Amen Spiritual Ministry

Amen Spiritual Ministry Provide Spiritual Service

30/05/2024

አንድ እውነት አለ።
ሁሉ ነገር ይቀየራል፤ የነበረው ጠፍቶ ያልነበረው ይመጣል፤ በሰው ሁሉ ዘንድ መገረም ይፈጥራል።
እኔ የማምነው ይሄን ነው፤ ነውጡ ለለውጥ ይሆናል።
የማይናወጥ አምላክ ሁሉን አናውጣለሁ ይላል።

“.... አሁን ግን፦ አንድ ጊዜ ደግሜ እኔ ሰማይን አናውጣለሁ እንጂ ምድርን ብቻ አይደለም ብሎ ተስፋ ሰጥቶአል።”
(ዕብራውያን 12፥26)

05/05/2024
25/11/2023

“እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ።”
— ራእይ 22፥12

23/11/2023

መዝሙር 33
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁶ ንጉሥ በሠራዊቱ ብዛት አይድንም፥ ኃያልም በኃይሉ ብዛት አያመልጥም።
¹⁷ ፈረስም ከንቱ ነው፥ አያድንም፤ በኃይሉም ብዛት አያመልጥም።
¹⁸ እነሆ፥ የእግዚአብሔር ዓይኖች ወደሚፈሩት ናቸው፥ በምሕረቱም ወደሚታመኑ፥
¹⁹ ነፍሳቸውን ከሞት ያድን ዘንድ፥ በራብም ጊዜ ይመግባቸው ዘንድ።
²⁰ ነፍሳችን እግዚአብሔርን ተስፋ ታደርገዋለች፥ ረዳታችንና መጠጊያችን እርሱ ነውና።
²¹ ልባችን በእርሱ ደስ ይለዋልና፥ በቅዱስ ስሙም ታምነናልና።
²² አቤቱ፥ ምሕረትህ በላያችን ትሁን፥ በአንተ እንደ ታመንን።

22/11/2023

“ንጉሡም በይሁዳ ምድር ላይ አለቃ እሆን ዘንድ ካዘዘኝ ጊዜ ጀምሮ ከንጉሡ ከአርጤክስስ ከሀያኛው ዓመት እስከ ሠላሳ ሁለተኛው ዓመት ድረስ አሥራ ሁለት ዓመት ያህል እኔና ወንድሞቼ ለአለቃ የሚገባውን ስንቅ አልበላንም።”
— ነሀምያ 5፥14

22/11/2023

“ንጉሥ በሠራዊቱ ብዛት አይድንም፥ ኃያልም በኃይሉ ብዛት አያመልጥም።”
— መዝሙር 33፥16

21/10/2023

በጠላት ከበባ ውስጥ ሆነህ ተፈርተህና ተከብረህ ከፍ ብለህ እንድትኖር ያደረገህ ዋናው ምስጢር እግዚአብሔር ከአንተ ጋር የገባው ቃል ኪዳን ነው።

እንዲህ ተብሎ እንደተፃፈ፦
“እግዚአብሔር ያልረገመውን እንዴት እረግማለሁ? እግዚአብሔር ያልተጣላውን እንዴት እጣላለሁ?”
— ዘኍልቁ 23፥8

የእስራኤል ህዝብ የሚጠፋ የሚረገም ህዝብ አይደለም። ዛሬም ዘርህን ሊያጠፉ ይሞክሩ ይሆናል፤ ግን አይችሉም።

“ትሕትናንና የመላእክትን አምልኮ እየወደደ፥ ባላየውም ያለ ፈቃድ እየገባ፥ በሥጋዊም አእምሮ በከንቱ እየታበየ ማንም አይፍረድባችሁ።”
— ቆላስይስ 2፥18

ከአጋንንት ጋር ኪዳን ያለው ነገር አንገቱ ላይ እያንጠለጠለ፤ ዛፍና ድንጋይ ፥ ጨረቃና ወንዝ እያመለከ ማንም አይፍረድብህ ወገኔ። ኪዳንህን ከጌታህ ጋር አዲስ። በጠላትህ የምትበላው ከጌታ ጋር ያለው ኪዳንህ ሲበላሽ ነው።

ፀጋህ ይብዛልን!

