የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማሕበር

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማሕበር የቀደምት ኢትዮጵያዊ መሻይኾችን የዕምነትና የስብዕና መስመር በማስቀጠል ዓላማ የሚንቀሳቀስ ህጋዊ ተቋም ነው! ላይክና ሼር በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ

ይህን “ተፍሲር” ተጠንቀቁት!!በቅርቡ ሸህ መሀመድ ዘህረዲን በእነ ሀጅ መሀመድ ሳኒ ሀቢብ እውቅ የቁርአን ተፍሲር ላይ በፈፀሙት ድፍረት እየተነሳ ያለው ጉዳይ ቀለል ተደርጎ የሚታይ ሳይሆን በ...
15/09/2026

ይህን “ተፍሲር” ተጠንቀቁት!!

በቅርቡ ሸህ መሀመድ ዘህረዲን በእነ ሀጅ መሀመድ ሳኒ ሀቢብ እውቅ የቁርአን ተፍሲር ላይ በፈፀሙት ድፍረት እየተነሳ ያለው ጉዳይ ቀለል ተደርጎ የሚታይ ሳይሆን በሃይማኖታዊ፣ በህግ እንዲሁም በስነ-ምግባር መመዘኛዎች ተቀባይነት የሌለውና ትልቅ ትኩረት የሚሻ አጀንዳ ነው።

አንድ ሰው የአቂዳ ወይም የትርጉም ልዩነት ካለው የመረጠውን ሃሳብ የሚያንጸባርቅበት መንገድ አለ።

ነገር ግን በመላ ሐበሻ የተውጣጡ ጉምቱ ዑለሞች ለአመታት የደከሙበትን እና በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያለውን ታሪካዊ ስራ ሰርዞ፣ ደልዞ፣ ጨምሮና ቀንሶ የወሀቢይ አስተሳሰብን በሚያንጸባርቅ መልኩ መበረዝ በምንም መስፈርቶች ተቀባይነት የለውም።

ከሙያዊ እና ከስነ-ምግባር አኳያ: የሌላውን ባለሙያና አሊም ስራ ይዘት በመቀየር የራሱ አስመስሎ ማቅረብ የአእምሯዊ ንብረት ስርቆት (Plagiarism) ነው።

ከህግ አኳያ: የቅጂ መብትን (Copyright) መጣስ ትልቅ ወንጀል የሚያስጠይቅ አሰራር ነው።

ከኢስላማዊ መመሪያ እና ከሸሪዓ አንፃር: የኡለማዎችን ድካም ባለቤትነት ሳያከብሩ የመጽሐፍ ይዘትን መለወጥ "አማናን" መጣስ ሲሆን፣ በኢስላም ታሪክም ላይ በጁሃላ የተፈፀመ ትልቅ ነውርና ሌብነት ተደርጎ ይወሰዳል።

በመሰረቱ በሳቸው ደረጃ ያለ ጃሂል ዝቅ ብሎ እንዲማር እንጂ እንኳን የዐሊሞችን ልፋት "ማረም" የራሱን የቁርአን ተፍሲር ኪታብ ማዘጋጀት አለበት ብለንም እናምንም።

ከዚህ ውጪ የተፍሲሩ አዘጋጆች የማይደግፉትንና አጥፊ የሆነን የወሀቢይ ትርጓሜ በዋናው ሥራ ውስጥ አስገብቶ ቃላትንና አረፍተ ነገሮችን መበረዝና ኪታቡን በነፃ ማደል ግን በታሪክ እና በእስልምና ላይየተፈፀመ ውንብድና እንጂ ታሪክ ሰሪነት አይደለም።

የእውነተኛ ዐሊም እና ታሪክ ሰሪ አሻራው የሚለካው የራሱን ስራ ሰርቶ ሲያስረክብ እንጂ የሌሎችን ድካም እያበላሹ በመበረዝ አይደለም። ታሪክን ለመስራት የራሳችንን መንገድ መሄድ እንጂ የሌሎችን ታሪክና አሻራ ማፍረስ ጎደሎነትን ማመን ነው።

ይህን ጉዳዩንም በዝምታ አናየውም።

14/09/2026
09/09/2026

ለሺ ዓመታት የነገሰ የኩፍር ጨለማ የተገረሰሰበት ብርሃን የፈነጠቀበት የረቢአል አወል ወር ሊያልቅ ጥቂት ቀናት ቀርተውታል። ሲራቸውን በመተዋወስ በሰለዋት እንበራታ!

