Halwot Emmanuel Church

Halwot Emmanuel Church Vision
To see the Church that creates a righteous influence in Addis Ababa, through the imitation of Christ Jesus
(2)

በኢትዮጵያ አማኑኤል ኅብረት ቤተክርስቲያን ሀልዎት አጥቢያ
#አድራሻ፦ ወሎ ሰፈር ጎርጎሪዮስ አደባባይ ፊውቸር ታለንት ት/ት ቤት አጠገብ
ACCOUNTS
Berhan Bank- 2600260021701
CBE-1000421805718
Awash - 01352574197600
Emmanuel United Church of Ethiopia Halwot Local Church A.A
Phone Number:- ☎️ +251118407763 ☎️ +251118633493 📱+251 973 422024

24/05/2026
https://www.youtube.com/live/8d8S4Ec8LN8?si=q3Dnag1TvEPp7DkX
24/05/2026

https://www.youtube.com/live/8d8S4Ec8LN8?si=q3Dnag1TvEPp7DkX

🔴የእሁድ ማለዳ | የአምልኮ እና የቃል ጊዜ | በኢትዮጵያ አማኑኤል ኅብረት ቤተክርስቲያን | ሀልዎት አጥቢያ | የቀጥታ ስርጭት| 2026ሀልዎት አማኑኤል ኅብረት ቤ/ክ ለመደገፍ - አቢሲኒያ ባንክ ....

  #ከፓስተር ሀይሉ # መንገዴን እሄዳለሁ📜ዘፍ 19:➪ አይነስውር ሆኖ ከጀመሩት ሩጫ አላቋረጡም።➪  የፈለጉትን ነገር ለማሳካት ሲደክሙ ነበር።➤ ወደ መጣልን ነገር በደንብ መጓዝ አለብን። ➤...
23/05/2026


#ከፓስተር ሀይሉ
# መንገዴን እሄዳለሁ

📜ዘፍ 19:

➪ አይነስውር ሆኖ ከጀመሩት ሩጫ አላቋረጡም።

➪ የፈለጉትን ነገር ለማሳካት ሲደክሙ ነበር።

➤ ወደ መጣልን ነገር በደንብ መጓዝ አለብን።

➤ እግዚአብሔር በዚህ ዘመን ሀይል እና ቅባቱን አዘጋጅቷል።

📜 ኤፌ 6

➤ እግዚአብሔር የፍቃዱን ሚስጥር አስታውቆናል።

➤ በምድር የሚጋፋን አለ... በሰማይ ግን አንዳች ነገር የለም... በክቡር ደሙ አጽድቆናል።

➤ ሙታን ሆነን ሳለን ነው በልጁ ህይወት የሰጠን ።

➤ የቁጣ ልጆች ሆነን፣ የስጋችንን ፍቃድን የምፈጽም የነበርን በእርሱ በኩል ዳንን።

➤ ውሸትን አስወግዱ፣ በቁጣችሁ ላይ ጸሀይ አትግባ፣ መንፈስ ቅዱስን አታሳዝኑ የሚል መልዕክት ያስተላልፋል ጻውሎስ።

➤ ከመናፍስት ጋር መዋጋት እና የጨለማ ስራ ማፍረስ አለብን።

➤ የእምነት፣ የአስተሳሰብ ቀረቤታ ከእግዚአብሔር ጋር ማድረግ አለብን።

➤ አብርሃምን እግዚአብሔር ካለህበት ሀገር ውጣ ብሎ አዞት ነበር።

➤ አብርሃም በአስተሳሰቡ የላቀ ስነበር ይስሀቅን እንኳን ቢሰዋው እግዚአብሔር እንደሚያስነሳው ያምን ነበር።

➤ በሚቀጥለው ዘመን የእግዚአብሔር ክብር የሚታይ ይሆናል።

➤ የምንጠብቀው ጌታ ድንገት ይመጣል።

➤ 📜ኢያ 3:7

➤ እግዚአብሔርም ተአምራት ሲያደርግ ተሳታፊ ነህ ።

➤ እግዚአብሔር አምነህ ስትራመድ ከአንተ አቅም በላይተ ተአምራት ያደርጋል።

➤ የደከማችሁበት ነገር ተአምራት ጎትቶ ያመጣል።


📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜
በኢትዮጵያ አማኑኤል ኅብረት ቤተ ክርስቲያን ሀልዎት አጥቢያ
አድራሻ፦ ወሎ ሰፈር ጎርጎሪዮስ አደባባይ ፊውቸር ታለንት ት/ት ቤት አጠገብ
☎️ +251118633493 📱+251 973 422024

