Pastor Eshetu Worike/ Ethiopian Pentecostal Churchs Fellowship

Pastor Eshetu Worike/ Ethiopian Pentecostal Churchs Fellowship Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Pastor Eshetu Worike/ Ethiopian Pentecostal Churchs Fellowship, Religious organisation, Addis Ababa.

This Page Is Ethiopian Pentcostal Churches Fellowship page የኢትዮጵያ ፔንቴኮስታል አብያተክርስቲያናት ኅብረት በ1986ዓ.ም በመንግስት የተመዘገበ እና እውቅና ያለው ሆኖ በአዋጅ የተቋቋመው የወንጌል አማኞች ካውንስል መስራች አባልም ነው ከእኛ ጋር የጌታን ስራ አብሮ ለመስራትና ለመደገፍ ለምትፈልጉ:- አድራሻ +251911235932/ AccNo CBE1000267948187

ከፓስተር እሸቱ ወርቄ ማስታወሻዎች በጥቂቱ
09/01/2026

ከፓስተር እሸቱ ወርቄ ማስታወሻዎች በጥቂቱ

የወንጌል አማኞች አ/ክ ካውንስል ጽ/ቤት ባዘጋጀው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት ክብረ በአል ላይ ሁላችሁም እንድትገኙ በአክብሮት እናሳስባለን።ከፔንቴኮስታል አ/ክ ኅብረትአዲሰ አበባ
02/01/2026

የወንጌል አማኞች አ/ክ ካውንስል ጽ/ቤት ባዘጋጀው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት ክብረ በአል ላይ ሁላችሁም እንድትገኙ በአክብሮት እናሳስባለን።

ከፔንቴኮስታል አ/ክ ኅብረት
አዲሰ አበባ

🔴  ከአጭበርባሪዎች ተጠንቀቁ       "Beware of  Fraudsters"ለኢትዮጵያ ፔንቴኮስታል አብያተክርስቲያናት ኅብረት አባላት ሁሉና ለሌሎችም:-የሩቅ ምስራቅ አለም ኢንተርናሽናል ቸር...
12/12/2025

🔴 ከአጭበርባሪዎች ተጠንቀቁ
"Beware of Fraudsters"

ለኢትዮጵያ ፔንቴኮስታል አብያተክርስቲያናት ኅብረት አባላት ሁሉና ለሌሎችም:-

የሩቅ ምስራቅ አለም ኢንተርናሽናል ቸርች
በሚል ከኅብረቱ የወጣ ደብዳቤ በሚመስል የማጭበርበር ስራ እየተሰራ መሆኑን ደርሰንበታል። ትምህርት እናስተምራለን በሚል ገንዘብ ገቢ አድርጉ በማለት አባሎቻችንን እየጠየቁ ስለሆነ እንድታውቁት እና እንድትጠነቀቁ እናሳስባለን።

🔴 የኢትዮጵያ ፔንቴኮስታል አብያተክርስቲያናት ኅብረት የማያውቀው ነው ።🙅‍♂️🙅‍♂️

እናንተ hacker አጭበርባሪዎች ይህንን ማጭበርበራችሁን እንድታቆሙ በእግዚአብሔር ስም እናዛችኋለን።
እግዚአብሔር ይገስፃችሁ።

እሸቱ ወርቄ ፓስተር
ከኢት.ፔንቴኮስታል አ/ክ ኅብረት

04/08/2025

👉 በመንፈስ ቅዱስ ተሞላ🔥🔥🔥🔥🔥

" መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና፤"
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5:18)

