21/08/2026
* *
ኪዳነ ምህረት እመቤት እመቤት(፪)
ነይልን ነይልን ካለንበት (፪)
ከሰማያት በላይ ካለው ከማደሪያሽ(፪)
ዝማሬ ከሞላው ከዘላለም ቤትሽ
የምድር ፍጥረታት ማርያም ማርያም ሲሉሽ(፪)
የቃል እናት እመቤቴ ነይ በሰረገላሽ(፪)
አዝ =======
ከጸጥታ ወደብ ከፍቅር አውድማ(፪)
ከሰላሙ መንደር ከእውነት ከተማ
ሰዐሊ ለነ ቅድስት ውዳሴሽ ሲሰማ(፪)
ከሚካኤል ከገብርኤል ጋር ነይልን ከራማ(፪)
አዝ========
ዘርፋፋው ቀሚስሽ ይውረድ ከሰማያት(፪)
እንባችን ይታበስ ባንቺ አማላጅነት
የጽዮን ዝማሬ ተሞላች ነፍሳቸን(፪)
ንዒ ንዒ ንዒ እንበል እንደ አባቶቻችን(፪)
አዝ========
ፍጥረታት ሊድኑ በአማላጅነትሽ(፪)
የዘላለም ኪዳን አማኑኤል ሰጠሽ
ትውልድ ይህን አምኖ ብፅይት ይሉሻል(፪)
እናቴ መመኪያዬ ምርኩዜ ሆነሻል(፪)
አዝ======
የልብን ሲያዋዩሽ ሰምተሽ ዝም አትይም(፪)
ችግረኛን አይቶ ልብሽ አይጨክንም
ከአይን ጥቅሻ ፈጥነሽ ትደርሽለታለሽ(፪)
ከህዘን ከመከራ ታሳርፊዋለሽ(፪)