድሞ ከነበርንበትና ከምንተዳደርበት መንግስት ወጥተን ወደ አዲሱ የእግዚአብሔር መንግስት ገብተናል።

ቆላስይስ 1:13-14
13 እርሱ ከጨለማ አገዛዝ ታደገን፤ ወደሚወድደው ልጁ መንግሥትም አሻገረን፤
14 በእርሱም መዋጀትን በደሙ አግኝተናል፤ ይህም የኀጢአት ይቅርታ ነው።

ስለዚህ ከገባንበት መንግስት የተነሳ የምንኖረውም የህይወት አኗኗር ተቀይሯል።
ቀድሞ በጨለማ፣ሀዘን፣ውድቀት፣ለቅሶና፣ዕርግማን ውስጥ ነበርን አሁን ግን በብርሃን፣በደስታ፣ሰላምና፣በበረከት ውስጥ ነን።
የመንግስቱ ዋና መተዳደሪያ ደግሞ ፍቅር ይባላል።

ታዲያ ከእነዚህ ነገሮች መካከል አንዱ የሆነው ዕርግማን በሰዎች አዕምሮ ላይ ተቀምጦ በአንደበታቸው ሲገልጡት ይታያል..

ወደ ሰው ልጅ ህይወት እርግማን በሁለት መንገዶች ነው የመጣው
1 በሀጥያት ምክንያት /ዘፍ 3:17/
የሰው ልጅ ሀጥያትን ሲያደርግ የመጣበት ውጤት ነው።

2 በህግ ምክንያት /ዘዳ 28:15/
ህጉን ባለመጠበቁ የሚመጣበት ውጤት ነው።

ለዚህ ነው መፅሐፍ ቅዱሳችን እንደዚህ ብሎ የነገረን
ገላትያ 3:13
13 “በዕንጨት ላይ የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው” ተብሎ ስለ ተጻፈ፣ ክርስቶስ ስለ እኛ ርግማን ሆኖ ከሕግ ርግማን ዋጅቶናል፤


መዋጀት ማለት አንድን ነገር ቀድሞ ወደነበረበት ስፍራ መመለስ ማለት ነው።
በሀጥያት ምክንያት ያጣነውን ህይወትና በውስጡም ያሉ ነገሮችን በሙሉ ክርስቶስ ኢየሱስ በሞቱ መልሶልናል።

ይኼም ማለት አሁን በአዲሱ ኪዳን ፀጋ ለእኛ ተሰጠንና እኛ በምናሳየው ጥሩ ፀባይና ባህሪ ወይም በማድረጋችንንና በመስራታችን ሳይሆን
እርሱ በሰራው ስራ ህይወት ተሰጥቶናል።

ፊተኛው አዳም ጥረን ግረን የምንበላበትን ዶማ አወረሰን
ሁለተኛው አዳም/ኢየሱስ/ በበረከት የምንኖርበትን የእግዚአብሔር ኪዳን ሰጠን

አማኝ የሚባረከው የእግዚአብሔርን ኪዳን በመያዝ እንጂ በጥረትና ግረት አይደለም።
ለዚህ ደግሞ ጥሩ ምሳሌያችን
ይስሀቅ በድርቁ ዘመን ዘርን ዘርቶ መቶ እጥፍ ማጨዱ ፤ ጉድጓድ የህይወት አንዱ ክፍል በሆነበት ምድረበዳ ሲወስዱበት እየሰጣቸው መቀጠሉ ነው።

ስለዚህ አማኝ እኔ የተባረኩ ነኝ ወይም ከመርገም ነፃ ነኝ ሲል የሚባርከኝ አምላክ አለኝ እያለ ነው።

እርግማን ማለት የእግዚአብሔርን የበረከት ጉልበት ማጣት ከበረከቱም መጉደል ማለት ነው።
በረከት ማለት ደግሞ በማንነታችን በስራችን ልንከናወን የምንችልበትን የእግዚአብሔር ጉልበት ማግኘት ማለት ነው።

ዘዳግም 8:17-18
17 ምናልባትም፣ “ይህን ሀብት ያፈራሁት በጕልበቴና በእጄ ብርታት ነው” ብለህ በልብህ ታስብ ይሆናል።
18 ነገር ግን ሀብት እንድታፈራ ችሎታ የሰጠህ፣ ለአባቶችህም በመሐላ የገባውን ኪዳን ያጸናልህ እርሱ ስለሆነ፣ አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) ዐስበው።

በዚህ ሁሉ አንድ ነገር ማስተዋል አለብን እርሱም
በረከት የሚጀምረው ከኪዳን እንደሆነና የሚገለጠውም በምንናገረው ቃል ላይ ተመስርቶ እንደሆነ ነው።

እንኳን አስበንና ተረድተነው እንደቀልድ እንኳን የምንናገረው ቃል በህይወታችን ላይ መገለጡ የማይቀር ነው።

በተመሳሳይ ዲያቢሎስም በተለያዩ ሰዎች በመጠቀም ንግርቶችን ወደ እኛ ህይወት ያመጣና ሰምተን በልባችን ካስቀመጥነው ህይወታችንን ያበላሸዋል።

