ገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም ቤ/ክ መሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • ገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም ቤ/ክ መሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት

ገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም ቤ/ክ መሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ይህ የገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም መሰረተ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ይፋዊ የፌስቡክ ገፅ ነው።

እንኳን አደረሳችሁ ሞት ድል አድርጎ የተነሳው ጌታችን በክብር እና በሥልጣኑ አርጓል።
21/05/2026

እንኳን አደረሳችሁ ሞት ድል አድርጎ የተነሳው ጌታችን በክብር እና በሥልጣኑ አርጓል።

16/05/2026

ዝክረ ቅዱስ ያሬድ እየደረሰ ነው...

ዝክረ ቅዱስ ያሬድየቤተክርስቲያናችን ኩራት ከሆኑ ኢትዮጵያዊ ሊቃውንት ዋነኛው የሆነው የአባታችን የቅዱስ ያሬድ መታሰቢያ ዓመታዊ ልዩ ጉባኤ በሰንበት ቤታችን እና በደብሩ ስብከተ ወንጌል ትብብ...
12/05/2026

ዝክረ ቅዱስ ያሬድ

የቤተክርስቲያናችን ኩራት ከሆኑ ኢትዮጵያዊ ሊቃውንት ዋነኛው የሆነው የአባታችን የቅዱስ ያሬድ መታሰቢያ ዓመታዊ ልዩ ጉባኤ በሰንበት ቤታችን እና በደብሩ ስብከተ ወንጌል ትብብር ተዘጋጅቷል።

መርኃግብሩ የፊታችን ግንቦት 15 ቀን ከቀኑ 10:30 ጀምሮ በደብራችን አውደምህረት የሚካሄድ ይሆናል።

በዚህ መርኃግብር ላይ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።

ልብ ይበሉ ከዚህ በፊት ግንቦት 8 ለማካሄድ ታስቦ የነበረው መርኃግብር ወደ ግንቦት 15 ተዘዋውሯል።

  እንኳን አደረሳችሁ የነቢያት ትንቢትና ምሳሌ፣ የሐዋርያት ሞገሳቸው፣ የሰማዕታት እናታቸው፣ የመላእክትም እኅታቸው፣ በመዓልትና በሌሊት በበሮችዋ ደጅ የሚጠኑ የጐልማሶችና የደናግል የመነኰሳት...
09/05/2026



እንኳን አደረሳችሁ

የነቢያት ትንቢትና ምሳሌ፣ የሐዋርያት ሞገሳቸው፣ የሰማዕታት እናታቸው፣ የመላእክትም እኅታቸው፣ በመዓልትና በሌሊት በበሮችዋ ደጅ የሚጠኑ የጐልማሶችና የደናግል የመነኰሳትም መመኪያቸው የሆነች ድንግል ማርያም ዛሬ ተወለደች።

ሰንበት ትምህርት ቤታችን እንደአምናው ሁሉ ዘንድሮም የእመቤታችንን ልደት በደመቀ ሁኔታ ለማክበር ዝግጅቱን አጠናቋል።

ኑ የእናታችንን ልደት በባለልደቷ ቤት ደጃፍ ከቀኑ 11:00 ጀምሮ እናክብር።

ስለዜማ ቢነሳ የዜማ መሰረት ጀማሪ (መሰረተ ዜማ ወጠነ ወጠነ ያሬድ ካህን እንዲል)ስለ ነገረ ድህነት ሲነገር ቀዳሚው አስተማሪስለ ኪነ ጥበብ የድርሰት ችሎታ ቢነሳ ቀድሞ ተጠሪብሉይን ከሐዲስ ...
08/05/2026

ስለዜማ ቢነሳ የዜማ መሰረት ጀማሪ (መሰረተ ዜማ ወጠነ ወጠነ ያሬድ ካህን እንዲል)
ስለ ነገረ ድህነት ሲነገር ቀዳሚው አስተማሪ
ስለ ኪነ ጥበብ የድርሰት ችሎታ ቢነሳ ቀድሞ ተጠሪ
ብሉይን ከሐዲስ አመስጣሪ የሆነው የቅድስት ቤተክርስቲያናችን አይን ተብሎ የሚጠራው የአባታችን የቅዱስ ያሬድ አመታዊ መታሰቢያ በዓሉ እነሆ ደረሰ።

ሊቁ አባታችን የተወልንን እወቀት ለማጥናት እንድንችል ትጋትን እየለመንንና አምላከ ቅዱስ ያሬድ የእርሱን ክብር (መንግሰተ ሰማያትን እንዲያድለን) እየጸለይን በዕለተ ሰንበት እሁድ ግንቦት 8/2018 ዓ.ም. ልንዘክረው ተዘጋጅተናል።

