Qusequwam Maryam ቁስቋም ማርያም እናቴ

Qusequwam Maryam ቁስቋም ማርያም እናቴ our business is created a great relationship with the community and serving people. first God

ግዕዝን በቀላሉ ይማሩ
14/11/2025

ግዕዝን በቀላሉ ይማሩ

"እግዚአብሔር ለእኛ መልካም የሚያደርግልን በጎ ነው ብለን በምናስበው ነገር ብቻ አይደለም። እጅግም ክፉና አስቸጋሪ መስለው ከሚታዩን ኹኔታዎችም ለእኛ ለልጆቹ እጅግ የሚደንቅ በጎ ነገ....

09/05/2025

በዛሬው ቀን በአለም ላይ ድንቅ ነገር ተከስቶ ነበር። 😘እንኳን ደስ አላቹህ።
እርሱም እመቤታችን የመወለዷ ድንቅ ዜና ነበር።
ግንቦት ልደታ😍

"ቅዳም ስዑር"ክርስቲያኖች ቅዳሜ ጠዋት በቤተ ክርስቲያን ተሰባስበው ጸሎቱ ሲፈጸም “ገብረ ሰላመ በመስቀሉ- ክርስቶስ በመስቀሉ ሰላምን መሠረተ፤ ሰላምን ፈጠረ፤ የምሥራች” ይባባላሉ፡፡ ለተሰበ...
19/04/2025

"ቅዳም ስዑር"
ክርስቲያኖች ቅዳሜ ጠዋት በቤተ ክርስቲያን ተሰባስበው ጸሎቱ ሲፈጸም “ገብረ ሰላመ በመስቀሉ- ክርስቶስ በመስቀሉ ሰላምን መሠረተ፤ ሰላምን ፈጠረ፤ የምሥራች” ይባባላሉ፡፡ ለተሰበሰበ ሁሉ የምሥራች ምልክት የሚሆን ቄጤማ ይታደላል፡፡ ምእመናንም ይህን እየሰነጠቁ በራሳቸው ያስሩታል፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያን ላልመጡት ደግሞ ካህናት በየበኩላቸው ልብሰ ተክኅኗቸውን ለብሰው መስቀልና ቃጭል ይዘው ቄጤማውን “የምሥራች” እያሉ ይሰጣሉ፡፡
ቄጤማው የምሥራች ምልክት መሆኑ ከታሪክ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ዓለም በንፍር ውሃ በተጥለቀለቀች ጊዜ ኖኅ ርግብን የውሃውን ሁኔታ ለመረዳት በመስኮት አሾልኮ ወደ ምድር ይልካታል፡፡ እርሷም በአፏ ቄጤማ ይዛለት መጥታለች፡፡ ኖኅ የውሃውን መጉደል በቄጤማው ተረድቶ ተደሰተ፡፡ መርከቢቱንም ለማሳረፍ ተዘጋጀ፡፡ ቄጤማው ለውሃው መጉደል ለኖኅ የምሥራች እንደሆነለት አሁንም ክርስቶስ የኃጢአትን ውሃ እንደደመሰሰው ለማስገንዘብ ምእመናን ቄጤማ አስረው፣ ቄጤማ ይዘው ይታያሉ፡፡ የምሥራች ይባባላሉ፡፡
ይህች ቅዳሜ የተለያዩ ስያሜዎች አሏት፡፡ አንደኛው “ሰንበት ዓባይ” የሚል ነው፡፡ ይኸውም የፊተኛይቱ ቅዳሜ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ፈጥሮ ከሥራው ያረፈባት ዕለት ስትኾን ይህቺ ግን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሦስት ዓመት ከሦስት ወር የማዳን ሥራውን በመስቀል ፈጽሞ በከርሠ መቃብር ዐርፎ የዋለባት ዕለት ስለሆነች ነው፡፡ ዳግመኛም ይህቺ ዕለት “ስዑር ቅዳሜ” ትባላለች፡፡ ስዑር መባሏም በዓመት አንድ ቀን ብቻ ስለምትጾም የተሻረች ቅዳሜ ማለት ነው፡፡
በመስቀሉ ደም ሰላም አድርጎ በምድር ወይም በሰማያት ያሉትን ሁሉ ለራሱ እንዲያስታርቅ ለፈቀደ ለሰላም አለቃ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ክብር የክብር ክብር ለእርሱ ይሁን አሜን::
በዚሁ ዕለት ቀሳውስቱና ዲያቆናቱ ቃጭል /ቃለ ዓዋዲ/ እየመቱ ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሳኤሁ አግሃደ የሚለውን ያሬዳዊ ዜማ በመዘመር ጌታ በመስቀሉ ሰላም እንደሰጠን እና ትንሳኤውንም እንደገለጠልን በማብሰር ቄጤማውን ለምእመናን ይሰጣሉ፡፡ ምእመናኑም ገጸ በረከት ያቀርባሉ፤ ቄጤማውንም በራሳቸው ያስራሉ፡፡ አንድም የምዕመናኑ በእራሳቸው ላይ ቄጠማ ማሰር አይሁድ ጌታችንን እያሰቃዩ ሊሰቅሉት ባሉ ጊዜ የእሾህ አክሊል ጭንቅላቱ ላይ ያሰሩበትን ድርጊት የሚያስታውስ ነው፡፡ በዚህ ዕለት ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ካህናትና ዲያቆናት ቄጤማ ተሸክመው፤ ቃጭል ሲያቃጭሉ መታየታቸው ዕለተ ትንሳኤውን ለሚናፍቁ ምእመናን ትልቅ ብሥራት ነው፡፡
ምንጭ፡- ስምዐ ተዋሕዶ፤ (ዘማኅበረ ቅዱሳን)

