የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማሕበር

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማሕበር የቀደምት ኢትዮጵያዊ መሻይኾችን የዕምነትና የስብዕና መስመር በማስቀጠል ዓላማ የሚንቀሳቀስ ህጋዊ ተቋም ነው! ላይክና ሼር በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ

26/05/2026

ለመላው የኢትዮጵያ ሙስሊም ዒድ ሙባረክ

የዒድ ተክቢራ በሀጅ መሐመድ ሳኒ ሃቢብ

የኡመር 26 መስጂድ ወቅታዊ ሁኔታ እና የሸይኽ ሙሐመድ ሰዒድ መገፋት       -----------//-------------//-------------ከመጅሊስ ለውጥ ወዲህ በኡመር 26 መስጂድ ውስ...
20/05/2026

የኡመር 26 መስጂድ ወቅታዊ ሁኔታ እና የሸይኽ ሙሐመድ ሰዒድ መገፋት
-----------//-------------//-------------

ከመጅሊስ ለውጥ ወዲህ በኡመር 26 መስጂድ ውስጥ ህገ-ወጥ እና መጅሊሱ የማይገነዘባቸው አካሄዶች እየተስተዋሉ ይገኛሉ።

የዚህ አካሄድ ዋና ዓላማ መስጂዱን ለረጅም ዓመታት በኢማምነት እና በዓሊምነት ያገለገሉትን፣ የቀደምት መሻይኾችን ፈለግ የተከተሉትን ታላቁን ዓሊም ሸይኽ ሙሐመድ ሰዒድን (26) ከመስጂዱ ሙሉ በሙሉ ለማስወገድ የሚደረግ ስልታዊ ጥረት ነው።

ይህ ቡድን መሻይኾቹን ከዲን አገልግሎት ለማስወገድ እና በማህበረሰቡ ዘንድ የተሳሳቱ መረጃዎችን በመንዛት ተቀባይነታቸውን ለማሳጣት እየሰራ ይገኛል። ቢሆንም ማህበረሰቡ የድርጊቱን በስተጀርባ ያለውን የግል ጥቅም እና የስልጣን ጥማት ጠንቅቆ ተረድቶታል።

በቀን ክፍፍል የተጀመረው ይህ አካሄድ አሁን ላይ ያደረሰውን መዋቅራዊ መበላሸት በቅርቡ ከወጣው የስራ መደብ ክፍፍል መረዳት ይቻላል። ከላይ በተያያዘው ሰነድ ላይ የተገለጹት አካላት የስራ ድርሻ

እንደሚከተለው ይነበባል፦
1. ሸይኽ ሙሐመድ ሰዒድ፦ ዋና ኢማም
2. ሸይኽ ቡሽራ ዓሊ፦ ምክትል ኢማም
3. ሸይኽ አብዱልዐዚዝ ሐምዳ፦ የሱብሒ ኢማም

በተለመደው የአሰራር መዋቅር፣ ምክትል ኢማም ዋናው ኢማም በሌለበት ወቅት ስራዎችን በገደብ የሚሸፍን አካል ነው። ነገር ግን አሁን ባለው ሰነድ ላይ የሱብሒ ኢማም ተብለው የመጡት አካላት የተሰጣቸው ስልጣን ተቋማዊ አሰራርን የጣሰና ዋናውን ኢማም የሚጋፋ ሆኖ ተገኝቷል።

ይህ በሸይኽ ሙሐመድ ላይ የሚደረገው በደልና ዛቻ በጥቂት ግለሰቦች የሚመራ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል፦
ሱልጣን ቱሬ የተባለው ግለሰብ፦ የኢማምነት ሚና ፍላጎት ያለውና አሁን ባለው መዋቅር በሸይኽ አብዱልዐዚዝ ስም ተገንብቶ እራሱን የጁምዓ ኸጢብ ለማድረግ በከፍተኛ ሁኔታ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።

ኑረዲን ኃይሌ የተባለው ግለሰብ፦ ይህ አካል በመስጂዱ ጥላ ስር በተለያዩ ህገ-ወጥ ተግባራት ላይ የተሰማራ ሰው መሆኑን መረጃዎች ደርሰውናል።