ተጋባዥ ዘማሪያን እና መመህራን በሚገኙበት በዚህ ልዩ መርኃግብር ላይ እንድትገኙ በኢትዮጵያዊው ቅዱስ አባት ስም ተገብዛችኋል።

 ''እስመ ኵሉ ዘይትለአካ ለእግዝእትነ ድንግል ማርያም ይረክብ ኵሉ ዘሰአለ'''' እመቤታችን ድንግል ማርያምን ያገለገለ የለመነው ሁሉ ይደረግለታል''(ተዓምረ ማርያም)
07/05/2026



''እስመ ኵሉ ዘይትለአካ ለእግዝእትነ ድንግል ማርያም ይረክብ ኵሉ ዘሰአለ''
'' እመቤታችን ድንግል ማርያምን ያገለገለ የለመነው ሁሉ ይደረግለታል''

(ተዓምረ ማርያም)

  ሰንበት ትምህርት ቤታችን እንደ አምናው ሁሉ ዘንድሮም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን   ግንቦት 1 ቀን ከምሽቱ 11:00 ጀምሮ በቤቷ ደጃፍ ለማክበር ተዘጋጅቷል።ልደት የሚከበረው ...
06/05/2026



ሰንበት ትምህርት ቤታችን እንደ አምናው ሁሉ ዘንድሮም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ግንቦት 1 ቀን ከምሽቱ 11:00 ጀምሮ በቤቷ ደጃፍ ለማክበር ተዘጋጅቷል።

ልደት የሚከበረው ባለልደት በሆነው ሰው ቤት ነውና ኑ በቤቷ አባት እናቶቻችን እንዳስተማሩን አድርገን ልደቷን እናክብር

" ከመተሰወርከ ያሬድ እምቅድመ ዓይኑ ለሞት አድኀነነ  በጸሎትከ እምዕለተ እኪት ወባልሓነ እምኩሉ መንሱት " " ቅዱስ ያሬድ ሆይ ከሞት ፊት እንደተሰወርክ ሁሉ በጸሎትህ እኛን ከክፉ ቀን እና...
06/05/2026

" ከመተሰወርከ ያሬድ እምቅድመ ዓይኑ ለሞት
አድኀነነ በጸሎትከ እምዕለተ እኪት ወባልሓነ
እምኩሉ መንሱት "

" ቅዱስ ያሬድ ሆይ ከሞት ፊት እንደተሰወርክ ሁሉ በጸሎትህ እኛን ከክፉ ቀን እና ከክፋ ነገር አድነን "

መልክዓ ያሬድ

ዝክረ ቅዱስ ያሬድ

ዓመታዊ የዝክረ ቅዱስ ያሬድ ጉባኤ

ግንቦት 8/2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:30 ሰዓት ጀምሮ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፤ ሰባኪያነ ወንጌል እና ዘማርያን በተገኙበት
ኑ የቤተክርስቲያን ባለውለታ ቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ ክብረ በዓል በአንድነት እናክብር ።

በዓለ   ለምን ከቤት ውጭ ይከበራል?ንፍሮ የምንቀቅለው አንባበሮ የሚጋገረውስ ለምንድን ነው?በዓለማችን ካሉና ቅዱሳንን የሚያከብሩ አብያተ ክርስቲያናት ከሚገኙባቸው ሀገራት ውስጥ ብዙ ጊዜ የሚ...
01/05/2026

በዓለ ለምን ከቤት ውጭ ይከበራል?
ንፍሮ የምንቀቅለው አንባበሮ የሚጋገረውስ ለምንድን ነው?