18/04/2025
05/04/2025
31/03/2025

ኃይልህ ሲገለፅ በሰማይ

እንኳን ለአብይ ፆም አደረሰን
21/02/2025

እንኳን ለአብይ ፆም አደረሰን

ሰብስክራይብ ላይክ ያድርጉ ለተጨማሪ መዝሙሮችን ከነግጥማቸው,ስብከተ ወንጌሎች /, ትምህርቶችን ለመስማት ይህንን ይጫኑ mezmur with lyrics https://www.youtube.com/channel/UCrsmJFP219un5mCk7mLfEfA/videos...

 ...1. በሁሉ ማመስገን:- "የምስጋና ሕይወት ትህትና የሚበቅልበት ለም አፈር ነው።"2. የመታዘዝ ሕይወት:-  መታዘዝ የሚፈልጉትን ማድረግ አይደለም የማንፈልገውንና የማንወደውን ማድረግ እ...
06/02/2025

...

1. በሁሉ ማመስገን:- "የምስጋና ሕይወት ትህትና የሚበቅልበት ለም አፈር ነው።"

2. የመታዘዝ ሕይወት:- መታዘዝ የሚፈልጉትን ማድረግ አይደለም የማንፈልገውንና የማንወደውን ማድረግ እንጂ:: ራስን መስጠት እንለማመድ።

3. ሰዎችን እናክብር ፥ ለእውቀታቸው እና ለስብዕናቸው እውቅና እንስጥ፤
ሰዎችን በመተቸት እና በማዋረድ የእኛን ክብር በድብቅ ከፍ ከማድረግ እንቆጠብ።

4. ለሰዎች ምክር እና ሀሳብ ከመስጠት እንቆጠብ፦

በሁሉም ጉዳይ ዘሎ የመምከር እና ሰውን የማቃናት ፍላጎታችንን እንግታ። ከዛ ይልቅ አጠገባችን ባለው እና በሚያወራን ሰው ላይ እናተኩር። በተለይ ሰዎች ችግራቸውን ሲነግሩን የኛ ሀሳብ ልዩ ስለሆነ አድርገን አናስብ። መደመጥ ፈልገው እንደሆነና፣ ብንችል በጸሎታችን እንድናስባቸው ይሁን እንጂ ለመምከር አንፍጠን።

+ጌታ በነገር ሁሉ ትሁት መሆንን ይስጠን!
አሜን !

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Qusequwam Maryam ቁስቋም ማርያም እናቴ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share