https://youtu.be/ofqzrECs-Tc
22/05/2026

https://youtu.be/ofqzrECs-Tc

ጉዞ | አንድ ሰው ከዳነ በኋላ ይጠፋል ወይስ አይጠፋም? | አምስቱ የምድረበዳ አጢያቶች | Prophet Z...

  📌 ከቤተ ልሔም ምንጭ ውኃ ማን ባጠጣኝ?📖2ተኛ ሳሙ 23 ፥ 13 - 17✍️ሦስቱ የዳዊት ኃያላን ጌታ ኢየሱስን መከተል ምን እንደሆነ ወንጌልን የሰበኩ ሰዎች ናቸው።✍️ ሦስቱ ኃያላን ህይወ...
20/05/2026



📌 ከቤተ ልሔም ምንጭ ውኃ ማን ባጠጣኝ?
📖2ተኛ ሳሙ 23 ፥ 13 - 17
✍️ሦስቱ የዳዊት ኃያላን ጌታ ኢየሱስን መከተል ምን እንደሆነ ወንጌልን የሰበኩ ሰዎች ናቸው።
✍️ ሦስቱ ኃያላን ህይወትን የመስጠት እና የመሰጠት ምልክቶች ናቸው።
📖1ኛ ዜና 11 ፥

📌የተሰጡ ሰዎች ምልክቶች

1/ የጌታቸውን የልብ ጥማት (መሻት)ማርካት ነው።
📖 2ተኛ ጢሞ 2 ፥ 3 - 4
✍️ክርስትና ውትድርና ነው፥ ወታደር የታዘዘውን ነው የሚያደርገው እነዚ ኃያላን ግን የጌታን የልብ ትርታ ለማወቅ ነው የሚሰሩት።
✍️አገልግሎት የሚለካው በእግዚአብሔር የልቡ ትርታ ነው።
✍️ኢየሱስን ከተከተልን አይቀር የልቡን ሀሳብ የምንፈፅም ሰዎች ያድርገን።
✍️ትዛዙን ብቻ ሳይሆን መሻቱን ማወቅ ይሁንልን።

2/ ዋጋ ለመክፈል የጨከነ ነው
✍️የዳዊት ኃያላን ከአቅማቸው በላይ የሚያዩ ሰዎች ናቸው።
✍️የጌታቸውን ፈቃድ ለማወቅ ሳይሆን የጌታቸውን ነገር ለማስቀደም ዋጋ ለመክፈል የጨከኑ ሰዎች ናቸው።
✍️የጌታ ደስታ መለኪያው የጌታ ደስታ ነው።
✍️የንጉሱን ጥማት ለማርካት መሞት ጀግንነት ነው።
📖ሐዋ 20 ፥ 24

3/ እግዚአብሔር የሚቀበለውን መስዋት ማቅረብ
✍️ዋጋ የተከፈለበት መስዋት እግዚአብሔር አክብሮ የተቀበለው ህይወት ነው።
✍️የተሰጠን ህይወት እግዚአብሔር ያከብራል ፣ ይቀበላል።

📖ዮሐ ወ 4 ፥14
📖ት. ኢሳ 55 ፥ 1
📖ዮሐ ወ 7 ፥37

✍️ ጌታ ኢየሱስ ለዘላለም የሚያረካ ውኃ ነው!!
📌የሚጠጡና የሚረኩ ሰዎች እግዚአብሔር ያድርገን።

📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖

በኢትዮጵያ አማኑኤል ኅብረት ቤተ ክርስቲያን ሀልዎት አጥቢያ
አድራሻ፦ ወሎ ሰፈር ጎርጎሪዮስ አደባባይ ፊውቸር ታለንት ት/ት ቤት አጠገብ
☎️ +251118633493📱+251 973 422024