በኤፌ.5፥18 ጳውሎስ ሁለት የትእዛዝ ቃሎችን ይሰጠናል የመጀመሪያው ተቃራኒ ወይንም አሉታዊ ነው። "በወይን ጠጅ አትስከሩ "።

ሁለተኛው አዎንታዊ ነው "በመንፈስ ተሞላ" ብዙ ክርስቲያኖች መጠጣት ትክክል እንዳልሆነ ያምናሉ።

ስንት ሰዎች ናቸው እንዲሁ በመንፈስ ቅዱስ🔥🔥🔥 ያለመሞላት ትክክል ያለመሆኑን የሚያምኑ።

🔥 በመንፈስ ቅዱስ መሞላት በጣም ጠቃሚ የሆነ እና በድል ለመኖር እንድንችል እንዲረዳን ዘንድ እግዚአብሔር አብ የሰጠን ስጦታ ነው።

💥ሐዋርያው ጳውሎስ መሞላቱ ተከታታይ የሆነና የማያቋርጥ መሆኑን ለመግለጽ ሁልጊዜ መንፈስ ይሙላባችሁ ይላል።
የሚናገረውም ስለ አንድ ጊዜ ልምምድ ሳይሆን ስለ ህይወት አኗኗር ነው።

👉 ባለማቋረጥ ምስጋና ለጌታ ማቅረብ
👉 ባለማቋረጥ ለእግዚአብሔር አብ ምስጋና ማቅረብ
👉 ራስን ዝቅ በማድረግና በትህትና አንዱ ለሌላው መገዛት

🔥🔥መንፈስ ቅዱስ በዚህ መንገድ ባለማቋረጥ ሲሞላን አጋንንት በሰውነት ክፍሎቻችን የሚቀመጡበት ባዶ ቦታ አያገኙም። 🙅‍♂️🙅‍♂️🙅‍♀️🙅‍♀️

ኢት.ፔንቴኮስታል ኅብረት✍️✍️

08/10/2023

ቃሉን እንዳለ.......

ወደ ሐዋርያዊነት እና ነቢይነት ቢሮ እየገቡ እና ተልዕኮ እየተቀበሉ ያሉ እየበዙ መምጣታቸው ጌታን ለሚወዱ ደስታ ሲሆን በአንፃሩ ደግሞ አንዳንዶችን እያስቆጣቸው ነው።

የክርስቲያኖችም ሆነ የወንጌል ጥሪ የተቀበሉ ዋና ተግባር ጌታ ኢየሱስን ከሰማይ ያወረደ የነፍሳት መዳን በመሆኑ የእኛም ዋና ተልዕኮ ለእግዚአብሔር መንግሥት ሰዎችን ለማዘጋጀት መረባረብ መሆን አለበት።

💥ሐዋሪያነት መላክ ሲሆን ተልዕኮውም ሰውን ሁሉ ለእግዚአብሔር መንግሥት ማዘጋጀት ነው።
ቀድሞ በሐዋርያት ዘመን ሲካሄድ የነበረው የመንፈስ ቅዱስ የኃይል አገልግሎት ዛሬም ላይ ይሰራል።
በአንዳንድ ቤተ እምነት ለምን እንደጥንቱ አይሰራም❓
በአጭር ቃል ከመጀመሪያዎቹ ሐዋርያት ሞት በኋላ በዚያው አብቅቶለታል የሚል አስተሳሰብ ስላለ ይመስላል ይህም አስተሳሰብ ከውጪው አገር ከወንጌል አገልግሎት ጋር ወደ እኛ የመጣ ሃሳብ መሆኑ ነው።

🔥የመንፈስ ቅዱስ የፀጋ አገልግሎት አላበቃለትም ዛሬም ይሰራል። ወደፊትም ጌታ ወደዚህ 🌍ዓለም እስኪመለስ ይሰራል።

🔥መንፈስ ቅዱስ ኃይል ብቻ ሳይሆን ህልውና ያለው አምላክ ነው።
ኃይል ይሰጣል፣ያጠምቃል፣ይሞላል፣
በእምነታችን ፀንተን እንድንቆም ይረዳናል፣የፀጋ ስጦታዎችን እያከፋፈለ ይሰጣል።
ለዚህ የሐ.ሥራ 1፥8 ን ከዚያም ምዕራፍ 2 ን ደጋግሞ ማንበብ ያስፈልጋል።
(የሐዋሪያት ሥራን ሁሉንም መደጋገም)
እንዲሁም ዕብ 13፥8 ማየት ነው።
⛪ቤተክርስቲያን ያለ መንፈስ ቅዱስ የኃይል አገልግሎት ቃል ብቻ ትሆንና ጌታንም እንደሚገባ ልታውቀው አትችልም።
የሕይወት ለውጥ ለጌታ በተቃጠለ ፍቅር ጌታን ማገልገልም ሊኖር አይችልም።

