የኣቡነ ሰላማ ማህበር/Mahbere abune selama addis ababa

የኣቡነ ሰላማ ማህበር/Mahbere abune selama addis ababa Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የኣቡነ ሰላማ ማህበር/Mahbere abune selama addis ababa, Addis Ababa.

✝✝✝ የካቲት ➊➏ ኪዳነ ምህረት ✝✝✝                      ➣እንኳን አደረሰን!!!ኪዳነ ምህረት ማለት የምህረት መሐላ ማለት ነው።ከ 33 ቱ በዓላተ እግዝእትነ ድንግል ማርያም አ...
22/02/2025

✝✝✝ የካቲት ➊➏ ኪዳነ ምህረት ✝✝✝
➣እንኳን አደረሰን!!!
ኪዳነ ምህረት ማለት የምህረት መሐላ ማለት ነው።
ከ 33 ቱ በዓላተ እግዝእትነ ድንግል ማርያም አንዱ ነው።
✔ እመቤታችንም ከጌታችን መቃብር እየሄደች በምትለምንበት ጊዜ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና ምን ልታመጣብን ነው በማለት ሊጣሏት ሲመጡ ጌታችንም ከዓይናቸው ሰውሯታል አይሁድም ጠባቂ ቢያቆሙ እመቤታችን ዕለት ዕለት መሄዷን አላቋረጠችም እመቤታችንም እንዲህ ብላ ስትጸልይ ልጄ ወዳጄ ሆይ ከስጋዬ ስጋ ከነፍሴ ነፍስ ነስተህ ሰው በመሆንህ
ዘጠኝ ወር ከ 5 ቀን በማኅጸኔ ያደረክ።
ከአንተ ጋር ሀገር ለሀገር ስለ መሰደዴ መጥተህ ልመናዬን ትሰማኝ ዘንድ እለምንሃለሁ አለች ።
✔ በዚህ ጊዜ ንውጽውጽውትል ሆነ መቃብራት ተሰነጣጠቁ ጌታሽንም እልፍ ከእልፍ መላእክቱ ጋር መጥቶ ሰላም ለኪ ማርያም ምን እንዳደርግልሽ ትለምኚኛለሽ አላት ።
✔ እርሷም መታሰቢያዬን ያደረገውን ስለ ስሜ ለችግረኛ
የሚራራውን በስሜ ቤተክርስቲያን ያነጸወን መባዕ የሰጠውን
ከሃይማኖት ከፍቅር ጽናት ልጁን በስሜ የጠራውን ሁሉ ማርልኝ ከሞተ ስጋ ከሞተ ነፍስ አድንልኝ አለችው ።
✔ ጌታችንም ይህን ሁሉ እንዳደርግልሽ መሐልኩ ለኪ በርእስየ ወበ አቡየ ህያው ወበመንፈስ ቅዱስ ብሎ ቃል ገብቶላት አርጓል ።
✔ ከመረጥኳቸው ጋራ ቃል ኪዳኔን አደርጋለሁ ተብሎ በዳዊት መዝሙር እንደተጻፈ እግዚአብሔር ከመረጣቸው ሁሉ ጋር ቃል ኪዳን አድርጓል ፤ወደፊትም ያደርጋል ።[
መዝ 89፥3 ] ቃል ኪዳኑም የምህረት ቃል ኪዳን ነው ።
ቅዱሳኑ
ወስበሀት ለእግዚአብሔር ከእመቤታችን ረድኤት በርከት ይክፈለን ✔✔~~ አሜንንንንንንንንንንንንንን

✍✍   ጥር 21  ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያ ወረደ ወልድ እም ዲበ ልዕልናጠሊሳነ ንግሥ ሶቤሃ ከደና!! ልቡናዋ በይኩነኒ የጸና ንጽሐ ሥጋ ፣ ንጽሐ ነፍስ ፣ ንጽሐ ልቡና አስተባብራ የያዘች ወላዲተ...
28/01/2025

✍✍ ጥር 21
ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያ ወረደ ወልድ እም ዲበ ልዕልና
ጠሊሳነ ንግሥ ሶቤሃ ከደና!!