    📜መዝሙር 89:20-35➪ ሰው የእግዚአብሔርን ባሕርይ በትክክል ተረድቶ በእርሱ ላይ መደገፍ ይከብደዋል።➪ የእግዚአብሔር ምሕረት ለመዳን ብቻ ሳይሆን ወደ ፊት እንድንቀጥልም የሚያደርገ ...
18/05/2026




📜መዝሙር 89:20-35
➪ ሰው የእግዚአብሔርን ባሕርይ በትክክል ተረድቶ በእርሱ ላይ መደገፍ ይከብደዋል።
➪ የእግዚአብሔር ምሕረት ለመዳን ብቻ ሳይሆን ወደ ፊት እንድንቀጥልም የሚያደርገ ነው።
👉 "ምሕረት" ማለት ምን ማለት ነው?
1 - ሔሴን ፦ በቀላሉ የማይናወጥ፣ የማይለወጥና ሁኔታዎች የማይቀያይሩት ፍቅር።
2 - ራሒሚም ፦ የእናትና የልጅ አይነት የጸና ትስስርና ግንኙነት ያለው።
➥ጥልቅ የሆነ ርኅራኄ ወይም ምክንያት አልባ ርኅራሄ።
➥ የእግዚአብሔር ምሕረትም እንደዚሁ ነው።
➪ ምሕረት ፦ አቅም ላጣ፣ ተስፋ ለቆረጠ፣ ሰላም ለሌለው ሰው፣ እንዲሁም ውድቀት ውስጥ ላለ ሰው ከእግዚአብሔር የተሰጠ ስጦታ ነው።
➥ ሳንጠይቅ ከእግዚአብሔር የተገኘ ስጦታ ነው።
➥ ይህ ስጦታ የሚያስፈልገንን ነገር ሁሉ ይዞልን መጥቷል።
➥ ለማይገባው ሰው የሚሰጥ ነው።
👉 ድካም ውስጥ ላላችሁ የእግዚአብሔር ምሕረት አለላችሁ።
➪ ከእግዚአብሔር ምሕረት ቀጥሎወደ እኛ ማዳን አለ።
➪ እግዚአብሔር ሰውን የሚምረው ባህሪው ስለሆነ ነው።
➪ የእግዚአብሔር ባሕርይ በሁኔታዎች የሚቀያየር አይደለም።
➪ እግዚአብሔር በምሕረቱ እጅግ ባለጸጋ ነው።
👉 የእግዚአብሔር ምሕረት በእነዚህ አራት ነገሮች ይገለጣል
1 - በጸና ፍቅሩ
2 - በርኅራኄው
3 - በቅድስናው
4 - ቃሉን በመጠበቅ
➪ እግዚአብሔር የሚረሳ አምላክ አይደለም ነገር ግን በደላችንን ፈቅዶ ይረሳል።
👉 የእግዚአብሔር ምሕረት የተገለጠበት አራት ነገሮች፦
1 - መስቀል
📜 ቲቶ 3:5
➪ መስቀል ትልቁ የምሕረት መገለጫ ነው።
➥ ከሞት፣ ከኃጢአት፣ ከሰይጣን ቀንበር አድኖናል።
📜 ኤፌሶን 2:4
➥ ምሕረቱ የእግዚአብሔር ጠላትና የቁጣ ልጆች ለነበርን ለእኛ የተገለጠ ነው።
➪ እግዚአብሔር ምሕረቱን በመስቀል ሲገልጥ ፍርድን ፈጽሟል/ፍርድ ተደርጎ/ለእኛ ደግሞ ምሕረት አድርጎልናል።
➪ እውነትና ምሕረት ሲስማሙ ለእኛ ወደ አብ መግባት ሆኖልናል።
2 - መታደስ
➪ ለደከመውና ለዛለ ሰው የእግዚአብሔር ምሕረት መታደስን ያደርጋል።
➪ በቃኝ፣ ጨረስኩኝ ላይ ላለ ሰው እግዚአብሔር ምሕረቱን ይገልጣል!
➪ በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ላላችሁ ሰዎች እግዚአብሔር ምሕረቱን ያደርግላችኋል!
➪ ሳምሶን "እግዚአብሔር ሆይ አስበኝ" ሲል እግዚአብሔር አስቦታል።
➪ የእግዚአብሔር ምሕረት ያድሰናል (ያነሳናል)።