ለእኛ ደግሞ ህይወት በራሱ በጣም ትርጉም ያለው ነገር ስለሆነ ከሚያበረቱን ወደፊት ቀጥል ከሚሉንና ቀናና መልካም ነገር ከሚያስቡልን ሰዎች ጋር ህብረት እናደርጋለን
ሌሎቹን ግን እንወዳቸዋለን እንጂ ከእነርሱም ጋር ህብረት አናደርግም።

ሮሜ 3:13-14
13 “ጕረሯቸው የተከፈተ መቃብር ነው፤
አንደበታቸው ሽንገላን ያዘወትራል።”
“በከንፈሮቻቸው የእባብ መርዝ አለ።”
14 “አፋቸው ርግማንና ምሬት ሞልቶበታል።”

ስለዚህ አማኝ በማንኛውም ሁኔታና ቦታ መልካም የሆነውን የእግዚአብሔር ሀሳብ ሰዎችንም ሊጠቅም የሚችል ነገር ነው መናገርም ማስተላለፍም ያለበት።

ዘፍጥረት 27:27
27 ያዕቆብም ቀርቦ ሳመው፤ ይስሐቅ የያዕቆብን ልብስ ካሸተተ በኋላ እንዲህ ብሎ መረቀው፤
“እነሆ፤ የልጄ ጠረን፣
እግዚአብሔር (ያህዌ) እንደ ባረከው፣
እንደ መስክ መዐዛ ነው።

በመጨረሻም እግዚአብሔር የጠራን ለበረከት እንደሆነ በመረዳት አሁን ያለንበት መንግስትም የበረከት እንደሆነ በማወቅ መልካም የሆነውን ህይወት እንኑር።
አንደበታችንንም ክፉ ከመናገር በመከልከል ቀጣዩን ጉዟችንን እናሳምር

1 ጴጥሮስ 3:9
9 ክፉን በክፉ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ፤ በዚህ ፈንታ ባርኩ፤ ምክንያቱም እናንተ የተጠራችሁት እንደነዚህ ያሉትን ነገሮች እያደረጋችሁ በረከትን ለመውረስ ነው።


ፓስተር ካሴ ከበደ
እሁድ.ሚያዝያ.18.2018
የመለኮታዊ ሞገስ አመታችን ነው

ዛሬ እሁድ ሚያዝያ.18.2018 ዓ.ም ከሰዓት ከ11:00 ጀምሮ በExcellence Life Faith Church / ቻይና ካምፕ አጥቢያ ለተከታታይ እሁዶች "የመጨመር መንፈስ" በሚል ርዕስ የተ...
26/04/2026

ዛሬ እሁድ ሚያዝያ.18.2018 ዓ.ም ከሰዓት ከ11:00 ጀምሮ በExcellence Life Faith Church / ቻይና ካምፕ አጥቢያ ለተከታታይ እሁዶች "የመጨመር መንፈስ" በሚል ርዕስ የተዘጋጀው መንፈሳዊ ኮንፍራንስ የመጀመሪያ ቀን ስለሚሆን እርስዎም በቤተክርስቲያናችን በመገኘት አብረውን እንዲካፈሉ በክብር ጋብዘንዎታል።

:-መፅሀፍ ቅዱስ እና አጀንዳዎትን መያዝ አይዘንጉ!!

አድራሻ :- አየር ጤና,ቻይና ካምፕ ከድልድዩ 100m ወረድ ብሎ በሚገኘው የመጀመሪያ ህንፃ ላይ ወደ ሚካኤል በሚወስደው አቅጣጫ በስተግራ በኩል

እሁድ ሚያዝያ.18.2018 ዓ.ም በEXCELLENCE LIFE FAITH CHURCH/HOUSE OF FAITH/ አጥቢያ ከእግዚአብሔር ቃል የምንማርበት እንዲሁም በአምልኮአችን አምላካችንን ከፍ የም...
25/04/2026

እሁድ ሚያዝያ.18.2018 ዓ.ም በEXCELLENCE LIFE FAITH CHURCH/HOUSE OF FAITH/ አጥቢያ ከእግዚአብሔር ቃል የምንማርበት እንዲሁም በአምልኮአችን አምላካችንን ከፍ የምናደርግበት ጊዜ ስለሚኖረን ከጠዋት 3:00 ሰዓት ጀምሮ በቤተክርስቲያናችን በመገኘት አብረዉን እንዲያመልኩና እንዲማሩ በክብር ጋብዘንዎታል

:-መፅሀፍ ቅዱስ እና አጀንዳዎትን መያዝ አይዘንጉ!!