ልቡናዋ በይኩነኒ የጸና ንጽሐ ሥጋ ፣ ንጽሐ ነፍስ ፣ ንጽሐ ልቡና አስተባብራ የያዘች ወላዲተ አምላክ ምንም እንኳን የአምላክ እናት ብትሆንም ሞተ ሥጋ ለሁሉም ዕጣ ፈንታ በመሆኑ በቃል መነገሩ በልብ መታሰቡ ከፍ ከፍ ይበልና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ተንሥኢ ወንዒ” የነፍሴ ደስታ የኾንሽ ውድ እናቴ ሆይ ተነሥተሽ ወደ እኔ ነዪ (መኃ ፪፥፲) ብሏታል።

ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ

ቅዱስ ዳዊት “ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ሀገረ እግዚአብሔር” መዝ.፹፮፥፫ እግዚአብሔር ማህጸንሽን ከተማ አድርጎ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን የኖረብሽ ሆይ ስለ አንቺ የተነገረው የተደረገው ነገር ዕጹብ ድንቅ ነው እንዳለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የአምላክ እናት ሆና ማረፏ ይደንቃል። ታላቁ የቤተክርስቲያናችን አባት ቅዱስ ያሬድ ሞቷ የሚያስደንቅ መሆኑን «ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ፤ ሞት ለማናቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል» በማለት ገልጾታል።

እንኳን ለእናታችን የዕረፍት በዓል አደረሳችሁ!!

።።።።።። እንካን አደረሰን።።።።።።።። 🌺🌺🌺 ጥምቀት 🌺🌺🌺ጥምቀት የሚለው ቃል አጥመቀ ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም መላ ሰውነትን በተቀደሰ ውኃ መነከር ወይም መዘፈቅ ውሰጥ ...
18/01/2025

።።።።።። እንካን አደረሰን።።።።።።።።
🌺🌺🌺 ጥምቀት 🌺🌺🌺

ጥምቀት የሚለው ቃል አጥመቀ ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም መላ ሰውነትን በተቀደሰ ውኃ መነከር ወይም መዘፈቅ ውሰጥ ገብቶ መውጣት መነከር መውጣት መቀበር ማለት ነው አንድ ሰው በመጠመቁ ክርስቶስን በሞቱ ይመስለዋል ይኸውም ተጠማቂው ከቅዱሱ ውኃ ሲነከር በክርስቶስ ሞቶ ሲመስለው ከውኃ ሲወጣ ደግሞ ክርስቶስን በትንሣኤው ይመስለዋል፤ በዚህም ከክርስቶስ ጋር አንድ ይሆናል፡
ጌታ ለምን ተጠመቀ?
✝ ለአብነት /ምሳሌ/ ለመሆን
✝ ጥምቀታችንን ሊባርክ ለጥምቀታችን ኃይልን ሊሰጥ
✝ ምሥጢራትን ለመግለጽፅ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተጠመቀ ጊዜ ለዘመናት ተሠውሮ የነበረው የአንድነትና የሦስትነት ምሥጢር (ምሥጢረ ሥላሴ) ገሃድ ሆኖ ተሰበከ። ይኸውም ብቻ ሳይሆን የክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት (የአብ ልጅ የድንግል ልጅ መሆኑ) በአብ በመንፈስ ቅዱስ የተመሰከረበት ዕለት ነው ወልድ ክርስቶስ ተብሎ በአካለ ሥጋ አብ በደመና ኾኖ፣ መንፈስ ቅዱስ በርግብ ምሣሌነት ሦስት አካላት በአንድ አምላክነት ተገለፁ። ክርስቶስ የተባለው የድንግል ልጅ እግዚአብሔር አብ ከባሕርይ የወለደው ስለመሆኑም አንዱን ባሕርይ በተዋሕዶ “ልጄ” ብሎ በመጥራቱ ሃይማኖት ታወቀ ተረዳ። የቀናውን ኦርቶዶክስ/ እምነት “ተዋሕዶ” ተብሎ የተጠራውም በዚህ መሠረትነት ነው።

🌺ጌታችን ለምን በ30 ዓመቱ ተጠመቀ?
✝ለካሣ ነው አዳም ከእግዚአብሔር በተፈጠረ በ30 ዘመኑ ያገኘውን ልጅነት በዲያብሎስ በተሠወረበት በከይሲ በእባብ/ ምክር ተታሎ አስወስዶ ነበርና፤ እርሱም በ30 ዘመኑ ተጠምቆ የዲያብሎስን ሥራ አጥፍቶ ልጅነቱን ሊመልስለት በ30 ዘመኑ ተጠመቀ።
✝ ሕግን ለመሥራት ነው በብሉይ ኪዳን ለመንፈሳዊ አገልግሎትና ሕግ ለማድረስ የሚታጩበት የሚመረጡበት/ ከ30 ዓመታቸው ጀምሮ ነበር። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የሕግ ባለቤት እንደመሆኑ ማስተማር የጀመረው በ30 ዕድሜው ነው። በዚህም መነሻነት በሐዲስ ኪዳን ሰዎች ለመንፈሣዊ ተግባር መመረጥ ያለባቸው በዕድሜያቸው ልክ ሙሉ ሲሆኑ ኃላፊነት ለመሸከም በሚችሉበት የዕድሜ ልክ የዕውቀት፣ የብስለት ደረጃ ሲደርሱ መሆን እንዲገባው ጌታችን በተግባር አሳየን፡፡

