Tehadiso international church

Tehadiso international church Bible study
(1)

1፤ በመጠበቂያዬ ላይ እቆማለሁ፥ በአምባ ላይም እወጣለሁ፤ የሚናገረኝንም፥ ስለ ክርክሬም የምመልሰውን አውቅ ዘንድ እመለከታለሁ። 2፤ እግዚአብሔርም መለሰልኝ እንዲህም አለ። አንባቢው ይፈጥን ...
22/05/2026

1፤ በመጠበቂያዬ ላይ እቆማለሁ፥ በአምባ ላይም እወጣለሁ፤ የሚናገረኝንም፥ ስለ ክርክሬም የምመልሰውን አውቅ ዘንድ እመለከታለሁ።

2፤ እግዚአብሔርም መለሰልኝ እንዲህም አለ። አንባቢው ይፈጥን ዘንድ ራእዩን ጻፍ፥ በጽላትም ላይ ግለጠው።

3፤ ራእዩ ገና እስከ ተወሰነው ጊዜ ነው፥ ወደ ፍጻሜውም ይቸኵላል፥ እርሱም አይዋሽም፤ ቢዘገይም በእርግጥ ይመጣልና ታገሠው፤ እርሱ አይዘገይም። ዕባቆ 2

✍️ እንባቆም ወደእግዚአብሔር ሲፀልይ እግዚአብሔርን ውረድ ፍረድ ህዝብህን መልስ እያለ ሲያወራ እንመለከትና ወደ ምእራፍ ሁለት ይሻገራል

👉 በምእራፍ ሁለት እንባቆም ስለፀለየው ፀሎት ከእግዚአብሔር መልስን ጠብቆ በአምባ ላይ እወጣለው በመጠበቂያዬ ላይ እጠብቀዋለው እያለ ጌታን ሲጠብቅ ጌታም ሲመልስ እናያለን ብዘገይም እመጣለሁ ጠብቀኝ አለው ጌታ

🔷 ዛሬ እንዲህ ልበላችሁ እግዚአብሔር ፀሎትን ይሰማል ደግሞም ይመልሳል ከእኛ የሚጠበቀው ነገር መፀለይ ከዛ ደግሞ እስኪመለስ መጠበቅ ደግሞ እንዲህ ልበላችሁ ጌታችሁ የዘገየ ቢመስል እንኳን ይመጣል አይቀርም ታግሳችሁ ጠብቁት ተባረኩልኝ

ፓስተር ካሳሁን ለማ

ተለቀቀ፣፣፣፣ ልጅሽን እገድላለው አለኝ ፣ የአመታት ፍትህ እጦትና መከራ
20/05/2026

ተለቀቀ፣፣፣፣ ልጅሽን እገድላለው አለኝ ፣ የአመታት ፍትህ እጦትና መከራ

ልጅሽን እገድላለው አለኝ ፣ የአመታት ፍትህ እጦትና መከራ 👆አገልግሎታችንን ለመደገፍ SUBSCRIBE AN...

20/05/2026
19/05/2026

የልቤ አምላክ / ዘማሪ አቤኔዘር / አገልግሎታችንን ለመደገፍ SUBSCRIBE AND THANKS GIFTS...

19/05/2026
“ስለዚህ፦ አንተ የምትተኛ ንቃ ከሙታንም ተነሣ ክርስቶስም ያበራልሃል ይላል።”  — ኤፌሶን 5፥14መንቃት በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ ትልቅ ምስጢር ያለው እውነት ነው።መንቃት ሀይል ነው።መ...
19/05/2026

“ስለዚህ፦ አንተ የምትተኛ ንቃ ከሙታንም ተነሣ ክርስቶስም ያበራልሃል ይላል።”
— ኤፌሶን 5፥14

መንቃት በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ ትልቅ ምስጢር ያለው እውነት ነው።
መንቃት ሀይል ነው።መንቃት ከእግዚአብሔር የሆነውን ዕርዳታ የምንቀበልበት ጥበብ ነው።

የእግዚአብሔር መንግስት የምትሰራው ለሚያቀላፉ ሳይሆን ለሚነቁ ነው።

ንቁዎች በእግዚአብሔር መንግስት እንቅስቃሴ ታዛቢዎች አይሆኑም ተካፋዮች ናቸው።

በቤተክርስቲያን ታሪክ ሁለት አይነት ሰዎች በማንኛውም ዘመን አይታጡም።
ፍፃሜአቸውን ተኝተው የገደሉና ተኝተው ያሳረቁ።

ሰይጣን በህይወታችሁ ያደረገውን ሁሉ ያደረገው በንቃት ወራታችሁ ሳይሆን በእቅልፍ ወራታችሁ ነው።
በአንደኛ ነገስት ላይ በመተኛት የገደለችና በመተኛት ያሰረቀች ሁለት ሴቶች እናገኛለን እነዚህ ሁለት ሴቶች በመተኛት ያጡት ነገር ይለያይ እንጂ ያጡበት ምክኒያት አንድ እርሱም እንቅልፍ ይባላል።