አድራሻ :- ጀሞ ሚካኤል መብራቱን ተሻግረው ወደ ጀሞ በሚወስደው መንገድ 100 ሜትር እንደተጓዙ ብርሀን ባንክ ያለበት ህንፃ 3ኛ ፎቅ ላይ ያገኙናል

የአዲስ ኪዳን ትምህርት አራተኛ ቀን  የአዲስ ኪዳን ትምህርት ብለን ለብቻው መማር ለምን አስፈለገ ካልን  በአዲሱ ኪዳን አማኞች በክርስቶስ ኢየሱስ የተደረገላቸውን ነገር በማወቅ የሚመላለሱበት...
24/04/2026

የአዲስ ኪዳን ትምህርት አራተኛ ቀን

የአዲስ ኪዳን ትምህርት ብለን ለብቻው መማር ለምን አስፈለገ ካልን

በአዲሱ ኪዳን አማኞች በክርስቶስ ኢየሱስ የተደረገላቸውን ነገር በማወቅ የሚመላለሱበትን እውቀት ለመስጠት ነው።
ምክንያቱም የሁለቱ ኪዳናት አሰራር በፍፁም የተለያየ ነው።

#ብሉይ ኪዳን በህግ በተስፋ በኩነኔና በሰዎች ታሪክ ላይ የተመሰረተ አገልግሎት ነው።
#አዲስ ኪዳን ግን የፀጋ የእምነትና የፅድቅ አገልግሎት ነው።

በብሉይ ኪዳን አገልግሎት
#ካህናት /በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያሉ ሰዎች/ የሌዊ ዘሮች ሲሆኑ / ዘፀ 28:1 ዘሁ 18:7 2ዜና 19:11/
በአዲስ ኪዳን ግን አማኞች ሁሉ በክርስቶስ ኢየሱስ አምነው ዳግመኛ ሲወለዱ ካህናት ተደርገዋል። /ዮሐ ራዕ 1:5/

1 ጴጥሮስ 2:9
9 እናንተ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የጠራችሁን የእርሱን በጎነት እንድትናገሩ የተመረጠ ትውልድ፥ የንጉሥ ካህናት፥ ቅዱስ ሕዝብ፥ ለርስቱ የተለየ ወገን ናችሁ፤


ነገር ግን አንድ መርሳት የሌለብን ነገር ካህናት የሆንነው የማያምኑ ሰዎችን ከእግዚአብሔር ጋር ለማገናኘት እንጂ አማኞችን ለማገናኘት አለመሆኑን ነው።
አማኞች አንድ ጊዜ በሞተላቸውና ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ደሙን ይዞ በገባው በክርስቶስ ኢየሱስ በኩል ከእግዚአብሔር ጋር ታርቀዋል በቀጥታም እርሱን ማግኘት ይችላሉ።

#አማኞች ሁሉ ካህናት ሆነዋል ሌላ ካህንም አያስፈልጋቸውም!!

ሌላው ደግሞ በብሉይ ኪዳን የነበረው የነቢያት አገልግሎት ሲሆን
በጊዜው ሰዎቹ በሀጥያት ውስጥ ስለሚኖሩና በቀጥታ ከእግዚአብሔር ጋር መገናኘት ስለማይችሉ እግዚአብሔር እራሱ ሰዎችን ለራሱ በመለየት መልዕክቶችን ያስተላልፍ ነበር

ከፃፉት የመፅሐፍ መጠን በመነሳትም Major እና Minor በማለት ተከፍለው ይጠራሉ።

ነገር ግን በአዲስ ኪዳን አማኞች ሁሉ እንዲሰሙትም ሆነ እንዲመሩበት የተሰጣቸው መንፈስ ቅዱስ ነው።
መንፈስ ቅዱስ ደግሞ አኛ ለመመራት ዝግጁ በሆንን ቁጥር ሁልጊዜ ይመራናል።

ሮሜ 8:14-15
14 በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ ሁሉ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና።
15 አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና።

የመጨረሻው ደግሞ የነገስታት አገልግሎት ሲሆን
በአዲሱ ኪዳንም ንግስና ለአማኞች ሁሉ የተሰጠ ስልጣን ነው።

ራእይ 5:9-10
9-10 “መጽሐፉን ትወስድ ዘንድ ማኅተሞቹንም ትፈታ ዘንድ ይገባሃል፥ ታርደሃልና፥ª በደምህም ለእግዚአብሔር ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ዋጅተህ ለአምላካችን መንግሥትና ካህናት ይሆኑ ዘንድ አደረግሃቸው፥ በምድርም ላይ ይነግሣሉ፡” እያሉ አዲስን ቅኔ ይዘምራሉ።


ንግስና ማለት በጠላት ሀይል ሁሉ ላይ ገዢ መሆን ማለት ነው። እርሱም በጨለማው አለም ሀይላትና ስልጣናት ላይ እንጂ በሰዎች ላይ አይደለም።

ስለዚህ እኛ አማኞች እንደ ንጉስ በዚህ ምድር ላይ መንቀሳቀስ አለብን።
ንጉስ ደግሞ ያዝዛል እንጂ አይለምንም።
እኛም የምንፈልገውን ነገር በማዘዝ ወደ ህይወታችን እንገልጠዋለን እንጂ የምንለምነው ነገር የለም።

ፓስተር ካሴ ከበደ
ሐሙስ.ሚያዝያ.15.2018
የመለኮታዊ ሞገስ አመታችን ነው

Address

Ayertena, China Camp 50m Away From The Bridge On The First Building
Addis Ababa

Telephone

+251911645877

Website

https://t.me/ExcellenceLifeFaithChurch, https://www.tiktok.com

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Excellence Life Faith Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share