🌺 ጌታችን ወደ ዮሐንስ ሄዶ ለምን ተጠመቀ ?ጌታችን የዮሐንስ ጌታ፣ ፈጣሪ ነው፡፡ ዮሐንስ አስቀድሞም ስለ እርሱ ሲመሰክር “አንድ ሰው ከእኔ በኋላ ይመጣል ከእኔም በፊት ነበረና ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኗል ብዬ ስለ እርሱ ያልሁት ይህ ነው” ዮሐ 1÷29 “ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣሙ ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል” ማቴ. 3፥11/ በማለት የክርስቶስን ቀዳማዊነት ልዕልና መስክሯል፡፡ ወደ እርሱ ሊጠመቅ በመጣ ጊዜም “እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን? ብሎ ይከለክለው ነበር” ተብሎ ተጽፏል፡፡ /ማቴ 3፥14/
✝ ለትሕትና ጌታችን “ከእኔም ተማሩ ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና” ማቴ. 11፡28
✝ ሥርዓትን ለመሥራት
ጌታችን እንደ ጌትነቱ ቅዱስ ዮሐንስ እርሱ ዘንድ መጥቶ እንዲያጠምቀው ቢያዘው ኖሮ በየዘመኑ የሚነሡ ነገሥታት፣ ባለጠጎች ምእመናን አጥማቂ ካህናትን በቤተ መንግሥታችን፣ በእልፍኛችን መጥታችሁ አጥምቁን ልጆቻችንንም አጥምቁልን ባሏቸው ነበር። ጌታችን ግን ወደ ቅዱስ ዮሐንስ ወዳለበት ባሕረ ዮርዳኖስ ሄዶ በመጠመቁ ምእመናን ካህናት ወደ ተሰየሙበት ቅድስት ቤተክርስቲያን ዘንድ ሄደው እንዲጠመቁ
ምክንያት ሆኖ ሥርዓትን ሠራልን።

✝✝✝ ከጥምቀቱ በረከት ያድለን!! ✝✝✝

እንኳን ለጌታችን በዓለ ልደት አደረሰን እነሆ ለህዝብ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምስራች እነግራችኋለሁ እና አትፍሩ ዛሬ በዳዊት ከተማ እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ መድኃኒት ተወልዶላችሀል ልቃ...
06/01/2025

እንኳን ለጌታችን በዓለ ልደት አደረሰን
እነሆ ለህዝብ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምስራች እነግራችኋለሁ እና አትፍሩ ዛሬ በዳዊት ከተማ እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ መድኃኒት ተወልዶላችሀል ልቃ ፪÷፩፩

እንኳን ለአቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ጵጵስና የተቀበሉበት አመታዊ መታሰቢያ አደረሰን 🌿🌺🌾🌿🌺🌾🌿🌺🌾🌿🌺🌾🌿🌺🌾''ብርሃንን ይገልጥልን ዘንድ ወደ አገራችን የተላከ ይህ ሰው አባታችንና መምህራችን...
26/12/2024