ለሸይኾቻችን ድምፅ ለመሆን እየሰራን በመሆኑ መላው ማህበረሰብ ከእውነትና ከፍትህ ጎን እንዲቆም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

18/05/2026

የሁከት ሹመኞች
••••••••••
በትላንትናው እለተ እሁድ ግንቦት 9/2018 ከዙሁር ሶላት በኃላ የአቃቂ ራህማ መስጂድ ከተለያዩ አካባቢዎች ተሰብስበው በመጡ ውሃቢያች በመስጂዱ ታሪክ የማይታወቅ እና የአካባቢው ሱፊያ ማህበረሰብ የማይፈልገው የውሃቢያ ትምህርት ካልተሰጠ በሚል ረብሻ አስነስተዋል ።

መስጂዱ በፖሊሶች ተከብቦ ሲቪል ለባሾችም መስጂድ ውስጥ ገብተው መጅሊሱ የላካቸው የሁከት ሹመኞች የፈጠሩትን ግርግር የታዘቡ ቢሆንም ሁከት ቀስቃሾቹ ላይ የተወሰደ እርምጃ አልታየም። ሁከቱ ከቀኑ 7 ሰአት እስከ 9 ሰአት ቀጥሎ እንደነበረ ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

የአካባቢው ማህበረሰብ ፊርማውን አባሪ በማድረግ እስከ ሰላም ሚኒስቴር ድረስ በደብዳቤ ተደጋጋሚ ጥያቄ አቅርቦ መፍትሄ ባለማግኘቱ ምክንያት መጅሊሱን የተቆጣጠሩት ውሃቢያዎች የሱፍያውን መሳጂዶች ለእራሳቸው የውሃቢያ ቡድን ለማስረከብ እና አስተምህሮታቸውን በሃይል ለማንገስ በማለም ፖሊሶችን ተጠቅመው ሱፊያውን ክፉኛ እያዋከቡ እና እያስፈራሩት ይገኛሉ።

ሀገሪቱ የምትመራበት ህገመንግስት ማንኛውም ሰው የፈለገውን እምነት የመተከተል እና የመስበክ ነፃነት የሰጠ ቢሆንም ወሀቢያ መራሹ መጅሊስ የወሀቢዝም አስተመህሮ አስገድዶ ሙስሊሙን ማህበረሰብ ለማጥመቅ እየሰራ ይገኛል። መጅሊሱ ሁሉም መስጂዶች የእኔ ናቸው ብሎ የመቀማት አስተምህሮት የመቅረፅ ህገመንግስታዊም ሆነ በመጅሊሱ አዋጅ ደንብ መሰረት መብት ስለሌለው መስጂዶችን በሁከት እየነጠቀ ወሀቢዝምን በግዳጅ ላስተምራቹህ የሚለው ህገወጥ አካሄድ ሊቆም እና የእምነት ነፃነት ሊከበር ይገባል።

Ministry of Peace የሰላም ሚኒስቴር

የመቃብር ክፍያ 4000 ተደረገ••••••••••••የኦሮሚያ መጅሊስ የመጅሊስ አባል መዋጮ ካልከፈላችሁ በሙስሊም መቃብር አትቀበሩም የሚል ህግ ማውጣቱ የሚታወቅ ሲሆን የአዲስ አበባ መጅሊስ አዲ...
12/05/2026

የመቃብር ክፍያ 4000 ተደረገ
••••••••••••
የኦሮሚያ መጅሊስ የመጅሊስ አባል መዋጮ ካልከፈላችሁ በሙስሊም መቃብር አትቀበሩም የሚል ህግ ማውጣቱ የሚታወቅ ሲሆን የአዲስ አበባ መጅሊስ አዲስ ባወጣው መመሪያ ከዚህ ቀደም ለመቃብር ይከፈል የነበረውን 2000 ብር ወደ 4000 ብር ከፍ አድርጓል። መጅሊሱ ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ዝቅተኛ የመቃብር ዋጋ ማቅረብ ሲገባው እንደ ነጋዴ እያሰበ ኑሮ ተወደደ ነዳጅ ጨመረ ብሎ በየጊዜው የመቀበሪያ ዋጋ መጨመር በደል ነው። አንድ ድሃ የሆነ ሰው ለመቀበር ከነ ብሎኬቱ ከ7000 ብር በላይ ያስፈልገዋል። አቅም የሌለው ሰው በሙስሊም መቃብር መቀበር አይችልም።