እንደውም ይህንን የኃይል አገልግሎት ያለመቀበል ብቻ ሳይሆን ተቃዋሚ ትሆናለች የጌታ ስራም እንዳይሰፋ እንዳይበዛ ለቤተክርስቲያን እድገትም እንቅፋት ልትሆን ትችላለች።

ይህ እንግዲ ባለፈው ያየነው እና አሁንም እየሆነ ያለ ጉዳይ ነው።
ሐዋሪያትና ነቢያት ማለት መላክ ማለት ሲሆን የተትረፈረፈ ፀጋ ያላቸው ሆነው በጌታ ፍቅር የተሞሉ የቤተክርስቲያን አደራጅ ማለት ነው።

💥የነቢያት አገልግሎት የእግዚአብሔር አፍ በመሆን ለአካሉ ለቤተክርስቲያን መልእክት 🗨️ አምጪዎች ሲሆኑ በጌታ ፍቅር የተሞሉ ሁነው የክርስቶስን አካል ቤተክርስቲያንን የሚያገለግሉ ናቸው።

እግዚአብሔር በነቢያት ይናገራል።

💥ፓስተሮች/መጋቢዎች ለቤተክርስቲያን የተሰጡ ሲሆኑ አካሉን የሚመግቡ፣የሚገነቡ፣ አቅጣጫ የሚያሲዙ፣፣የሚያስተምሩ፣የሚጠብቁ፣ የሚመልሱ ሆነው በፍቅር የተሞሉ ናቸው።
ይኸውም መለያቸው ነው።

💥የሐዋሪያት እና የነቢያት የሌሎቹም ጥንት አብሯቸው የነበረው ቅባት ዛሬም ይሰራል።

💥የሐዋርያት እና የነቢያት የአገልግሎት ቅባት በሁሉም ቤተ እምነቶች ሊሰራ ይችላል።

ምንም እንኳን ሰዎች ከነቅባቱ በኤፌሶን 4 እንዳለ ለቤተክርስቲያን ለአገልግሎት የሚሰጡ ቢሆንም ቅባቱ በተቀበሉ በሁሉም ክርስቲያኖች ሊሰራ ይችላል።

በየ ቤተ እምነቱ ሰዎች በግልፅ ሐዋሪያት ነቢያት ተብለው የሚጠሩ ባይኖሩም ቅባቱ አለ ይሰራል። ይህ ማለት የመንፈስ ቅዱስ የኃይል አገልግሎት ዛሬም እንደሚሰራ አምነው በተቀበሉት መሃል ይከናወናል ለማለት ነው። 👉በአጋንንት የተያዙ ነፃ ይወጣሉ
👉አማኞች በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ይጠመቃሉ ይሞላሉ።
👉ህሙማን ይፈወሳሉ ወዘተ ይህ እንግዲህ ቅባቱ ይሰራል። ዛሬም አለ ማለት ነው።

የቀድሞቹ ሐዋርያት ነቢያት ሌሎቹም አልፈዋል። ስጦታውና ቅባቱ አላለፈበትም። ዛሬም ይሰራል ድንቅና ተአምራት ይካሄዳል።

❓ይህንን የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ካልተቀበልንና ዛሬም እንደሚሰራ ካላመንን የክፋት መናፍስትን እንዴት መቃወምና መቆጣጠር ይቻላል❓

ቃሉስ እንል ይሆናል እውነት ነው ግን እኮ ቃል ብቻ ይሆናል ፊደል ይገላል።

እንደ እውነቱ ከሆነ በጌታ ቃልም ሆነ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በሁለቱም የተካንን መሆን ይገባናል።