07/09/2026

ውድ ሸይኾቻችን እናቶቻችን እህቶቻችን ጥሪው የነቢ ነው ብላችሁ ጥሪአችንን አክብራችሁ ተገኝታችሁ ሶብር አድርጋችሁ እስከ መጨረሻዋ ሰዓት አብራችሁን ስለቆያችሁ በአላህና በነቢ ስም ላቅ ያለ ምስጋናን እናቀርባለን

ጀዛኩሙሏሁ ኸይረን

አመት አመት ይደጋገምብን🤲

07/09/2026
«ሰውነት ይቀድማል» በሚል መሪ ቃል የነጃሺ ኢስላማዊ ማህበር ከኡለማዎችና ከወጣቶች ጋር ያካሄደው የጉብኝት መርሃ ግብር በሰላም ተጠናቋል። መርሃ ግብሩ ወጣቶችን በኢስላማዊና ማህበራዊ እሴቶች...
07/09/2026

«ሰውነት ይቀድማል» በሚል መሪ ቃል የነጃሺ ኢስላማዊ ማህበር ከኡለማዎችና ከወጣቶች ጋር ያካሄደው የጉብኝት መርሃ ግብር በሰላም ተጠናቋል።

መርሃ ግብሩ ወጣቶችን በኢስላማዊና ማህበራዊ እሴቶች ለማነፅ እና የነብያችንን ﷺ የፍቅርና የመተሳሰብ አስተምህሮ ለማስፋፋት ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል።

የነጃሺ ኢስላማዊ ማህበር በ1501ኛው የነብያችን ﷺ ዊላዳ ወቅት ባዘጋጀው የጉብኝት መርሃ ግብር ላይ የተገኙት ኡለማዎች፣ ወጣቶች የነብያችንን ﷺ ምሳሌያዊ ህይወት በመከተል ለማህበረሰቡ ጠቃሚ...
07/09/2026

የነጃሺ ኢስላማዊ ማህበር በ1501ኛው የነብያችን ﷺ ዊላዳ ወቅት ባዘጋጀው የጉብኝት መርሃ ግብር ላይ የተገኙት ኡለማዎች፣ ወጣቶች የነብያችንን ﷺ ምሳሌያዊ ህይወት በመከተል ለማህበረሰቡ ጠቃሚ የሆኑ አወንታዊ ተግባራት ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ አቀረቡ።

ሀገርን የሚያነቁና ህብረተሰብን የሚጠቅሙ ቦታዎችን መጎብኘት የሀገር ውዴታንና አብሮነትን የሚጨምር በጎ ተግባር ነው።

የጉብኝት ቪዲዮውን ዝርዝር ዘገባ በዩቲውብ ገፃችን ይጠብቁ

የ1501ኛው ዊላዳ በልዩ የጉብኝት መርሃ ግብር ተከበረ!የነጃሺ ኢስላማዊ ማህበር የ1501ኛውን የነብያችንን ﷺ ዊላዳ በማስመልከት ከኡለማዎች፣ ከወጣቶች እና ከአባላቱ ጋር ልዩ የጉብኝት መርሃ...
07/09/2026

የ1501ኛው ዊላዳ በልዩ የጉብኝት መርሃ ግብር ተከበረ!

የነጃሺ ኢስላማዊ ማህበር የ1501ኛውን የነብያችንን ﷺ ዊላዳ በማስመልከት ከኡለማዎች፣ ከወጣቶች እና ከአባላቱ ጋር ልዩ የጉብኝት መርሃ ግብር አካሄደ።

መርሃ ግብሩ የመውሊድን መልዕክት ከመድረክ ውጭ ወደ ማህበረሰቡ ለማስፋፋትና ወጣቶችን ከኡለማዎች ጋር በማቀራረብ በነብያችን ﷺ ፍቅር የተገነባ የመተሳሰብ መንፈስን ለማጠናከር ያለመ ነው።

ዛሬ በዐሊ መስጂድ የነብያችን ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም መውሊድ በዚህ መልኩ በድምቀት ተከብሯል!
01/09/2026

ዛሬ በዐሊ መስጂድ የነብያችን ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም መውሊድ በዚህ መልኩ በድምቀት ተከብሯል!

ሰውነት ይቀድማል በሚል መሪ ቃል 1501ኛውን የነብያችን ﷺ ዊላዳ  ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው የእግር ኳስ ውድድር የሁለተኛ ዙር ጨዋታዎች የተካሄዱ ሲሆን የጨዋታዎቹ ውጤት፦ኻሊድ (01) ...
30/08/2026

ሰውነት ይቀድማል በሚል መሪ ቃል 1501ኛውን የነብያችን ﷺ ዊላዳ ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው የእግር ኳስ ውድድር የሁለተኛ ዙር ጨዋታዎች የተካሄዱ ሲሆን የጨዋታዎቹ ውጤት፦ኻሊድ (01) መስጂድ 5–3 ዑስማን ኢብኑ ዐፋን (ጠሮ) መስጂድ፣ ሙዓዝ ኢብኑ ጀበል መስጂድ 6–2 ለኸውፈላህ መስጂድ ጨዋታው ያለቀ ሲሆን።

ለዚህ የመውሊድ መርሃ ግብር በተነሳሽነት በመሳተፍ የወጣቶችን አቅም በመጠቀም ለሃይማኖታዊ እሴቶችና ለማህበረሰብ ዕድገት የምታደርጉት ተሳትፎ ይበልጥ እንዲጎለብት እየተመኘን ለመስጂዱ ጀመዓዎች እና ለአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማህበር አባላት ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

Address

Fitawrari Gebeyehu Street
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማሕበር posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share