እንኳን ለአቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ጵጵስና የተቀበሉበት አመታዊ መታሰቢያ አደረሰን
🌿🌺🌾🌿🌺🌾🌿🌺🌾🌿🌺🌾🌿🌺🌾
''ብርሃንን ይገልጥልን ዘንድ ወደ አገራችን የተላከ ይህ ሰው አባታችንና መምህራችን ነው ብሎታል፡፡'' ቅዱስ ያሬድ /መጽ.ድጓ/
+++ እንኳን ለታላቁ ሐዋርያ ጻድቅ ኣባታችን ማር ኣቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ጵጵስና የተሾሙበት ለሃገራችን ብርሃን የተገለጸበት አመታዊ ክብረ በዓላቸው በሰላም ኣደረሳችሁ። +++
''የቅዱስ አባታችን ኅሩይ ማር አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ፍሬምናጦስ በታሕሳስ 18 ጵጵስና የተቀበለ ሲሆን ህየወቱ ሁሉ ወንጌል እየሰበከ ያልተጠመቁት እያጠመቀ በተጋድሎ አሳልፏል ።ብርሃነ ወንጌሉን ለሀገራችን ስላበሰረ፤ በብርሃነ ትምህርቱ የተደሰቱ በጨለማው ውስጥ ኖረው በእርሱ አማካኝነት ወንጌሉ የበራላቸው ምዕመናን ከሳቴ ብርሃን በማለት ሰይመውታል ይህም ብርሃን ገላጭ ማለት ነው፡፡
🌿🌿🌿 ቅዱስ ያሬድም ዝንቱ ብእሲ መምህርነ ዘተፈነወ ውስተ ምድር ይከስት ብርሃነ ማለትም ብርሃንን ይገልጥልን ዘንድ ወደ አገራችን የተላከ ይህ ሰው አባታችን እና መምህራችን ነው ብሎታል፡፡ /መጽ.ድጓ/።
🌿🌿🌿ሰአል ለነ ሰላማ አቡነ ወመምህርነ እለ ፅልመት ነበርነ ከሰትከ ለነ ብርሃነ ዜናሁ ለመድሃኒነ፤ አባታችንና መምህራችን አቡነ ሰላማ በጨለማ የነበርን ለኛ የክርስቶስ ብርሃነ ወንጌል አበራህልን፡፡ /አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በሰዓታት/።
🌿🌿🌿አቡነ ተክለ ሃይማኖት እና አቡነ አረጋዊ አባታችን ብለዋቸዋል።
🌿🌿🌿ቅዱስ አትናቴዎስ ክብራቸውን አይቶ ከእግራቸው በታች ዝቅ ብሎ አክብሯቸዋል
🌿🌿🌿ድንግል ማርያም ሰውና እግዚአብሔር የሚያስታርቅ የመከራ ጊዜ ተስፋ ብላዋለች
''የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፥ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው።'' ዕብራውያን 13:7።
አቡነ ሰላማ
🌿🌺🌾🌿🌺🌾🌿🌺🌾
1. የመጀመሪያ የሀገራችን የወንጌል ሐዋርያ ጳጳስ በመሆን የክርስትና ወንጌል ለመጀምሪያ ጊዜ የሰበኩ ከተለያዩ ቋንቋ ወንጌል የተረጎሙ ጠንካራ መሰረት ያላት መንበረ ሰለማ ቤተክርስቲያን መስርተዋል
2የመጀመሪያ የፅዋ ማሕበር በአክሱም መስርተዋል
3.ታቦተ ፅዬን ከድንኳን አውጥተው ትልቅ ቤተመቅደስ አንፀውሏታል
4.አፃፃፋችን ከግራ ወደ ቀኝ በመቀየር አናባቢም በመጨመር አሰተካክለዋል
5.ብዙ ጳጳሳት ኤጲስ ቆጶሳት ካህናት ዲያቆናት ሾመዋል
6. በቃል ኪዳነቸው ላመኑ የመንግስተ ሰማይ ወራሾች እንዲሆኑ ከኣምላክ ቃል ኪዳን የተሰጣቸው ሲሆን ሰማቸው ለጠራ ዝክራቸው ለዘከረ እሰከ 15 ትዉልድ ሊምርላቸው ቃልኪዳን ሰጥቷቸዋል።
''እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል። ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋው አይጠፋበትም።'' ማቴዎስ 10፥40-42።

እንኳን ለእናታችን ባእታ ማርያም አመታዊ መታሰብያ በሰላም አደረሰን።🌺🌺🌺🌿🌿🌿🌺🌺🌺🌿🌿🌿🌺🌺🌺🌿🌿🌿ቅድስት ድንግል ማርያም ከሐና እና ከኢያቄም በፈቃደ እግዚአብሔር ተወልዳ እስከ ሦስት ዓመት ድ...
12/12/2024