1ኛ ነገሥት 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁶ በዚያን ጊዜም ሁለት ጋለሞቶች ሴቶች ወደ ንጉሡ መጥተው በፊቱ ቆሙ።
¹⁷ አንደኛይቱም ሴት አለች፦ ጌታዬ ሆይ፥ እኔና ይህች ሴት በአንድ ቤት እንኖራለን፤ እኔም ከእርስዋ ጋር በቤት ሳለሁ ወለድሁ።
¹⁸ እኔ ከወለድሁ ከሦስት ቀን በኋላ ይህች ሴት ደግሞ ወለደች፤ እኛ በቤት ውስጥ አብረን ነበርን፥ ከሁለታችንም በቀር ማንም በቤት ውስጥ አልነበረም።
¹⁹ እርስዋም በላዩ ስለ ተኛችበት የዚህች ሴት ልጅ በሌሊት ሞተ።
²⁰ እርስዋም በእኩለ ሌሊት ተነሥታ፥ እኔ ባሪያህ ተኝቼ ሳለሁ፥ ልጄን ከአጠገቤ ወሰደች፥ በብብትዋም አደረገችው፥ የሞተውንም ልጅዋን በእኔ ብብት አደረገች።

ተኝታ ያሰረቀችው ማልዳ ስተነሳ መፅሐፍ እንደሚለን በብርሃን ስትመለክት ወዲያው በመተኛት ከእጇ የወጣውን ልጅ ለማስመለስ የሚሆነውን አቅም አገኝች።

ተኝታችሁ የሚያስመልስላችሁ እግዚአብሔር የለም።
በእናንተ መንቃት እግዚአብሔር ይነሳል በእግዚአብሔር መነሳት ደግሞ የጠፍባችሁ ይመለሳል።

“አንተ ተነሥ ጽዮንንም ይቅር በላት፥ የምሕረትዋ ጊዜ ነውና፥ ዘመንዋም ደርሶአልና፤”
— መዝሙር 102፥13

ስንነቃ እግዚአብሔር መንገዳችንን ያቀናልናል ስንተኛ ስይጣን ይሰራልናል።
ንቁ የሚያደርግ የእግዚአብሔር መንፈስ ያግኛችሁ!!!

ፓስተር ካሳሁን ለማ

18/05/2026

👆አገልግሎታችንን ለመደገፍ SUBSCRIBE AND THANKS GIFTS ARE AVAILABLEhttps://gofund.me/a19ca602 CASHAPP AND ZAIL 7028303515 AWASH BANK 01320851954200 birhan bank 100...

³ የደከሙትን እጆች አበርቱ፤ የላሉትንም ጒልበቶች አጽኑ፤⁴ የሚፈራ ልብ ላላቸው እንዲህ በሉ፤ “በርቱ፤ አትፍሩ፤ አምላካችሁ ይመጣል፤ ሊበቀል ይመጣል፤ እርሱም ብድራቱን ይዞ፣ ሊያድናችሁ ይመ...
18/05/2026

³ የደከሙትን እጆች አበርቱ፤ የላሉትንም ጒልበቶች አጽኑ፤

⁴ የሚፈራ ልብ ላላቸው እንዲህ በሉ፤ “በርቱ፤ አትፍሩ፤ አምላካችሁ ይመጣል፤ ሊበቀል ይመጣል፤ እርሱም ብድራቱን ይዞ፣ ሊያድናችሁ ይመጣል።” ኢሳ 35

✍️ የሚይበረታ የእግዚአብሔር መንፈስ ያግኛችሁ አፅንቶ ያቁማችሁ የሚያበረቱ መልካም ሰዎችን እግዚአብሔር ይስጣችሁ እየተገዳደራችሁ ያለውን የክፋት ሃይል እግዚአብሔር ይምታላችሁ እንደገና መበረታታት እንደገና መቆም እንደገና መታደስ ይሁንላችሁ ተባረኩ

ፓስተር ካሳሁን ለማ

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tehadiso international church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Tehadiso international church:

Share