22/05/2026
1፤ በመጠበቂያዬ ላይ እቆማለሁ፥ በአምባ ላይም እወጣለሁ፤ የሚናገረኝንም፥ ስለ ክርክሬም የምመልሰውን አውቅ ዘንድ እመለከታለሁ።
2፤ እግዚአብሔርም መለሰልኝ እንዲህም አለ። አንባቢው ይፈጥን ዘንድ ራእዩን ጻፍ፥ በጽላትም ላይ ግለጠው።
3፤ ራእዩ ገና እስከ ተወሰነው ጊዜ ነው፥ ወደ ፍጻሜውም ይቸኵላል፥ እርሱም አይዋሽም፤ ቢዘገይም በእርግጥ ይመጣልና ታገሠው፤ እርሱ አይዘገይም። ዕባቆ 2
✍️ እንባቆም ወደእግዚአብሔር ሲፀልይ እግዚአብሔርን ውረድ ፍረድ ህዝብህን መልስ እያለ ሲያወራ እንመለከትና ወደ ምእራፍ ሁለት ይሻገራል
👉 በምእራፍ ሁለት እንባቆም ስለፀለየው ፀሎት ከእግዚአብሔር መልስን ጠብቆ በአምባ ላይ እወጣለው በመጠበቂያዬ ላይ እጠብቀዋለው እያለ ጌታን ሲጠብቅ ጌታም ሲመልስ እናያለን ብዘገይም እመጣለሁ ጠብቀኝ አለው ጌታ
🔷 ዛሬ እንዲህ ልበላችሁ እግዚአብሔር ፀሎትን ይሰማል ደግሞም ይመልሳል ከእኛ የሚጠበቀው ነገር መፀለይ ከዛ ደግሞ እስኪመለስ መጠበቅ ደግሞ እንዲህ ልበላችሁ ጌታችሁ የዘገየ ቢመስል እንኳን ይመጣል አይቀርም ታግሳችሁ ጠብቁት ተባረኩልኝ
ፓስተር ካሳሁን ለማ