3 - መኖርያ የሆነ (ለመኖር የሚሆን)
➪ እግዚአብሔር ያለን /የተናገረን/ ቦታ ለመድረስ የእግዚአብሔር ምሕረት ያስፈልገናል።
➪ በደከመንና ባቃተን ነገር ላይ የእግዚአብሔር ምሕረት እንድንሄድና እንድንቀጥል ያደርገናል።
➪ እግዚአብሔር በእኛ ተስፋ ስለማይቆርጥ ነገን ያሳየናል።
📜መዝሙር 135
➥ የእግዚአብሔር ምሕረት ለዘላለም ነው።
➪ እስራኤላውያን በምድረ በዳ እንዲቀጥሉ ያደረጋቸው የእግዚአብሔር ምሕረት ነው።
➪ የእግዚአብሔር ምሕረት የሚያራምድ ፣ የሚያስኬድና የሚያስቀጥል ነው።
➪ የዕለት ተዕለት ኑሯችን ላይ የእግዚአብሔር ምሕረት ያስፈልገናል።
📜ሰቆቃው ኤርምያስ 3:22
➥ ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው። ርኅራኄው አያልቅምና!
👉 የእግዚአብሔር ምሕረት ከፊት ለፊታችን ዘወትር ይቅደምልን።
➪ ዳዊት ደጋግሞ "እግዚአብሔር ሆይ ምሕረትህን" ብሏል።
➥ ምክንያቱም ምሕረቱ በደንብ ስለገባው ነው።
➪ ያልራቀ ምሕረት ከዳዊት ጋር ነበረ።
➥ ምክንያቱም እግዚአብሔር ለዳዊት ቃል ገብቶለት ስለነበር ነው።
➪ ምሕረት የሌለው ሰው ሞገስ አልባ ነው።
➥ ንጉሥ ሳኦል የእግዚአብሔር ምሕረት ተወስዶበት ስለነበረ ሞገስ አልባ ሆኖ ነበረ።
➪ ለዳዊት የተገባለት ኪዳን ለእኛም በመስቀል በኩል ቤታችን ገብቷል!
➥ ከዚህ ምሕረት የተነሣ የእግዚአብሔር ባለጠግነት እንድናይ አድርጎናል።
➥ የፍቅሩን መጠን በምሕረቱ በኩል እንድናይ አድርጎናል።
➪ ለዳዊት የተገባው ኪዳን ምሕረቱን እንዳበዛለት ሁሉ፣ ለእኛም በመስቀል በኩል እንዲሁ ሆኖልናል።
➪ የእግዚአብሔር ምሕረት ከሌለ ነገን ማየት አንችልም።
➪ በእግዚአብሔር ምሕረት የተከበበ ሰው ሁሉን ነገር ማለፍ ይችላል።
👉 በዘመናችሁ ይህ ይሁን
➥ እግዚአብሔር ምሕረቱን ከእናንተ አያርቅ!
➥ እግዚአብሔር ምሕረቱን ከቤታችሁ አያርቅ!
➥ እግዚአብሔር ምሕረቱን ከልጆቻችሁ አያርቅ!
➥ እግዚአብሔር ምሕረቱን ከልጅ ልጆቻችሁ አያርቅ!
አሜን 🙏
📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜
በኢትዮጵያ አማኑኤል ኅብረት ቤተ ክርስቲያን ሀልዎት አጥቢያ
አድራሻ፦ ወሎ ሰፈር ጎርጎሪዮስ አደባባይ ፊውቸር ታለንት ት/ት ቤት አጠገብ
☎️ +251118633493 📱+251 973 422024

  ሀልዎት_ቴሌግራም_ፋሚሊን_ለመቀላቀል! 👇https://t.me/+jYFLz5UZB4k0ZDA0ሀልዎት_ቴሌግራም_ቻናልን_ለመቀላቀል👇https://t.me/halwotchurch🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐...
18/05/2026