የመጅሊሱን ስልጣን ከያዝን ለሙስሊሙ ማህበረሰብ መብት እንቆረቆራለን የተሻለ አገልግሎት እንሰጣለን ሲል የነበረው የወሀቢ ቡድን መጅሊሱን ከያዘ በኋላ መጅሊሱ ህዝበ ሙስሊሙን የሚበዘብዝ ስግብግብ ነጋዴ አድርገውታል።

10/05/2026

የኢስነይን ሶለዋት አዲስ አበባ ፒያሳ ሱማሌ ተራ በሚገኘው የቃጥባሬ መስጂድ

በጉራጌ ዞን የጉንችሬ ከተማ መጅሊስ ዕለተ ሰኞ ቀን የሚደረግ የሶለዋት እና የዱዓ ፕሮግራም ህገወጥ ነው ብሎ አገደ። በጉንችሬ ከተማ ነስር መስጂድ ውስጥ የሚገኙ ሙስሊሞች በሳምንት አንድ ቀን...
10/05/2026

በጉራጌ ዞን የጉንችሬ ከተማ መጅሊስ ዕለተ ሰኞ ቀን የሚደረግ የሶለዋት እና የዱዓ ፕሮግራም ህገወጥ ነው ብሎ አገደ። በጉንችሬ ከተማ ነስር መስጂድ ውስጥ የሚገኙ ሙስሊሞች በሳምንት አንድ ቀን ዘወትር ሰኞ ተሰባስበው ዱዓ እና ሰለዋት ያደርጋሉ። ይህን ፕሮግራም የሚቃወሙ ጥቂት ወሀብዮች ቅሬታ አቅርበዋል በሚል ሽፋን ብዙሃኑ የመስጂዱ ማህበረሰብ አምኖ ተቀብሎ የሚተገብረውን የኢስነይን ፕሮግራም ማስቆም የማህበረሰቡን የእምነት ነፃነት መግፈፍ ህገመንግስቱን መቃረን ነው።

የጉራጌ ማህረሰብ ሰኞ ቀን ኢስነይን ማክሰኞ ቀን መገርገብያ ብሎ ለዱዓ እና ለሶለዋት መሰባሰብ ለመቶ አመታት ሲተገብረው የኖረው እምነቱ እሴቱ ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መጅሊሱን የተቆጣጠረው ወሀቢያ መራሽ መጅሊስ ለዘመናት ሲተገበሩ የኖሩ የሱፍያው ማህበረሰብ እምነቶችን ለማጥፋት እየሰራ ይገኛል።

መጅሊሱ በወሀቢያ እጅ እስካለ ድረስ ሱፍያው ማህበረሰብ ህገመንግስቱ ያጎናፀፈውን የእምነት ነፃነት መነጠቁ አይቀሬ ነው። መፍትሄው ሱፍያው ማህበረሰብ ለመብቱ መታገል እና ከጨቋኙ ወሀቢያ መራሽ መጅሊስ እራሱን ነፃ ማውጣት ብቻ ነው።

ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡንإنا لله وإنا اليه راجعون ለረጅም ዓመታት በኑር መስጂድ ውሰጥ በተለያዩ ዘርፎች ይካድሙ የነበሩት የምንወዳቸው ሸይኽ ኸድር ኡመር  ወደ አኼራ ተሻግ...
09/05/2026

ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን
إنا لله وإنا اليه راجعون

ለረጅም ዓመታት በኑር መስጂድ ውሰጥ በተለያዩ ዘርፎች ይካድሙ የነበሩት የምንወዳቸው ሸይኽ ኸድር ኡመር ወደ አኼራ ተሻግረዋል።

ዝሁር በኒ መስጂድ ከተሰገደ በኋላ ቀብራቸው በጉለሌ የሙስሊም መቃብር የሚፈፀም ይሆናል።

አላህ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጆቻቸው እና ለመላው ማህበረሰብ መፅናናትን እንዲሰጣቸው እሳቸውምንም አላህ በሰፊው ፊርደውሰል ጀና ይቀበላቸው ዘንድ አላህን እንማፀናለን።

አስቸኳይ መልዕክት ‎ከቋንጤ አቡበክር ሲዲቅ መሥጂድ ሙስሊም ማህበረሰብ  ‎••••••••••••••••••••••••••••‎አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላህ የተከበራችሁ ሙሥሊም እህት ወንድሞች ‎‎...
07/05/2026

አስቸኳይ መልዕክት ‎ከቋንጤ አቡበክር ሲዲቅ መሥጂድ ሙስሊም ማህበረሰብ
‎••••••••••••••••••••••••••••
‎አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላህ የተከበራችሁ ሙሥሊም እህት ወንድሞች

‎እንደሚታወቀው በጉራጌ ዞን ውስጥ የሚገኘው የቋንጤ አቡበክር ሢዲቅ ሙስሊም ማህበረሰብ በሁሉም ነገር ንቁ በሠላም ታዋቂ ለሀገሪቱ ህገመንግስት ተገዢ የልማት አርበኛ ከሁሉም እምነቶች ተሥማምቶ በሰላም የሚኖር የሠላም ማህበረሰብ መሆኑ የማይካድ ሀቅ ነው ።

‎ከጥንት ከመሻይሆቻችን ከነብዩ ሲወርድ ሲዋረድ ወደኛ የደረሰዉ የተቀበለውን እምነት እና እስልምና በተጠንቀቅ ይዞ ለዲኑ ደሞ ምንም ማይበግረው ከመስጠት ወደኋላ የማይል የተመሠከረለት ጀግና ማህበረሰብ ነው ።

‎ከባለፉት ሁለት ሳምንታት ወደዚህ ከማህበረሰቡ ያፈነገጡ #የወሓብያ አንጃ ተከታይ በሆኑ ጥቂት ረባሾች ሚዲያ ላይ የሚለቀቁ የተዛቡ መረጃዎች ሙሉ በሙሉ ከእውነት የራቀ ሙሥሊሙን የማይመጥን ግድፈት መሆኑ ለማረጋገጥ እንወዳለን ።

‎መስጂዱን በዛሬ ህልውና እንዲቆይ ያደረጉት በልማት የሚታወቁት የመሥጂድ ኮሚቴዎች የሥም ማጥፋት ዘመቻ በጭራሽ የማይገባቸውና ማህበረሠቡን ለማወዛገብ የሚደረግ እንቅስቃሴ መኖሩን ታዝበናል ህዝባችንም ነቅቷል እነማን ከየት እንደሚሾፈርም አዉቋል
‎በዛሬ ዘመን ህዝብን መሸወድ አይቻልም ለማለት እንወዳለን ።

‎ሲቀጥል በወረዳው መንግስት ፓርቲ እና የጸጥታ ሀላፊ ላይ ህዝብ ከመንግስት ለማጋጨት በጣም ብዙ ርቀት ሄደዋል በሚል የቀጠፉት ዉሸት ሲሆን በተቃራኒው ጌታ ወረዳን በሀገሪቱ አሉ ከሚባሉ ሞዴል ወረዳዎች ቅድሚያ ያሠለፉ ጀግና መሪ መሆናቸዉ መለሰ የወረዳዉ ህዝብ ምስክር ነዉ ።

‎በ2006 በቋንጤ አካባቢ ሙስሊም ማህበረሰብ መስጂድ አስፈላጊ መሆኑ በመታመኑ ግንባታዉ ተጀመረ ። አቡበከር ስዲቅ መስጂድ እስከ 2015 ዓል በግንባታ ቆይቷል በዚህ ወቅት ሙስሊሙ ከፍተኛ ርብርብ አድርጓል አልሃምዱሊላህ ።

