ገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም ቤ/ክ መሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • ገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም ቤ/ክ መሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት

ገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም ቤ/ክ መሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ይህ የገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም መሰረተ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ይፋዊ የፌስቡክ ገፅ ነው።

በሰንበት ትምህርት ቤታችን የእቅድ ግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይት ከመደበኛ አባላት ጋር ተደረገ።በሰንበት ት/ቤታችን አዲስ የተመረጠው ስራ አመራር በቀጣይ ሊሰራቸው የሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ጥቆማ ...
02/08/2026

በሰንበት ትምህርት ቤታችን የእቅድ ግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይት ከመደበኛ አባላት ጋር ተደረገ።

በሰንበት ት/ቤታችን አዲስ የተመረጠው ስራ አመራር በቀጣይ ሊሰራቸው የሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ጥቆማ እና ግብዓት ለማሰባሰብ ያለመ ጉባኤ በዛሬው እለት ሐምሌ 26/2018 ዓ.ም በሰ/ት/ቤታችን አዳራሽ አካሂዷል።

በዚህም ለውይይት መነሻ የሚሆኑ ዐበይት ርዕሶች እና የውይይት መነሻ ሃሳቦች ላይ በመመስረት በቀጣይ አመታት ሊሰሩ የሚገባቸው እና ሊታረሙ የሚገባቸው ችግሮች ላይ ውይይት ተደርጓል።

በተለያዩ ቡድኖች በመከፋፈል የተደረጉ ውይይቶች ማጠቃለያዎችም ለጠቅላላ ተሰብሳቢዎች ከቀረቡ በኋላ ያልተነሱ የተባሉ ተጨማሪ ሃሳቦችን ከጉባኤው የማሰባሰብ ሂደት ተከናውኗል።

ከዚህ በኋላ የሰንብት ት/ቤታችን ሊቀመንበርነቱን መ/ር ዘውዱ ኃ/ገብርኤል በሰጡት ማጠቃለያ የተሰጡትን ግብአቶች ወደ እቅድ አውርዶ ለመተግበር እንዲቻል በሐዋርያት ስራ ም 2 ቁ 46 ላይ እንደተመለከቱት የመጀመሪዎቹ ክርስቲያኖች የሚያስፈልግ መሆኑን በመጥቀስ በግብዓቶቹ መሰረት ለሚወጡ እቅዶች ትግበራ አባላት ቀና ትብብራቸውን እንዲያደርጉ በማሳሰብ ጉባኤው ተጠናቋል።

በቀጣይ ሳምንታት መሰል ውይይቶች ከነባር እና ጎልማሳ አባላት እንዲሁም ከማዕከላውያን ክፍል (ታዳጊ) አባላት ጋር የሚቀጥል ይሆናል።

“እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች ዕወቁ በርሷም ላይ ኺዱ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ።” ኤር 6÷...
15/07/2026

“እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች ዕወቁ በርሷም ላይ ኺዱ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ።” ኤር 6÷16

መልካሚቱ መንገድ የተባለች ቅድስት ሃይማኖታችንን የምንማርበት የምናውቅበት የተከታታይ የክረምት ትምህርት (ኮርስ) በሰንበት ትምህርት ቤታችን አዘጋጅነት ከሐምሌ 11/2018 ዓ.ም. ጀምሮ ይሰጣል።

ትምህርቱን ለመከታተል የምትፈልጉ ምስሉ ላይ በተያያዙት ስልክ ቁጥሮች ስልኮች በመደወል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

የእርዳታ ጥሪየመንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን (ሽሮሜዳ) ውሉደ ብርሃን ሰ/ት/ት ቤት አባል የሆነችው መቅደስ መቆያ የደም ካንሰር ህመም አጋጠሟታል። ህክምናው በአጠቃላይ ከአራት ...
15/07/2026

የእርዳታ ጥሪ

የመንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን (ሽሮሜዳ) ውሉደ ብርሃን ሰ/ት/ት ቤት አባል የሆነችው መቅደስ መቆያ የደም ካንሰር ህመም አጋጠሟታል።

ህክምናው በአጠቃላይ ከአራት ሚሊዮን ብር በላይ የሚፈጅ ሲሆን ቤተሰቦቿ ወጪውን ሸፍነው ለማሳከም አልቻሉም።

በመሆኑም እህታችን ተገቢውን የህክምና እርዳታ አግኝታ ወደ አገልግሎት ለመመለስ እንድትችል ሁሉም የሰንበት ት/ት ቤት ተማሪዎች እና ምዕመናን አቅማቸው የፈቀደውን ድጋፍ እንዲያደርጉ የውሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ጠይቋል።

በመሆኑም ሁላችሁም አባላት አቅማችሁ የፈቀደውን እዚህ ደብዳቤው ላይ በተጠቀሰው የሂሳብ ቁጥር ላይ በማስገባት እህታችንን እንድትደግፉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