እንኳን ለእናታችን ባእታ ማርያም አመታዊ መታሰብያ በሰላም አደረሰን።

🌺🌺🌺🌿🌿🌿🌺🌺🌺🌿🌿🌿🌺🌺🌺🌿🌿🌿
ቅድስት ድንግል ማርያም ከሐና እና ከኢያቄም በፈቃደ እግዚአብሔር ተወልዳ እስከ ሦስት ዓመት ድረስ የኖረችው በወላጆቿ ቤት ነበር፡፡ ከዚህ በኋላ ኢያቄምና ሐና የተሳሉትን ስእለታቸውን አስታውሰው ወስደው ለቤተ እግዚአብሔር ሰጧት፤ ካህኑ ዘካርያስም ስለምግቧ በመጨነቁ ሕዝቡን ሰብስቦ ሳለ መልአኩ ፋኑኤል ኅብስት ሰማያዊ ጽዋዕ ይዞ ከሰማይ ወረደ፤ ዘካርያስ ለእርሱ የመጣ ሀብት መስሎት ታጥቆ እጅ ነስቶ ቢቆም ወደ ላይ ራቀበት፡፡ ከስምዖን ጀምሮ በዚያ የተሰበሰቡት ሰዎችም በተራ ቢሞክሩ በተመሳሳይ ወደ ላይ ራቀባቸው፡፡ ምን አልባት ለእንግዶች የመጣ ሀብት እንደሆነ ብለው ሐና እና ኢያቄም እንዲቀርቡ አደረጓቸው፤ ለእነርሱም ራቀባቸው፤ ዘካርያስም ሐናን ‹‹እግዚአብሔር የሚያደርገውን የሚያውቅ የለምና ልጅቷን ትተሸ ወደዚህ ነይ›› ባላት ጊዜ ቅድስት ማርያም ድክ ድክ እያለች እናቷን ስትከተል መልአኩ ፋኑኤል ወደ እርሷ ቀርቦ አንድ ክንፉን አንጥፎ አንድ ክንፉን ጋርዶ መግቧት ዐረገ፤ ሊቀ ካህናቱም ሕዝቡም የምግቧ ነገር ከተያዘልን በቤት እግዚአብሔር ትኑር ብለው አስገቧት፤ይህም ታኅሣሥ ፫ ቀን ነበር፡፡
ድንግል ማርያምም ሰማያዊ ኅብስትና መጠጥ እየተመገበች ፲፪ ዓመት በቤተ መቅደስ ኖረች፡፡ ፲፭ ዓመት ሲሞላት ግን ለአቅመ ሔዋን በመድረሷ ከቤተ መቅደስ ትውጣልን በማለት አይሁድ በጠላትነት ተነሱባት፡፡ ካህኑ ዘካርያስም ይህን ሰምቶ እመቤታችንን ጠየቃት «ኦ ወለተ እስራኤል እፎ ትፈቅዲ ትንበሪ፤ ልጄ እንደምን ሆነሽ ልትኖሪ ትወጂያለሽ?» አላት፡፡ እርሷም «ከእግዚአብሐር በታች ያለኸኝ አባት አንተ ነህ፤ በዚያውም ላይ እናት አባቴ አደራ ያሉህ አንተን ነው፤ ወደ እግዚአብሔር አመልክትልኝ፤» አለችው፡፡ ዘካርያስም ጸለየ፤ እግዚአብሔርም ከነገደ ይሁዳ ሚስቶቻቸው የሞቱባቸውን በትራቸውን ሰብስበህ በቀዳማይ ሰዓተ ሌሊት ከቤተ መቅደስ አግብተህ ስትጸልይ አድረህ በቀዳማይ ሰዓተ መዓልት አውጣው ብሎ ምልክትም እሳይህአለው ብሎ ነገረው፡፡ እርሱም እንዳለው አድርጎ በማግሥቱ በትሮቹን አውጥተው ቢያዩ የዮሴፍ በትር አብባና አፍርታ ተገኘች፡፡ ከበትሩ ጫፍ ላይ «ኦ ዮሴፍ ወልደ ዳዊት ዕቀባ ለማርያም ፍኅርትከ፤ ዮሴፍ ሆይ እጮኛህ ማርያምን ጠብቃት፤» የሚል ጽሑፍ አገኙ፤ርግብም መጥታ በራሱ ላይ አርፋለች፤ ስለሆነም ዮሴፍ እንዲጠብቃት ተወሰነ፡፡

የእናታችን ፀሎትና ቃል ኪዳን ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን።

⛪⛪⛪ ዮም ተወልደ ከሳቴ ብርሃን⛪⛪⛪እንኳን ለአባታችን ከሳቴ ብርሃን የልደታችው ክብረ በዓል በሰላም አደረሰን! ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ ይህ ፃድቅ የክብር ኮከብ በገድ...
04/12/2024

⛪⛪⛪ ዮም ተወልደ ከሳቴ ብርሃን⛪⛪⛪
እንኳን ለአባታችን ከሳቴ ብርሃን የልደታችው ክብረ በዓል በሰላም አደረሰን! ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