ሀልዎት_ቴሌግራም_ፋሚሊን_ለመቀላቀል! 👇
https://t.me/+jYFLz5UZB4k0ZDA0
ሀልዎት_ቴሌግራም_ቻናልን_ለመቀላቀል👇
https://t.me/halwotchurch
🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐
🖐 የእግዚአብሔር ምህረት፤ የእግዚአብሔር ቸርነት፤ የእግዚአብሔር ደግነት በምድሬ፤ በሕዝቤ፤ በአገሬ እንዲሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እባርካለሁ፣
🖐 ምድራችን ምህረት የበዛላት፣ የገነነላት እንድትሆን፣ በእግዚአብሔር ምህረት፣ በእግዚአብሔር ደግነት፣ በእግዚአብሔር ቸርነት ስራዎቿ ወደ ፍጻሜ የሚመጡበት እንዲሆን፣ እግዚአብሔር የትኛውንም የምድሪቷን ሁኔታ በምህረት የተከናወኑ፣ የተሳኩ እንዲያደርግ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ምድራችንን ባረኩ
🖐 እግዚአብሔር ምድራችንን፤ አገራችንን ይባርክ፣ አብያተ ክርስቲያናትን ይባርክ፣ የእግዚአብሔር ምህረት፤ የእግዚአብሔር ቸርነት፤ የእግዚአብሔር ደግነት፤ የእግዚአብሔር ጣልቃ ገብነት፣ የእግዚአብሔር የፍቅርና የቸርነት ውጤት በሆነው በእግዚአብሔር ጸጋ፤ በእግዚአብሔር አይን የሚታይ እንዲሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ምድሬንና ህዝቤን ባረኩ
🖐 በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናንተን ጌታ ኢየሱስ ይባርካችሁ፣ ወንዶችን፤ ሴቶችን እግዚአብሔር ይባርክ፣ በመንገዳችሁ፤ በሕይወታችሁ የእግዚአብሔር በረከት፤ የእግዚአብሔር ምህረት፤ የእግዚአብሔር ቸርነት፤ የእግዚአብሔር ደግነት፤ የእግዚአብሔር ምህረት እንደገና ይግነንላችሁ፣ እግዚአብሔር ምህረቱን አገነነልኝ፤ እግዚአብሔር ስኬትን ሰጠኝ፤ እግዚአብሔር በዚህና በዚያ አሳካልኝ፤ እግዚአብሔር ማረኝ፤ እግዚአብሔር አከናወነልኝ ስትሉ የእግዚአብሔር ምህረት መገለጫ እንድትሆኑ በኢየሱስ ስም ባረኳችሁ
🖐 እግዚአብሔር ይባርካችሁ፣ እግዚአብሔር ይቀድሳችሁ፣ ፊቱን ያብራላችሁ፤ የእግዚአብሔር ክንድ፤ የእግዚአብሔር እጅ፤ የእግዚአብሔር ጣት አሁንም ከእናንተ ጋር ትሁን
🖐 እግዚአብሔር ምህረቱን፤ ቸርነቱን፣ ፍቅሩን፤ ደግነቱን እንደገና በመንገዳችሁ፤ በሕይወታችሁ፤ በራዕያችሁ፤ በህልማችሁ፤ በጸሎታችሁ፤ በልጆቻችሁ፤ በቤታችሁ፤ በስራችሁ ሁሉ ላይ እግዚአብሔር ይገለጥላችሁ
🖐 የእግዚአብሔር ምህረት፤ የእግዚአብሔር ቸርነት፤ የእግዚአብሔር ደግነት በዙሪያችሁ ይሁንላችሁ
🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐
በኢትዮጵያ አማኑኤል ኅብረት ቤተ ክርስቲያን ሀልዎት አጥቢያ
አድራሻ፦ ወሎ ሰፈር ጎርጎሪዮስ አደባባይ ፊውቸር ታለንት ት/ት ቤት አጠገብ
☎️ +251118633493 📱+251 973 422024

Address

Halwot Emmanuel United Church
Addis Ababa

Telephone

+251973422024

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Halwot Emmanuel Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Halwot Emmanuel Church:

Share

Category