‎በመሆኑም በ2015 ዓ.ል የግንባታ ኮሚቴ የዞን መጅሊሥ የወረዳ ጸጥታ የሀገር ሽማግሌ የመስጊድ ኮሚቴ የጌቶ ኡለማ ተፈራርመው የቀረው የግንባታ ሥራ በሶስት ወር አጠናቀው እንዲያሥረክቡ ስራዉ ከወሰዱ አካላት ጋሬ ተፈራርመው ሀላፊነት እንዲወጡ ተሰጥቶ ነበር ።

‎ይህን መፈጸም ሳይችሉ ሲቀር ከሶስት አመት በኋላ የአካባቢው ማህበረሰብ የቋንጤ ወጣቶች የመሥጂዱን ያልተነጠፈው ቦታ ከራሣቸው አዋጥተው በጁመአ አስተባብረው አ/አ እና የተለያየ ቦታ ያሉ እህት ወንድሞች ያላቸው ነገር አሠባስበው የመሥጂዱ ግማሽ ምንጣፍ አስነጠፉ ።

‎መስጂዱ ተሰርቶ ሲያልቅ የመሻኢኾቹ ጠላት ታሪክ መነሻ የሌለዉ የወሓብያ ቡድን የሙሽሪኮች መስጂድ ፣የሙብተዲኦች መስጂድ በሚል ሙሉ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ሳይሆን ለዲን ከፍተኛ ልፋት ያደረጉትን ባለታሪኮች አብሬትየን ፣ቃጥባሬንና ፣ዘቢሞላን በመስደብ
‎ከነዚህ እናፀዳዋለን እንቆጣጠረዋለን ህገወጥ ፕሮፓጋንዳቸዉ መንዛት ከመጀሩ ቢሠነብትም ማህበረሰቡ ንቆት እየሰማ እያየ ባላየ ቢያልፍም ምርጫን ተገን በማድረግ የመረበሽ እቅድ በመሆኑ ዝም ብለን ለማለፍ አልፈለግንምና ሁሉም ይህንን ህገወጥ ተግባር ሊያዉቅልን ይገባል ።

‎በዛው የተዘረጋው የውሀ መሥመር አሠርተው ለውዱእ እና የሽንትቤት ውሀ ለተጠቃሚው ክፍት አስደርገው የሀገሪቱን የኮሪደር ልማት በመደገፍ የመሥጂዱ አጥር መቀባቱ ያልተመቻቸው #የወሓቢያ ቡድን የመስጂዱን የማህበረሠቡን እና ሙሉ የሆነ መሥጂዱ በሰላም ባለበት ሁኔታ ለመረበሽ ለመበጥበጥ እና ከፊት ለፊት ያለውን ሀገራዊ ምርጫ ለማወክ ሆን ብሎ የተሠራ የውሸት ቅንብር በሚዲያ ቅሥቀሳ መደረጉ የረብሻ አጀንዳ መሆኑ ለማሳወቅ እንሻለን ።‎

 ዛሬ ከዙሁር ሶላት በኃላ የአቃቂ ራህማ መስጂድ ተበጥብጧል !!ከተለያዩ አካባቢዎች ተሰብስበው የመጡ ውሃቢያች በመስጂዱ ታሪክ የማይታወቅ እና የአካባቢው ሱፊያ ማህበረሰብ የማይፈልገው የውሃቢ...
03/05/2026



ዛሬ ከዙሁር ሶላት በኃላ የአቃቂ ራህማ መስጂድ ተበጥብጧል !!