ይህ ፃድቅ የክብር ኮከብ በገድል የተጠመደ ታጋይ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በኋላ በ 245 ዓም በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መቃብር ቦታ የእግዚአብሔር ሀገር እምብርት ማዕከለ ምድር በሆነችው በቅድስት ኢየሩሳሌም ብፁዕ ቅዱስ የሆነ የተመረጠ ማር አባታችን ከሳቴ ብርሃን ሰላማ ሕዳር 26 ቀን ተወለደ። የባቱ ስም ምናጦስ የእናቱ ስም ማርያም ሰናይት ነው። በተወለደበት ቀን ከፀሐይና ከጨረቃ ከከዋክብት ይልቅ ሰባት እጅ የሚያበራ ታላቅ ብርሃን ከሰማይ ወረደ፣ ከብርሃኑም የተነሳ ቀንና ሌሊት አልታወቀም ስለ ልደቱ ክብር ምድር ሰባት ቀን ፈፅማ አበራች። ይህም ህፃን ፍሬምናጦስ ለአብ ስግደት፣ ለወልድ ስግደት፣ ለመንፈስ ቅዱስ ስግደት ይገባል፣ ለአብ ምስጋና ለወልድ ምስጋና ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል ከጨለማ ወደ ብርሃን ላወጡኝ ቅድም ዓለም ለነበሩ ዛሬም ላሉ ዓለምን አሳልፈው ለሚኖሩ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን ብሎ ፈጣሪውን አመሰገነ። ዳግመኛም አሃዱ አብ ቅዱስ፣ አሃዱ ወልድ ቅዱስ አሃዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ አለ። እነዚህን ምሳጋናዎች መንፈስ ቅዱስ አናገረው። በተወለደበት ዕለትም ጌታችን መድኋኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት በሶስትነት ሆኖ ከብዙ አዕላፍ መላዕክት ጋር ወደ እሱ መጣ። እነዚህም መላዕክት ክንፍ ለክንፍ ተያይዘው እየተጋፉ እሱን ለማየት ይጨናነቁ ነበር። ፀሎቱ በረከቱ ከሁላችን የዓለም ህዝብ ጋር ይሁን።

➥እንኳን ለህዳር❷❶ ለእናታችን ለቅድስት ማርያም አመታዊ መታሰቢያ ክብረ በአል አደረሳችሁ አደረሰን!!➝ህዳር ❷❶ቀን➢በዚህ ዕለት ህዳር ❷❶ ቀን አመቤታችን ድንግል ማርያም ታቦተ ፅዮን በፍል...
30/11/2024

➥እንኳን ለህዳር❷❶ ለእናታችን ለቅድስት ማርያም አመታዊ መታሰቢያ ክብረ በአል አደረሳችሁ አደረሰን!!

➝ህዳር ❷❶ቀን

➢በዚህ ዕለት ህዳር ❷❶ ቀን አመቤታችን ድንግል ማርያም ታቦተ ፅዮን በፍልስጥኤም ሀገር በምርኮ በሔደችበት ጊዜ ዳጎን የተባለውን ጣኦት አድቅቃ :አውልቃ የመጣችበት ዕለት ነው::❶ኛ ሳሙ 1:6

➢በዚች ዕለትም ታቦተ ፅዮን ንጉስ ሰሎሞን በክብር ወደሰራላት ቤተ መቅደስ የገባችበት ዕለት ነው ❶ኛ ነገ 8:1

➢በዚች ዕለት ታቦተ ፅዮን በንግስት ሳባ ልጅ በአፄ ሚኒሊክ አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ የገባችበት ዕለት ነው

➢እነ ዩዲት ጉዲት በነገሱበት ዘመን የተሰደደችው እመቤታችን የስደት ጊዜዋን ጨርሳ ወደ ክብር መንበሯ የተመለሰችበት ዕለትን በማሰብ ህዳር ፅዮንን በድምቀት እናከብራለን

➝ ፅዮን ማርያም የተባለችበት ምከንያት

➢አክሱም ፅዮን እደዛሬው ድርቅ ያለ መሬት አልነበረም ባህር ነበር እንጂ ፤አብርሃምና አጽብሃ ለታቦተ ፅዮን ምን አይነት ቤተ ክርሰቲያን ነው የምንሰራላት ? ቦታውስ የት ጋር ነው የሚሆነው ?እያሉ ዘወትር ሲጨነቁ ጌታችን ተገልፆ ድንጋይ ላይ ቆሞ አዩት

➢አክሱም ቤተ ክርስቲያኗን እዚህ ባህር ላይ ስሯት ስሟንም በእናቴ ስም ሰይሟት አላቸው

➢እነርሱም ጌታ ሆይ ይሄ እኮ ባህር ነው ይሉታል በዚህ ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ከገነት አፈር ይዞ መጣና ባህሩ ላይ ነሰነሰው ባህሩም ደረቀ የዛሬውንም ቅርጽ ያዘ ይላል ጌታችን የቆመበት የእግሩ ምልክት ዛሬም ድረስ ይታያል እደሚለው በድርሳነ ጽዮን ላይ