ጌታ ኢየሱስ በምድር🌐 ላይ ካገለገለባቸው ጊዚያት ጀምሮ የሐዋሪያትና የነቢያት የሌሎቹም የመንፈስ ቅዱስ የቅባት አገልግሎት እስከዛሬ የቤተክርስቲያን አካል ሆኖ ቆይቷል ይቀጥላልም።

👉ዛሬስ በቀጣይስ ያለዚህ ስጦታና ያለ መንፈስ ቅዱስ ኃይል እንዴት ማገልገል እንችላለን🤔❓

በመንፈሳዊ እውቀት በቲኦሎጂ ትምህርት ጭንቅላታችን አብጦ እንደ ልጅ ማሰብ አቅቶን በጌታ ቃል ላይ እየተፈላሰፍን ይሆን❓

መጽሐፍ ቅዱሳችን ማንኛውም ሰው አንብቦ የሚረዳው ሆኖ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የተፃፈ የሕይወት ቃል እንጂ የምንፈላሰፍበት አይደለም።

👉የሕይወት ቃል ነዉ።

ጌታ ኢየሱስ እኔን ያገኘ ሕይወት አገኘ አለ።
አላማውም ይኸው ነው።
በእውነቱ አንዳንዶች በእልከኝነት ከጌታ ቃል ጋር መዋሃድ አቅቶአቸው ይሆን❓
ጌታ ይርዳን።

ለማንኛውም አንዳንዶቻችን እስክንስተካከል ወይም እስኪገባን ባንቃወም ዝም🤭
ብንልስ❓

እሸቱ ወርቄ ፓስተር
የፔንቴኮስታል ኅብረት ፕሬዚዳንት

ውሸት ሲደጋገም እውነት ይመስላልሜጀር ነቢይ ዩበርት ኤንጅል🔥🔥 (Major Prophet Ubert Angel)🔥🔥ወደ አገራችን  መጥቶ ለአንድ ቀን አገልግሎ ከሄደ በኋላ አንዳንድ በሶሻል ሚዲያ ...
04/10/2023

ውሸት ሲደጋገም እውነት ይመስላል

ሜጀር ነቢይ ዩበርት ኤንጅል🔥🔥
(Major Prophet Ubert Angel)🔥🔥
ወደ አገራችን መጥቶ ለአንድ ቀን አገልግሎ ከሄደ በኋላ አንዳንድ በሶሻል ሚዲያ እየሰማን ያለው ነገር ጭንቁር ሆኖብናል።
ይህችንም ማስታወሻ ለመፃፍ ፈፅሞ አላሰብኩም ነበር
እንደው እንዲህ ዓይነቱን ያልተጨበጠ ወሽካታ ወሬና በእግዚአብሔር ለወንጌል አገልግሎት የተጠሩ እጅግ ጌታ የሚጠቀምባቸውን አገልጋዮች ስም ማጠልሸት መቃወም መሳደብ ሌላም መቼም ከጌታ ነው ማለት አንችልም።
ለመሆኑ እንደዚህ አይነት ሞራል የጎደላቸውን ሃይ የሚል የለም ወይ❓
ለዚህም ነው ይህችን አጭር ማስታወሻ ለመፃፍ የተነሳሳሁት።
መጽሐፍ ቅዱስ እኮ እንደ ባህር ነው።
እኔና እናንተ የአንድ አገር ዜጎች ስንሆን ያወቅነው እጅግ እጅግ ትንሽ ነው
ከመቶ 5% ሲሆን በህይወታችን ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት ተማሪዎች ነን።
ለመሆኑ አወቅሁ ብለን ነው ከጌታ ጋር እና ጌታ ከቀባቸው አገልጋዮች እየተጋጨንና የጌታን ስራ ለማፍረስ ሙከራ እያደረግን ያለነው❓
በእውነት ለጌታ ቀንተን ወይስ ሌላ❓❓
💥እግዚአብሔር የተቀቡ ነቢያትን አስነሳ
💥ሰይጣን ደግሞ ተቃዋሚዎችን አስነሳ
እባካችሁ ለጠላት ሰይጣን መጠቀሚያ አንሁን። የእሱንም ተግባር አናካሂድ።
💥 በአጭር ቃል ባህር ከሆነው ከመጽሐፍ ቅዱስ አንድ ቃል ብቻ ልጥቀስ
💥እግዚአብሔር ፍቅር ነው።
እኔ እዚህም ሆነ ከኢትዮጵያ ውጪ እንዳየሁት Major Prophet Ubert Angel የተቀባ ምንም ስህተት የሌለበት የእግዚአብሔር ሰውና አገልጋይ ነው።

