28/09/2023
ነቀምቴ መካነየሱስ 100 ዓመት ሞላት...
"ጊዜው 1924 ዓ.ም በፈረንጆቹ አቆጣጠር ነበር ከ100 ዓመት በፊት ንጉሥ ኩምሳ ሞሮዳ ሞተው ልጃቸው ደጃዝማች ሀብተማርያም የሌቃ ነቀምቴ ንጉሥ የሆኑበት ወቅት ።
ኦኔሲሞስ እግሩ ነቀምቴን ከረገጠ 20 ዓመት ሞላዉ።
የሲውዲን ዜጋ የሆኑት ዶ/ር ሴደስትሮም እና ባለቤታቸው ነቀምቴ መኖር ከጀመሩ ሁለት ዓመት አስቆጥሯል ።
ቄስ ማርቲን ፎርድፌልት እና ባለቤታቸው እንድሁም ቄስ ኦሎፍኤሪክሴን ከጥቅት ቀናት በፍት ከሲውዲን ሃገር ነቀምቴ ገብተዋል። ሁሉም የነቀምቴ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያንን ምረቃ በጉጉት እየተጠባበቀ ነዉ። ሲጠበቅ የነበረውም ቀን ደረሰ ታህሳስ 25,1924 ዓ.ም በፈረንጆች አቆጣጠር የክርስቶስ ልደት ቀን።
የነቀምቴ መካነየሱስ ቤተክርስቲያንም በዚሁ ዕለት ተወለደች ። በዚህ ታሪካዊ ሥነሥርዓት ለመታደም 150 የሚሆኑ ምዕመናን ቦታቸውን ይዘው ተቀምጠዋል። ፕሮግራሙም ጀመረ ቄስ ኦሎፍ ኤርክሰን ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ጌታን ከአመሰገኑ በሃላ አጭር ንግግር በማድረግ ፕሮግራሙን ከፍተው በመምራት ቀጠሉ። የዕለቱን ቃል ግን ያካፈሉት ዶ/ር ኤሪክ ሴዴስትሮም ሲሆኑ የስብከቱም ሪዕስ "በበረት የተወለደው ህፃን" የሚል ነበር ።ኦኔሲሞስ ደግሞ ቆሞ ወደ አፋን ኦሮሞ እየተተረጎመ ነው። የፀሎት ፕሮግራሙም ከተፈፀመ በሃላ ከቤተክርስቲያኗ ደጅ በሚገኘው ሰፊ አደባባይ ለሁሉም ምዕመናን ምግብና የሚጠጣ ቀርቦ ትልቅ ግብዣ ተደረገ..."
የነቀምቴ መካነየሱስ ማህበረ ምዕመናን ከጥቂት ወራት በሃላ ይሄው 100ኛ ዓመቷን ልታከብር ነው።
እንኳን ደስያላችሁ!!! እንኳን ደስያለን!!
(Adapted from: Aren, Gustav. Envoys of the Gospel in Ethiopia: In the Steps of the Evange
Via Robsan Mako , September 2023
http://www.youtube.com/channel/UCt3blVWzKDJpTAsZvVRNr-g?sub_confirmation=1