ከተለያዩ አካባቢዎች ተሰብስበው የመጡ ውሃቢያች በመስጂዱ ታሪክ የማይታወቅ እና የአካባቢው ሱፊያ ማህበረሰብ የማይፈልገው የውሃቢያ ትምህርት ካልተሰጠ በሚል ረብሻ አስነስተዋል።

የአቃቂ ራህማ መስጂድ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና የወረዳ መጅሊስ ፀሀፊ የሆነው አቶ ይግረም ገብረመድህንን የመጅሊሱ መተዳደሪያም ሆነ የምርጫ ማስፈፀሚያ ደንቡ ባልከለከሉበት ሁኔታ ከህግ እና ስርዓት ውጪ አንዱን መልቀቅ አለብህ የምትለቀውም መስጂዱን ነው በማለት እና ሌሎች 2 ተጨማሪ ውሃቢያዎችን የአካባቢው ሱፊያ ማህበረሰብ ይሁንታ በሌለበት ኮሚቴ ውስጥ በማካተት እስከዛሬ መስጂዱ ላይ የቆየውን ሱፊያዊ አስተምህሮ ለማጥፋት እና በምትኩ የውሃቢያን አስተምህሮ ለማንገስ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እየተደረገ እንደሆነ በተደጋጋሚ ልጥፎች በተለያዩ የሶሻል ሚዲያ አማራጮች ስንገልፅ መቆየታችን ይታወቃል።

በመስጂዱ ታሪክ ከቶ የማይታወቅ ውሃቢያ ስብከት ከተለያዩ አካባቢዎች ሰዎቻቸውን በማምጣት መንግስትን አክብሮ ህግ እና ስርዓት በተከተለ መንገድ ከዛሬ ነገ መፍትሄ እናገኛለን በሚል የታገሰውን የአካባቢውን ሱፊያ ማህበረሰብ ክፉኛ እየተፈታተኑት ነው።

አቶ ይግረም ገብረመድህንን ማንሳት እና ሌሎች 2 ተጨማሪ ውሃቢያዎችን ማካተቱ የተፈለገው መስጂዱ ላይ የአስተሳሰብ ገፅታ ለውጥ ለማድረግ መደላድል ለመፍጠር መሆኑ ከጅምሩ የሚታወቅ ቢሆንም አሁን ጉዳዩ ለመንግስት አካላትም ጭምር ግልፅ ሆኗል።

በተለያየ ጊዜ የአካባቢውን ሱፊያ ወጣት ከመብት ጥየቃ ትግል ገሸሽ ለማድረግ በማቀድ ለፀጥታ አካላት ስሁት መረጃን በማቀበል እና በጥቅም ጭምር በመያዝ ንፁሃን ወንድሞቻችን እና እህቶቻችንን በተደጋጋሚ በግፍ አሳስረዋል።

9ኙም ስራ አስፈፃሚዎች ውሃቢያ የሆኑበት የክፍለ ከተማው መጅሊስ በክፍለከተማው ከሚገኙ ከ30 በላይ መሳጂዶች ከ2 እና 3 መስጂዶች በቀር ሙሉ ለሙሉ ለራሱ የውሃቢያ ቡድን ያስረከበ ሲሆን አሁን የቀሩትን የሱፊያ መስጂዶች ሙሉ ለሙሉ ለመቆጣጠር ከፍተኛ ሴራ ላይ ተጠምደዋል።

ጉዳዩን በመጅሊስም ሆነ በመንግስት በኩል እስከላይኛው እርከን ድረስ ደረጃውን ጠብቀን ያሳወቅን ሲሆን ሰላም ሚኒስቴር ጉዳዩ በድጋሚ እንዲታይ እና መፍትሄ እንዲሰጠን ለታች አመራሮች ትዕዛዝ እናስተላልፋለን ብለውን በመጠባበቅ ላይ እንገኛለን።

በመጨረሻም የሚመለከታቹ የመንግስት አካላት ህግን ሽፋን በማድረግ በእጃቸው ያለውን ማህተም ተጥቅመው የሱፍያውን ህልውና ለማክሰም በማንአለብኝነት እየተጉ የሚገኙ የመጅሊስ አመራሮችን እንድታስታግሱልን እና በአስቸኳይ ተገቢውን እልባት በመስጠት የአካባቢያችን ሱፊያ ማህበረሰብ ህገ-መንግስታዊ የሆነው የእምነት ነፃነት መብትን እንድታስከብሩልንን እንጠይቃለን