እባካችሁ ለማንኛውም ጉዳይ አንቸኩል።
እንደ መንፈሳዊ ሰው የሚመክር የሚጸልይ የፍቅር ሰው እንሁን።

ጌታ ለስራው ይጠነቀቃል።

💥ሁሉ በፍቅር ይሁን

እሸቱ ወርቄ ፓስተር
የፔንቴኮስታል ኅብረት ፕሬዚዳንት

Don't Miss It🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
27/09/2023

Don't Miss It🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥

05/05/2023

ለአብያተክርስቲያናት ሁሉም ከ1998ዓ/ም ጀምሮ የአምልኮ መሬት እንዲሰጠን ጥያቄ
በፓስተር እሸቱ ወርቄና በጓደኞቹ ሲከታተሉ የነበረው ጥያቄው አ.አ ከተማ አስተዳደር ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ እና የቀድሞ መንግሥት ባለስልጣናት ዘንድ ስንከታተል የነበረው በ2010ዓ/ም ተፈቅዶ ይኸው ባለፈው ዓመትና በዚህ በሚያዝያ ወር 2015ዓ/ም በአ.አ ከተማ አስተዳደር በኩል ተግባራዊ ሆኖልናል።

በቀጣይ ያጋጠመንን ሁሉንም በዝርዝር እናቀርባለን።

ስለተደረገልን እግዚአብሔር አምላካችንን እናመሰግናለን።
እንዲሁም መንግሥታችንንም እናመሰግናለን።

እሸቱ ወርቄ ፓስተር
የፔንቴኮስታል ኅብረት ፕሬዚዳንት
(ከጓደኞቹ ጋር )
አዲስ አበባ

የስብሰባ  ጥሪለኢትዮጵያ ፔንቴኮስታል አብያተክርስቲያናት ኅብረት አባላት በአዲስ አበባም ሆነ ከአዲስ አበባ ውጪ በየአቅጣጫው የቤተክርስቲያን የወንጌል አገልግሎት እያካሄዳችሁ ለምትገኙ ሁሉየጌ...
05/04/2023

የስብሰባ ጥሪ

ለኢትዮጵያ ፔንቴኮስታል አብያተክርስቲያናት ኅብረት አባላት በአዲስ አበባም ሆነ ከአዲስ አበባ ውጪ በየአቅጣጫው የቤተክርስቲያን የወንጌል አገልግሎት እያካሄዳችሁ ለምትገኙ ሁሉ

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ይብዛላችሁ እያልን
ማክሰኞ ሚያዚያ 03/2015ዓ.ም ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ የትንሳኤን በአል ምክንያት በማድረግ የአንድነት የአምልኮ ጊዜ ከሜክሲኮ አደባባይ ዝቅ ብሎ ሳርቤት አጠገብ በሚገኘው ETC ስብሰባ አዳራሽ የካውንስሉ ቢሮ ባዘጋጀው ስብሰባ እንድትገኙ በአክብሮት ጥሪ እናስተላልፋለን።

ከፔንቴኮስታል ኅብረት ጵ/ቤት

Address

Addis Ababa

Telephone

+251911235932

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Pastor Eshetu Worike/ Ethiopian Pentecostal Churchs Fellowship posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share