እህታችንን እግዚአብሔር ይማርልን። አሜን🙏

ሰንበት ት/ቤታችን 41ኛ የክረምት መንፈሳዊ ተከታታይ ትምህርት ለአካባቢው ምዕመናን ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቋል። የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ ወጥነት ባለው ለመማር ፍላጎቱ ላላቸው የአካባቢያ...
06/07/2026

ሰንበት ት/ቤታችን 41ኛ የክረምት መንፈሳዊ ተከታታይ ትምህርት ለአካባቢው ምዕመናን ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቋል። የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ ወጥነት ባለው ለመማር ፍላጎቱ ላላቸው የአካባቢያችን ምዕመናን በሙሉ ክፍት የሆነውን የክረምት ትምህርት ለመማር ፍላጎቱ ያላችሁ እንድትመዘገቡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

«ዕጣውም ለማቲያስ ወደቀ...» (የሐዋ. ሥራ 1፥26)የመሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት አዲሱን የሥራ አመራርና የክትትል ቁጥጥር አባላት በዕጣ ሥርዓት ሰየመ(ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ....
06/07/2026

«ዕጣውም ለማቲያስ ወደቀ...» (የሐዋ. ሥራ 1፥26)

የመሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት አዲሱን የሥራ አመራርና የክትትል ቁጥጥር አባላት በዕጣ ሥርዓት ሰየመ
(ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም.፣ አዲስ አበባ)

በገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም ቤተክርስቲያን የመሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ለቀጣዩ የአገልግሎት ዘመን የሚያገለግሉትን የሥራ አመራርና የክትትል ቁጥጥር አባላት የመምረጥ የዕጣ ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም. በታላቅ መንፈሳዊ ሥርዓትና በተሳካ ሁኔታ ተካሂዷል።

ሥነ-ሥርዓቱ ከመካሄዱ በፊት በሐመረ ኖኅ እንጦጦ ቅድስት ኪዳነምህረት እና በገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም ቤተክርስቲያን ለአንድ ሳምንት የተካሄደው የጸሎተ ዕጣን መርሃ ግብር በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። ይህንን ተከትሎ በተደረገው ታሪካዊና መንፈሳዊ መድረክ በርካታ የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባላት በመገኘት ሂደቱን በጸሎትና በአንድነት ተከታትለዋል።

በመርሃ ግብሩም የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ጸሐፊ ሊቀ ስዩማን አምባዬ፣ የደብሩ ሰበካ ጉባኤ አባልና የስብከተ ወንጌል አገልጋይ መ/ር መለሰ ምህረቴ፣ እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ተወካይ መ/ር ጎይቶም በክብር ተገኝተው አባታዊ ምክርና መንፈሳዊ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የምርጫ አስፈጻሚ ኮሚቴው በሰጠው መግለጫ፣ የዕጣ ሥርዓቱ የሰውን ፍላጎት ሳይሆን የእግዚአብሔርን ፈቃድ በጸሎት የመሻት መንፈሳዊ ሥርዓት መሆኑን ገልጾ፣ ሂደቱም በሙሉ የቤተክርስቲያንን ሥርዓት በጠበቀና በሰላማዊ ሁኔታ መፈጸሙን አረጋግጧል።

በዚሁ መሠረት በዕጣው ለቀጣዩ የአገልግሎት ዘመን የተመረጡት የሥራ አመራር አባላት፦
የሥራ አመራር
፨ መ/ር ዘውዱ ኃ/ገብርኤል
፨ ዲ/ን በረከት አለማየሁ
፨ ዶ/ር ኤርሚያስ ክ/አብ
፨ ዲ/ን ተገኝ በላይ
፨ ዲ/ን ዳግም አዱኛ
፨ ዲ/ን ዶ/ር ናትናኤል ስንታየሁ
፨ ወ/ሮ ገነት ተኩ
፨ ወ/ሮ መቅደስ ኃይሉ
፨ ወጣት ጽዮን ቢራራ
የአፈጻጸም ክትትልና ቁጥጥር
፨ ወ/ሮ ቢታንያ አበበ
፨ አቶ አንተነህ ክንፈ
፨ አቶ ከበደ አዱኛ

ተመራጮቹ በጠቅላላ ጉባኤውና በክቡራን አባቶች ፊት ቀርበው ቅድስት ቤተክርስቲያንንና ሰንበት ትምህርት ቤቱን በታማኝነት፣ በትህትናና በትጋት ለማገልገል ቃለ-መሐላ ፈጽመዋል። አባቶችም በአዲሱ የአገልግሎት ዘመናቸው የእግዚአብሔር ረድኤትና በረከት እንዲበዛላቸው አባታዊ ምክራቸውንና ቡራኬያቸውን ሰጥተዋል።

ከዚያም አዲሱ የሥራ አመራር ለቀጣዩ ሦስት ዓመታት የሚያገለግሉትን ኃላፊዎች በመምረጥ፦
፨ መ/ር ዘውዱ ኃ/ገብርኤል – ሊቀመንበር
፨ ዲ/ን በረከት አለማየሁ – ጸሐፊ