🌿ከእመቤታችን ረድኤት በረከት ያሳትፈን ሀገራችን ና ህዝባችን በፅኑ ሰላም ይጠብቅልን🙌💒☦️❷❶🌿❤️

💐💐💐🌺🌺✞✞✞💐💐💐🌺🌺🌺✞✞✞💐💐💐🌺🌺እንኳን ለታላቁ መልዐክ ለቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አጀረሰን!!💐💐💐🌺🌺✞✞✞💐💐💐🌺🌺🌺✞✞✞💐💐💐🌺🌺ህዳር 12 ቀን ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤ...
20/11/2024

💐💐💐🌺🌺✞✞✞💐💐💐🌺🌺🌺✞✞✞💐💐💐🌺🌺
እንኳን ለታላቁ መልዐክ ለቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም
አጀረሰን!!
💐💐💐🌺🌺✞✞✞💐💐💐🌺🌺🌺✞✞✞💐💐💐🌺🌺

ህዳር 12 ቀን ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በኢዮር ባለችው በአራተኛይቷ ከተማ በሚኖሩት ኃይላት እና በአሥሩ ነገደ መላእክት ላይ አለቃ ሆኖ የተሾመበት ቀን ነው፡፡ እግዚአብሔር ሳጥናኤልን በትዕቢቱ ምክንያት ከሥልጣኑ ገፍፎ ወደ ምድር ሲጥለው ቅዱስ ሚካኤል በእርሱ ቦታ በዐሥሩ ከተማ በመቶውም ነገደ መላእክት ላይ ተሹሟል፡፡(ይህን ሁለተኛውን ሹመት ያገኘው በሚያዚያ 2 እንደሆነ አክሲማሮስ በሚባለው የቤተክርስቲያናችን መጽሐፍ ላይ ሰፍሮ አናገኛለን፡፡)
የቅዱስ ሚካኤል ሹመት በነገደ መላእክት ላይ ብቻ ግን አይደለም ፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሆኑት ላይም ጭምር ነው ፡፡ ይህም እንደሆነ እንድንረዳ በብሉይ ኪዳን የእግዚአብሔር ሕዝብ የተባለውን እስራኤል ዘሥጋን ሲራዳና ሲጠብቅ እንደነበረ ተጽፎልን እናገኛለን፡፡ ለምሳሌ መጽሐፍ ቅዱስ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለኢያሱ በኢያሪኮ ምድረ በዳ እንደተገለጠለት “… ዐይኑን አንሥቶ ተመለከተ እነሆም የተመዘዘ ሰይፍ የያዘ ሰው በፊቱ ቆመ፤ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ “ከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህ? አለው፡፡ እርሱም “እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁንም ወደ አንተ መጥቼአለሁ” (ኢያ.5፡13) ይለናል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ስለ ቅዱስ ሚካኤል እንዲህ አለ "በሰማይም ሰልፍ ሆነ፤ ሚካኤልና መላእክቱም ዘንዶውን ተዋጉት፥ ዘንዶውም አልቻላቸውም፥ ከዚያም በኋላ በሰማይ ቦታ አልተገኘለትም። ራእ 12፤7 ነቢዩ ዳንኤልም እንዲህ አለ "በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል" ዳን ፲፪፥፩። በዚህም የመልአኩ ስልጣን በህዝቡ ላይ በሐዲስ ኪዳንም ፀንቶ እንደሚኖር ነቢዩ ዳንኤል አስቀድሞ ነግሮናል፡፡

እንኳን ለኣባቶቻችን አብርሃ እና አፅብሃ እና ለቅዱስ ዩሐንስ ወርሐዊ መታሰቢያ አደረሰን🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺 #በክርስትና ሕይወትህ ይህን አስተውል 🌹ከሃይማኖት እንዳትስት እነዚህን አድርግ...
12/11/2024