Ministry of Peace የሰላም ሚኒስቴር

"ከዑስማን ኢብን አፋን (ጠሮ) መስጅድ ማህበረሰብ የተላለፈ መልዕክት"ከለፉት ጥቂት ቀናት ጀምሮ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ መስጅዳችንን አስመልክቶ እየተሰራጨ ባለው እጅግ ከእውነት በራቀ መረጃ ላ...
29/04/2026

"ከዑስማን ኢብን አፋን (ጠሮ) መስጅድ ማህበረሰብ የተላለፈ መልዕክት"

ከለፉት ጥቂት ቀናት ጀምሮ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ መስጅዳችንን አስመልክቶ እየተሰራጨ ባለው እጅግ ከእውነት በራቀ መረጃ ላይ በመስጅዱ ማህበረሰብ የተሰጠ ማብራሪያ ።

ከሰሞኑን የመስጅዳችን ሰላም መሆን በማይሹ አካላት እጅግ ሰላማዊ ሁኔታ ላይ ያለው መስጅዳችንን ወደ ሁከት ቀጠና ለመለወጥ ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም የመቀስቀስ ብሎም ጥሪ መሰል መልዕክቶችን እየተላለፉ ይገኛል ፤ ማህበረሰቡ ጉዳይን በአንክሮ እየተከታተለ ያለ እና ከዛሬ ነገ ይሻላል በሚል ተስፋ መልስ ከመስጠት የተቆጠበ ቢሆንም እነዚህ አካላት በጉዳዩ ላይ በመቀጠል መስጅዱን ለመረበሽ ያመቻቸው ዘንድ የወጣት ማህበራችን እንዳንድ አባላትን ጨምሮ በመስጅዱ ማህበረስብ ላይ በውሸት የተቀነባበረ የስም ማጥፋት ዘመቻቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል ።

የዑስማን ኢብን አፋን (ጠሮ) መስጅድ ማህበረሰብም ጉዳዩን እስከላይኛው እርከን ላይ ላሉ የህግ አካላት ከተጨባጭ ማስረጃ ያሳወቀ ሲሆን ጉዳዩን በትኩረት እና በአንክሮ በመከታተል ሀገራችን ለሀገር አቀፍ ምርጫ እየተሰናድችበት ባለችበት በዚህ ወቅት መስጅዱን ከማንኛውም ሁከት እና ረብሻ ለመከላከል ከህግ አካላት ጋር በትብብር እንደሚሰራ ለማሳወቅ እንወዳለን።

ሙስሊሙ ማህበረሰብም እውነታው ይህ መሆኑን አውቃችሁ በመረጃው በመደናገጥ በስልክም በአካልም የጠየቃችሁ በሙሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን ፤ የሚመለከተው የህግ አካልም የመስጅዱ እና የአካባቢው ሰላም መሆን በማይሹ ግለሰቦች ዳግም ግጭትን ለመፍጠር በሚመስል መልኩ እየተሰራጨ ባለው መረጃ ማህበረሰቡ ላይ ስጋትን እየፈጠረ በመሆኑ መረጃውን አጣርታችሁ የበኩላችሁን ኃላፊነት እንድትወጡ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን።

ሙስሊሙ ማህበረሰብም እውነታው እንዲያውቀው ፖስቱን ሼር እንድታደርጉት በአክብሮት እንጠይቃለን።

የዑስማን ኢብን አፋን (ጠሮ) መስጅድ ወጣት ማህበር

📸 ምስል ፤ የወጣት ማህበራችንን ስም በመጠቀም በተከፈተ ሀሰተኛ ገፅ እየተላለፉ የሚገኙ ሀከት ቀስቃሽ ጥሪ እና የስም ማጥፋት መልዕክቶች ፤ ይህ ገፅ ወጣት ማህበራችንን የማይወክል እና በዚህ በኩል የሚተላለፉ መልዕክቶች የማህበራችን አለመሆኑን እናሳውቃለን ።

Address

Fitawrari Gebeyehu Street
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማሕበር posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share