22/05/2026
🕊በአሁኑ ዘመን ነቢያት አሉን? 🗣አዎን አሉ📖
✍️የቃሉ ትርጓሜ በሶስት ቋንቋዎች ሲታይ:-
👉ከቃሉ ምንጭ/Etymology/ እንመልከት:-
1) በዕብራይስጥ(Hebrew)
✍️"ነቢይ"= nabû/Nāvīʼ/(נָבִיא) ማለት ሲሆን ትርጓሜውም የመለኮትን ቃል ከምንጩ ተቀብሎ ለሕዝቡ ሳይጨምር እና ሳይቀንስ የሚያውጅ(proclaim)፤ የህዝቡንም ጩኸት ለአምላክ የሚያቀርብ የያህዌ ተወካይ እና አፍ ማለት ነው።
✍️በብሉይ ኪዳን በተለያዩ ስፍራዎች ላይ ነቢያት "seer/“רֹאֶה” (Ro’eh) ወይም “חֹזֶה” (Chozeh) ተብሎም ተጠርተዋል ትርጓሜውም 👉"ባለራዕይ/visionary ፣ ባለመገጥ እና ራዕይ የሚያይ" ማለት ነው።1ሳሙ9:9፤ 2ሳሙ24:11፤2ዜና9:29
ወይም ኢሳ1:1፤ሕዝ1:1፤ዳን7:1-2
✍️ሌላኛው የነቢያት መጠሪያ=’Ish HaElohim (ኢሽ ሃኤሎሂም) ትርጓሜውም "የእግዚአብሔር ሰው" ማለት ነው።አንድ ሰውን "የእግዚአብሔር ሰው ስንል:- ለእግዚአብሔር የተለየ፤ በመንፈስ የሚመራ፣የእግዚአብሔርን ቃል የሚናገር፣ በቅድስና የሚመላለስ እና ሕዝቡን የሚያገለግል ማለታችን ነው። ዘዳ33:1፤ 1ኛሳሙ9:6፤1ኛነገ17:18፤1ጢሞ6:11፤2ጢሞ3:17።
2) በግሪክ(Greek) ነቢይ
✍️προφήτης (Prophētēs) ማለት ሲሆን የሁለት ቃላት ውህደት ነው:_
pro = ውክልና/ስም / on behalf of
phemi = መናገር / to speak
ስለዚህ ትርጓሜው፦
Prophet = one who speaks for God
“በእግዚአብሔር ስምና ውክልና የሚናገር ሰው” ማለት ነው።
3)በግዕዝ (Ge’ez) "ነቢይ"
✍️ነቢይ (Nabiy) በቀጥታ ከሴሜቲክ ቋንቋ ዕብራይስጥ የተወረሰ ሲሆን ያለፈውንና የሚመጣውን በእግዚአብሔር መንፈስ ተነድቶ የሚያውጅ ማለት ነው።(በ1970ዓ.ም በካህናት እና በሀገረሰብ ቋንቋ ከታተመው የደስታ ተከለወልድ ያማረኛ መዝገበ ቃላት የተወሰደ።)
👉ነቢየ ጽድቅ:- ከእግዚአብሔር የሰማውንና ያየውን በቅዱስ መንፈስ ተመርቶ የሚናገር/የሚገልጥ።
👉ነቢየ ሐሰት:- ያላየውን አየኹ፤ ያልሰማውን ሰማኹ ወይም እግዚአብሔር ሳያዛቸው ታዝዣለሁ በማለት ከራሳቸው/ከሌላ አለም በመኮረጅ የሚናገር/ሩ።(ት.ሕዝ13:1-23/ት.ኤርሚ14:14-16/ዘዳ 18/ዘዳ13/1ኛ ነገ22:23/1ነገ13:18
📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖
"ነቢይ/ነቢይት":- የወደፊቱን እና የአሁኑን ቃል/ድምጽ/መልዕክትን ከእግዚአብሔር ተቀብለው ለሕዝቡ የሚናገሩ የእግዚአብሔር አፍ ናቸው።
📖የነቢይ ዋና ተግባራት📖
1)የእግዚአብሔርን ቃል ማወጅ
2)ሕዝብን ወደ ንስሐ መጥራት
3)ስለ ወደፊት ነገር መናገርና መግለጥ
4)መንፈሳዊ መሪነት/ምሪት መስጠት
5) ማስጠንቀቅ
6) ማጽናናት
7) የእግዚአብሔር ፈቃድ መግለጥ
📖የብሉይ እና የሐዲስ ኪዳን ነቢያት📖
✍️የብሉይ ኪዳን ነቢያት የተላኩት ለእስራኤል ሕዝብ ነው።በእግዚአብሔር እና በእስራኤላውን ዘንድም መካከለኛ ሆነው አገልግለዋል።ይሁን እንጂ ስለ መሲሁ መገለጥ፣መንግስት እና ስለ ሐዲስ ኪዳን ተመልክተው አውጀዋል።
🗣ንስሐ፤ፍርድ፤ የመሲሑ መምጣት እና የእስራኤል ዕጣ ፈንታ ይተነቢዩ ነበር።
🗣መንፈስ ቅዱስ ሁልጊዜ አይኖርባቸውም ነበር።ስለዚህ ይመጣል፣ ይፈጽምና ይመለስ ነበር።
🗣ቃላቸው እንደ እግዚአብሔር ቃል ይቆጠራል
🗣ብቸኛ መልዕክተኞች ናቸው(ካልተደመጡ እግዚአብሔር ፈጣን ፍርድን ይፈርዳል)