እንኳን ለኣባቶቻችን አብርሃ እና አፅብሃ እና ለቅዱስ ዩሐንስ ወርሐዊ መታሰቢያ አደረሰን
🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
#በክርስትና ሕይወትህ ይህን አስተውል
🌹ከሃይማኖት እንዳትስት እነዚህን አድርግ
•ከሊቃውንት እግር ሥር ተማር
•ለሃይማኖት ቤተሰቦች መልካም አድርግ
•አባቶች ለመረመሩት ነገር ትጋ( ኢዮ ፰፣፰)
🌹እነዚህን አስተባብረህ ያዝ
•እምነትና ምግባርን(ያዕ፪፣፲፰)
•ፍቅር ና ሰላምን
•ትዕግስትና መረጋጋትን
(ዕብ ፲፩፣፮; ፪ቆሮ ፲፫፣፩ ; ዕብ ፲፪፣፩)
🌹ራስህን ከእነዚህ ነገሮች አርቅ
•ታናናሾችን ከመናቅ(ማቴ ፲፣፲፰)
•ከልክህ ማለፍን፣ በሚዛን ማጭበርበርን
• ደሃን መበደልን (ኢሳ ፫፣፲፫)
🌹እነዚህን ዘወትር ልብ በል
•አጥብቀህ ልብህን ጠብቅ
• ለአንደበትህ መዝጊያ አብጅ
•ቁጡነትንና ስሜታዊነትን አስወግድ
(ምሳ ፬፣፳፫; ኤፌ ፬፣፳፱)
🌹እነዚህ ነገሮች ጠብቅ
•በጎ ኅሊና
•ንጹህ ልቡና
•ይቅር ባይ ስብእና
🌹እነዚህን አጥብቀህ ያዝ
• ጥበብን
•ቅድስናን
•እግዚአብሔርን መፍራትን

🌹ይህንን አታድርግ
•በማንም ላይ አትፍረድ (ማቴ፯፣፯)
•በሰው ነገር አትግባ
•የሰውን ሀቅ አትውሰድ
🌹እነዚህ ይኖራሉና አትዘናጋ
•ዕለተ ሞት(ማር፲፫፣፴፭)
• ምጽአት ክርስቶስ(ማቴ ፳፬፣፬)
• ክፉ ዘመን (ዮሐ ፱፣፩)
---------------------------------------

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

እንኳን ቤተ መቅደስ የገባችበት መታሰቢያ በዓል ባእታ ማርያም አደረሰን።❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄የሴም…………………ቸርነትየሳሙኤል……………የሽቱ፡ሙዳይ የዘይት፡ቀንድየእሴይ…………… …ስርየሶሎሞን…...
11/11/2024

እንኳን ቤተ መቅደስ የገባችበት መታሰቢያ በዓል ባእታ ማርያም አደረሰን።
❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄
የሴም…………………ቸርነት
የሳሙኤል……………የሽቱ፡ሙዳይ የዘይት፡ቀንድ
የእሴይ…………… …ስር
የሶሎሞን…………...አክሊል
የዕምባቆም…………ተራራ
የሕዝቅኤል…………ምስራቅ የቤተልሄም፡ህግ፡መውጫ ኤፍራታ
የሲሎንዲስ…………ዕፀ ህይወት
የናሆምን ቁስል፡የምታድን
የዘካርያስ ……………ደስታው
የሚልክያስ፡…………ንፅህት፡አዳራሽ
የነቢያት………ትንቢታቸው
የሀዋርያት…………ሞገሳቸው
የሠማዕታት………እናታቸው
የመላዕክት…………… እህታቸው
የአቤል............................የዋህት የኖህ...............................መርከብ
የጌድዬን..................... .....ፀምር
የኮሬብ.............................ቁጥቋጦ
የአሮን........................... ...በትር
የእስራኤል ........................መና
የአሚናዳብ.........................ስረገላ
የያእቆብ.............................መሰላል
የኤልሳ ..............................ማስሮ
የይሥሀቅ............................በረከት
አቤናዘር የተባለች የረድኤት ድንጋይ.......
የቀርሜሎስ መሰውያ..............
የእግዚአብሔር ደመና............
የእግዚአብሔር ከተማ.........
ጠል የወረደባት እርሻ........
የሊባኖስ እንጨት...........
የተቆለፈች ገነት............
የተዘጋች ምንጭ.........
የታተመች ፈሳሽ.........
የሮማን መብቀያ......
የገነት ምንጭ.....
የሕይወት ጉድጎድ..............እመቤቴ ሆይ....... ............ .......... ........ ..........

የመስቀል ሥር ሥጦታችን
የመዳን ሰንደቅ ዓላማችን
እሙ ለአዶናይ ሆይ እንወድሻለን
ፍቅርዋ በረከትዋ በሁላችንም ላይ ይደርብን

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኣቡነ ሰላማ ማህበር/Mahbere abune selama addis ababa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to የኣቡነ ሰላማ ማህበር/Mahbere abune selama addis ababa:

Share