03/10/2023

“በዓይኖችህ ብቻ ትመለከታለህ፥ የኃጥኣንንም ብድራት ታያለህ።”
— መዝሙር 91፥8

02/07/2023

"ምን አለበት?"

የሰይጣንን ሀሳብ አንስተውም ደግሞ ምስጢርን የሚገልጥ በሰማይ ውስጥ አለ:: ቤተ እምነቶቻችን ምን አለበት እያሉ የሰይጣን ተገዢ ሆኑ:: ጌታ ለወንጌል ቀብቶኛል ብለው ይወጡና ቤተ ክርስቲያን በመትከል ፋንታ ድርጅት ይመሰርታሉ:: ለምን ስትሉአቸው ምን አለበት ይሏችሁዋል::
ጌታ ለወንጌል ቀብቶኛል ብለው ይወጡና ጌታ ሰው አጥማጅ አደርግሃለሁ ብሎኛል ይሉና የተጠመደ ሰው ያጠምዳሉ:: ለምን ስትሉአቸው ምን አለበት ይሏችሁዋል::
ጌታ ለወንጌል ቀብቶኛል ብለው ይወጡና ከህዝብ ለወንጌል ብለው ብር ይሰበስቡና የግላቸውን ቤትና መኪና ይገዙበታል:: ለምን የጌታ ብር አይደል እንደ ስትሉአቸው ምን አለበት ይሏችሁዋል::
ጌታ ለወንጌል ቀብቶኛል ብለው የተሻለ ደመወዝ ሲያገኙ ቤተ ክርስቲያንን ለቀው ይሔዳሉ ወደ ውጪም ይሔዳለ አገር ውስጥም ይሠራሉ:: ለምን ስትሉአቸው ምን አለበት ይሏችሁዋል::
ጌታ ለወንጌል ቀብቶኛል ብለው ስልጣን ሲያገኙ አገልግሎቱን ትተው ስልጣን ይይዛሉ ለምን ስትሉአቸው ምን አለበት ይሏችሁዋል::
ሰይጣን እንዲህ ይላል:- ምን ችግር አለው? ሐጢያት ብትሰራ ምን አለበት ይላል:: ሐጢያት ብትሰራ ምንም አትሆንም ይላል:: ብትዋሽ ሙስና ብትሰራ ሰው ካላየህ ብትሰርቅ ብትዘሙት ምን ችግር አለው ይላል:: ይህን ሁሉ እያደረጉ መኪና ገዙ: ስልጣን ያዙ: ቤት ሰሩ: ድርጅት ከፈቱ:: አንተ ግን በጽድቅ እየኖርክ ምንም የለህም ይላል::
ወዳጄ አንድ እውነት ልንገርህ ምን አለበት ብለህ የሰይጣንን ምክር ብትሰማ ያለበትን እነግርሃለሁ:-
1. ሞት አለበት
2. ክርክር አለበት
3. ቅንዓት አለበት
4. ምቀኝነት አለበት
5. ስካር አለበት::
ሰይጣን ምን አለበት ነው ያለህ: እኔ ደግሞ የሌለበትን ልንገህ:-
1. ህይወት የለበትም
2. ፍቅር የለበትም
3. ደስታ የለበትም
4. ሰላም የለበትም
5. እምነት የለበትም::
ዛሬ ምረጥ! ወይ የሰይጣንን ምክር መቀበል ወይም ውድቅ ማድረግ::
ማለትም "ሞት" ወይም "ህይወት"
እኔ ግን "ህይወትን" መረጥሁ!

29/06/2023

ጥሩ ክርስቲያን መሆን ቢያቅትህ እንኳን ጥሩ ሰው ሁን!

21/06/2023

“አቤቱ፥ ኃጢአተኞች እስከ መቼ? ኃጢአተኞች እስከ መቼ ይጓደዳሉ?”
— መዝሙር 94፥3

Address

Mekanisa
Addis Ababa

Telephone

+251913026407

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amen Spiritual Ministry posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Amen Spiritual Ministry:

Share