🗣ቅዱሳት መጽሐፍትን የመጻፍ ስልጣን ነበራቸው
🗣በሐሰተኛ ነቢያት ላይ ፍርዱ ከባድ ነበር።(ዘዳ18:20)
✍️የአዲስ ኪዳን ነቢያት የተላኩት ለቤተክርስቲያን ሲሆን የተገለጠውን ወንጌል(ኢየሱስን) ከሐዋርያት፣ ከወንጌላውያን፥ ከመምህራንና ከእረኞች ጋር ያገለግላሉ። አማኞችን በክርስቶስ እውነት ላይ ያንጻሉ፣ በፈተና ውስጥ ያጽናናሉ፤ አማኙን ለታላቁ ተልዕኮ ያበረታታሉ።
🗣መንፈስ ቅዱስ በውስጣቸው ይኖራል
🗣ትንቢታቸው ይመረመራል(እንደ ብሉይ ኪዳን ነቢያት በቀጥታ አይወሰድም።1ቆሮ14:29
🗣ክርስቶስ የፈጸመውን ሥራ ያብራራሉ
🗣ቅዱሳት መጽሐፍትን የመጻፍ ስልጣን የላቸውም።
📖የብሉይ እና የሐዲስ ኪዳን ነቢያት📖
ለመጀመሪያ ጊዜ ነቢይ በመባል የተጠራው "የእምነት አባታችን አብርሃም ነው::"ዘፍ20:7 በይሁዳ መልዕክት ቁጥር 14 ላይ "ሄኖክ" ነቢይ እንደነበር ይናገራል።
፩] መሠረተ/ቀደምት ነቢያት (Former / Foundational Prophets)
1) ነቢይ ሄኖክ
2) ነቢይ አብርሃም
3) ነቢይ ሙሴ
4) ነቢይት ማርያም(ዘጸ15:20)
5) ነቢይ ኢያሱ(የሙሴ ተተኪ)
6) መሳፍንት/መስፍኖች
7) ነቢይት ዲቦራ(መሳ 4:4)
8)ነቢይት ሕልዳና(2ነገ22:14)
9)ነቢይት ኖዓድያን (ነህ6:14)ተቃዋሚ
10) ነቢይ ኤሊያስ
11) ነቢይ ኤልሳ
12) ነቢይ ሳሙኤል
13) ነገስታት(1ኛ እና 2ኛ ነገስት) ዳዊት፣ሰለሞን..ወዘተ
14) ነቢይ ናታን
፪] ኋለኞቹ ነቢያት (Latter Prophets)
ነቢይ ኢሳይያስ / Isaiah
ነቢይ ኤርምያስ / Jeremiah
ነቢይ ሕዝቅኤል / Ezekiel
ነቢይ ዳንኤል /Daniel
ነቢይ ሆሴዕ / Hosea
ነቢይ ኢዮኤል / Joel
ነቢይ አሞጽ / Amos
ነቢይ አብድዩ / Obadiah
ነቢይ ዮናስ / Jonah
ነቢይ ሚክያስ / Micah
ነቢይ ናሆም / Nahum
ነቢይ ዕንባቆም / Habakkuk
ነቢይ ሶፎንያስ / Zephaniah
ነቢይ ሐጌ / Haggai
ነቢይ ዘካርያስ / Zechariah
ነቢይ ሚልክያስ / Malachi
🗣እነዚህ በቀጥታ የእግዚአብሔርን ቃል፣ ራእይ፣ ፍርድ፣ ንስሐ እና የወደፊት ትንቢት የሚያወጁ ነቢያት ናቸው።
📖የአዲስ ኪዳን ነቢያት📖
1) ነቢይ ዮሐንስ(መጥመቁ) ማቴ 11:9
2) ኢየሱስ ክርስቶስ ሉቃ 24:19
3) ነቢይት ማርያም(የኢየሱስ እናት-ሉቃ1:26-38)
4) ነቢይት ሐና(የፋኑኤል ልጅ 2:36)
5) 4 ሴት ልጆች(የወንጌላዊ ፊልጶስ ልጆች)ሐ.ሥራ21:9
6) ነቢይ አጋቦስ (ሐ.ሥራ 11:27)
7) ነቢይ ስላስ(ሐ.ሥራ15:32)
8) ነቢይ ይሁዳ በርሳባስ(ሐ.ሥራ 15:32)
9) ነቢይ ስምዖን-ጥቁሩ(ሐ.ሥራ 13:1
10) ነቢይ ምናሔ(ሐ.ሥራ13:1)
11) ነቢይ ሉክዮስ የቀሬናው(ሐ.ሥራ13:1)
📖📖📖📖📖📖📖📖📖
ነቢያት እና የነቢያት አገልግሎት በብሉይ ኪዳን ሳይወሰን በአዲስ ኪዳን በተለየ መልኩ መቀጠሉን የአዲስ ኪዳን መጽሐፍት ያስረዱናል።
🗣በአንጾኪያ ባለችው ቤተ ክርስቲያን ነቢያትና መምህራን ነበሩ፤ ሐ. ሥራ 13:1
🗣"አንዳንዶቹ ሐዋርያት፣ አንዳንዶቹ ነቢያት፣ አንዳንዶቹም ወንጌል ሰባኪዎች፣ ሌሎቹ ደግሞ እረኞችና አስተማሪዎች ይሆኑ ዘንድ የሰጠ እርሱ ነው፤"ኤፌ4:11
📖ወንድና ሴት ነቢያት ዛሬም አሉ🕊ለወደፊትም ይኖራል። እሰከ ቤተክርስቲያን ንጥቀትና ታላቁ መከራ ቀን ድረስ የሚቋረጥ የጸጋ ስጦታና አገልግሎት የለም።
👇👉ክፍል 3 ይቀጥላል👉...
ሐዋርያ ዶ/ር አገኘው ሹካ
የክርስቶስ ምስክሮች ቤተክርስቲያን
ግንቦት 14/2018ዓ.ም
አዲስአበባ