በዓለማችን ካሉና ቅዱሳንን የሚያከብሩ አብያተ ክርስቲያናት ከሚገኙባቸው ሀገራት ውስጥ ብዙ ጊዜ የሚያከብሯቸውን ቅዱሳን መታሰቢያ የሚያደርጉት የእረፍታቸውን እለት ሲሆን የልደታቸውን ቀን የሚያከብሩላቸው ግን አንደኛ፦ የአምላካችን የመድኃኔዓለም ክርስቶስን ሁለተኛ፦ የእመ አምላክ ድንግል ማርያምን ሶስተኛ፦ የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስን ብቻ ነው፡፡ የእመቤታችን የልደት በዓል በዓለም አቀፍ ደረጃ መከበር የተጀመረው በ5ኛው -7ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ባለው ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ የእመቤታችን የልደት በዓል በምዕራባውያን ዘንድ ኬክ በመጋገርና በእመቤታችን ስም ሐውልት በመስራት ዙሪያውን ሻማ በማብራት ይከበራል፡፡ በሀገራችን በኢትዮጵያ ደግሞ ለየት ባለ መልኩ ሃይማኖታዊ ይዘቱን ሳይለቅ ባሕላዊ ገፅታውን ተላብሶ በቤተክርስቲያን ውስጥና በመላው ሕዝበ ክርስቲያን ቤት በደማቁ ይከበራል፡፡ ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን አንፃር ከዋዜማው ጀምሮ ለምስጋና በመቆም በማሕሌቱ በመሳተፍ አዳሩን ሙሉ ውዳሴው ይቀርባል፡፡ ሲነጋጋም በኪዳን ጸሎት ከዛም በሥርዓተ ቅዳሴ በመጨረሻም ደግሞ የቃል ኪዳኑን ታቦታት ይዞ በመውጣትና ሕዝቡን በመባረክ ይከበራል፡፡ ምዕመኑ ደግሞ የቤተ ክርስቲያኑ ሥርዓት ካለቀ በኋላ ወደ ቤቱ ተመልሶ ከቤተሰቡና ከጎረቤቶቹ ጋር በፍቅር ያከብራል፡፡
የእመቤታችን የልደት በዓል በሕዝበ ክርስቲያኑ ዘንድ ከቤት በመውጣት ከደጅ ላይ በመሆን ይከበራል፡፡ ከላይ እንደተጠቀሰው የእመቤታችን ወላጆች ቅድስት ሐና እና ቅዱስ ኢያቄም በአይሁድ ምቀኝነት ምክንያት ከቤታቸው ተፈናቅለው
በሊባኖስ ተራራ ላይ ነውና እመቤታችንን የወለዷት ይህን ታሪክ ለማስታወስና ትውፊቱን ለማስቀጠል በዓሉ ከቤት በመውጣት ሊከበር ችሏል፡፡ ሌላ በዚህ በዓል የሚበላው የምግብ ዓይነት ከሌላው የምግብ አይነት ለየት ይላል፡፡ በየትኛውም ቤት ንፍሮና ጥራጥሬ አይጠፋም፡፡ የዚህም ምሳሌነቱ ቅድስት ሐና በሊባኖስ ተራራ ላይ ሳለች ትመገበው የነበረው ቶሎ የሚደርስ የሆነውን ጥራጥሬና ንፍሮን በመቀቀል ነበርና እርሱን ለማስታወስ ነው፡፡ የእመቤታችንን የልደት በዓል በዚህ ዓይነት ትውፊታዊ ምስጢር ሁሉም በደመቀ ሁኔታ ያከብረዋል፡፡

ምንጭ:- የማ/ስ/ቅ/ ልደታ ለማርያምና ደ/መ/ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የተክለ ሣዊሮስ ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ

19ኛ ዙር የበጎ አድራጎት ስራ“እናንተ ግን ወንድሞች ሆይ መልካም ሥራን ለመሥራት አትታክቱ።” 2ኛ ተሰ 3÷13ሰንበት ትምህርት ቤታችን በዚህም ሳምንት ቅዳሜ 24/8/18 ዓ.ም. በአየር ጤና...
01/05/2026

19ኛ ዙር የበጎ አድራጎት ስራ

“እናንተ ግን ወንድሞች ሆይ መልካም ሥራን ለመሥራት አትታክቱ።” 2ኛ ተሰ 3÷13

ሰንበት ትምህርት ቤታችን በዚህም ሳምንት ቅዳሜ 24/8/18 ዓ.ም. በአየር ጤና ወይብላ ማርያም ጸበል በመገኘት የወንዶችን ጸጉር የመቁረጥ እና የሴቶችን ጸጉር የመስራት ስራ ለመስራት ዝግጅቱን አጠናቋል።

በዚህ የበጎ አድራጎት ስራ ላይ ጊዜው ያላችሁ በጎ ፈቃደኞች ቅዳሜ ጠዋት 3:00 በደብራችን በመገኘት እንድትሳተፉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

፣ሳሙና፣ላርጎ፣ጓንት፣ ማበጠሪያ በመለገስ አገልግሎቱን እንድትደግፉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

ለበለጠ መረጃ በ 0943303309 ወይም 0941359159 ይደውሉልን።

" እነሆ የሃይማኖት ፍሬ "      ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ከሁሉ አስቀድመን በነገሮች ሁሉ የረዳዎትን ቅዱስ እግዚአብሔርን እያመሰገንን መጋቢት 5/2018 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይ...
19/04/2026

" እነሆ የሃይማኖት ፍሬ "
ቅዱስ ዲዮስቆሮስ

ከሁሉ አስቀድመን በነገሮች ሁሉ የረዳዎትን ቅዱስ እግዚአብሔርን እያመሰገንን መጋቢት 5/2018 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በህክምና የትምህርት ዘርፍ በከፍተኛ ውጤት የተመረቁትና የሰንበት ትምህርት ቤታችን ፍሬ የሆኑት ዲ/ን ዶ/ር ተመስገን አባቡ ለዚህ ክብር በመብቃትዎ የተሰማንን ደስታ እየገለጽን ሁሉን ያደረገን እግዚአብሔርን ስለእርስዎ እናመሠግናለን።

እንኳን ደስ አልዎት።

Address

Ferensay Legaseon(41 No. Bus End Station)
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም ቤ/ክ መሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share