በተመሳሳይ የክትትልና ቁጥጥር ክፍሉ፦
፨ ወ/ሮ ቢታንያ አበበ – ሰብሳቢ
፨ አቶ አንተነህ ክንፈ – ጸሐፊ

ሆነው ተመርጠዋል። እንዲሁም በሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሰንበት ትምህርት ቤቱን የሚወክሉት
፨ ዲ/ን አሸናፊ ተስፋዬ ሆነው ተመርጠዋል።

በመጨረሻም ለአዲሱ የሥራ አመራር አባላት በፍቅር፣ በሰላም፣ በትህትናና በኦርቶዶክሳዊ አንድነት ከመንፈሳዊ አባቶች፣ ከአመራር አባላትና ከመላው የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባላት ጋር ተባብረው እንዲያገለግሉ ጽኑ አደራ ተሰጥቷል።

መርሃ ግብሩ በከፍተኛ መንፈሳዊ ድባብና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። ምርጫ አስፈጻሚው ለመላው የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባላትና ለአዲሱ የተመረጠው አመራር እንኳን ደስ አላችሁ! በመጪው የአገልግሎት ዘመን በብዙ ፍሬ፣ በበረከትና በእግዚአብሔር ጸጋ የተሞላ አገልግሎት እንዲያከናውኑ ከልብ እንመኛለን።

የምርጫ አስፈጻሚ ኮሚቴ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፣ ወለወላዲቱ ድንግል፣ ወለመስቀሉ ክቡር!

"እነሆ የሃይማኖት ፍሬ "      ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ከሁሉ አስቀድመን በነገሮች ሁሉ የረዳችሁን ቅዱስ እግዚአብሔርን እያመሰገንን በቀን 20 እና 21/10/2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርታችሁን...
03/07/2026

"እነሆ የሃይማኖት ፍሬ "
ቅዱስ ዲዮስቆሮስ

ከሁሉ አስቀድመን በነገሮች ሁሉ የረዳችሁን ቅዱስ እግዚአብሔርን እያመሰገንን በቀን 20 እና 21/10/2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርታችሁን አጠናቃችሁ ከአዲስ አበባ እና ኮተቤ ዩኒቨርሲቲዎች የተመረቃችሁት የመሠረተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት ፍሬ የሆናችሁት
ዲ/ን አምሐ ኃይሌ በአካውንቲንግ እና ፋይናንስ ዲግሪ
ኢ/ር ዮሴፍ ወንድሙ በሲቪል ኢንጂነሪንግ ዲግሪ
መ/ር አየናቸው አይናለም በስፖርት ሳይንስ ዲግሪ
ለዚህ ክብር በመብቃችሁ የተሰማንን ደስታ እየገለጽን ሁሉን ያደረገን እግዚአብሔርን ስለእናንተ እናመሠግናለን።

እንኳን ደስ አላችሁ።

በዕለተ ሰንበት ሰኔ 21/2018 ዓ.ም. በደብራችን የተከበረው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም እና የቅድስት ቤተክርስቲያን በዓል የማስታወሻ ምስሎች - 2
30/06/2026

በዕለተ ሰንበት ሰኔ 21/2018 ዓ.ም. በደብራችን የተከበረው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም እና የቅድስት ቤተክርስቲያን በዓል የማስታወሻ ምስሎች - 2

በዕለተ ሰንበት ሰኔ 21/2018 ዓ.ም. በደብራችን የተከበረው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም እና የቅድስት ቤተክርስቲያን በዓል የማስታወሻ ምስሎች - 1
30/06/2026

በዕለተ ሰንበት ሰኔ 21/2018 ዓ.ም. በደብራችን የተከበረው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም እና የቅድስት ቤተክርስቲያን በዓል የማስታወሻ ምስሎች - 1

“ቃልህ ለጉሮሮዬ ጣፋጭ ነው” መዝ 118÷103 ከማር እና ከወተት ይልቅ የሚጣፍጠውን የእግዚአብሔር ቃል ወደ ውስጣችን የሚፈስበት ወርኃዊ የትምህርት መርሐግብራችን ከሰኔ 22/2018 ዓ.ም. ...
24/06/2026

“ቃልህ ለጉሮሮዬ ጣፋጭ ነው” መዝ 118÷103

ከማር እና ከወተት ይልቅ የሚጣፍጠውን የእግዚአብሔር ቃል ወደ ውስጣችን የሚፈስበት ወርኃዊ የትምህርት መርሐግብራችን ከሰኔ 22/2018 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም ድረስ በልዩ ልዩ ተጋባዥ መምህራን ይሰጣል።

የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት እንዲሁም የአካባቢያችን ምዕመናን ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።

24/06/2026

ሰኔ 21 በስሙ የታነጸች ቤተክርስቲያን በዓል

Address

Ferensay Legaseon(41 No. Bus End Station)
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም ቤ/ክ መሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share