ገዳማትና አድባራት Monasteries and Churches

ገዳማትና አድባራት Monasteries and Churches ገዳማትና አድባራትን ማወቅ፥ መሳለም፥ በረከትን ማግኘት፨

ሶበ ተዘከርናሃ……፤ የኢትዮጵያውያን እናቶችና ሕፃናትን ባሰብናቸው ጊዜ አለቀስን፡፡በመላው ሀገራችን በግፍ በሚገደሉ፣ በምሥራቅ አርሲና በሆሮጉድሩ ወለጋ በግፍ በሚገደሉ በሚሰየፉ እና በሚታገቱ...
22/12/2025

ሶበ ተዘከርናሃ……፤ የኢትዮጵያውያን እናቶችና ሕፃናትን ባሰብናቸው ጊዜ አለቀስን፡፡
በመላው ሀገራችን በግፍ በሚገደሉ፣ በምሥራቅ አርሲና በሆሮጉድሩ ወለጋ በግፍ በሚገደሉ በሚሰየፉ እና በሚታገቱት ሕፃናትን እናቶች እንባችን ሳይደርቅ፤
ዛሬ ደግሞ በትግራይ ሕፃፅ በረሃብ ያሉ እናቶቻችን ስቃይ ስናይ አለቀስን!!!፡፡
በትግራይ በተለይ በገጠራማው አካባቢ ያሉ እናቶች አንድ ሰው ውኀ ተጠምቶ (ማይ ሀበኒ) ብሎ ጠይቆ ውኀ አይሰጡትም፤ ካለ ጠላ ከሌለም ቅራሬ ከሌለም በማዕጠንት የታጠነ ውኀ እንጂ፡፡
እናቶቼ፤ አምላከ አበው መድኀኔዓለም በበረከት ይጎብኛችሁ፡፡
የእኔ እናት ቢሆኑስ እንዲህ የሆኑት ብላችሁ አስቡ!!!!፤ ልብ ያለው ልብ ይበል፡፡
ታኅሣሥ 13/2018 ዓ.ም.

እስመ ተሀጥኦ ሊቅሰ ግብር እኩይ ውእቱ፡፡ (የመምህር መታጣት ይጎዳል፡፡) /ድርሳን ዘዮሐንስ አፈ ወርቅ 34/አፈር መልሱ እንጂ ድንጋይ ሰብስባችሁ፤የቀለም ቀንድ ነው ትሰብሩታላችሁ፡፡ለ26ት ...
08/09/2025

እስመ ተሀጥኦ ሊቅሰ ግብር እኩይ ውእቱ፡፡ (የመምህር መታጣት ይጎዳል፡፡) /ድርሳን ዘዮሐንስ አፈ ወርቅ 34/
አፈር መልሱ እንጂ ድንጋይ ሰብስባችሁ፤
የቀለም ቀንድ ነው ትሰብሩታላችሁ፡፡
ለ26ት ዓመታት በኢትዮጵያ ብቸኛው የመጻሕፍተ መነኰሳት ምስክር፣ የታሪክ ዐውድማው መጋቤ ምሥጢር የኔታ ተሾመ ታደሰ፤ አሸልበዋል፡፡
ሲያስተምሩ ዕለት ዕለት ሲጠሩት ወደ ነበረው ወደ ቅዱሳን (ማር ይስሐቅ፣ ፊልክስዩስ አረጋዊ) አምላክ ተጠርተዋል፤ እሳቸውም ሳይነግሩን ቀጠሯቸዋን አክብረው ሄደዋል፡፡

 ….. መምህር ኀይለ ሥላሴ የመጻሕፍተ መነኰሳት ጕባኤ ቤት ለ፲፰ ዓመታት አስተምረው ወደ ሐማሴን በ፲፱፻፹፯ዓ.ም ሒደዋል፤ ከ፲፱፻፹፯ዓ.ም እስከ ፲፱፻፺፩ዓ.ም ለ፬ ዓመታት መምህር የኔታ ታሪክ ሲያስተምሩ ቆይተው አርፈዋል፤ በምትካቸው ከ፲፱፻፺፩ዓ.ም ጀምሮ እስከ አሁን በጎንደር ሐመረ ኖኅ ሠለስቱ ምዕት ቤ.ክ. የምስክር መምህር ሆነው ያስተማሩ መጋቤ ምሥጢር መምህር ተሾመ ታደሰ ናቸው እንግዲህ በርኅወ ሰማይ ቀን በጳጕሜን 3 የተለዩን!!፡፡ /በቃላቸው ከነገሩኝ ታሪክ የተቀነጨበ/

‹‹…በጺሐኪ ድንግል ጊዜ ዕረፍትየ፤ (ድንግል በዕረፍቴ ጊዜ ደርሰሽ)
ጽጌ ዕፀ ገነት ገሪ ላዕሌየ፤ (የገነት የዛፍ አበባን በእኔ ላይ ጣዪ፥ ዕጠኚ)
በመዐዛሁ ትትመሠጥ ነፍስየ፡፡ (በመዐዛው ነፍሴ ከሥጋዬ ትለይ ዘንድ) /ማሕሌተ ጽጌ ቊ.፻፲፮/

ንፍሑ ቀርነ በጎንደር (በጎንደር ሐመረ ኖኅ መለከትን ንፉ)፤ መምህራችን አረፏልና!!!!፡፡
ግብዐተ መሬታቸውም በኑዛዜያቸው መሠረት በዓለም ሁሉ ለሚገኙ ገዳማት ምክሆን በሆነው በዋልድባ ገዳም (ገዳመ ዋሊ) ዛሬ በርኅወ ሰማይ ይፈጸማል፡፡

፨ ‹‹ወኢትጸመም ሞቶ ለዘ ተልአከከ
(ያገለገለህን ሰው ሞት ቸል አትበል፡፡'') ሲራክ 38÷16
፨ ኦ መምህርነ በከመ ልማድከ ሰአል በእንቲአነ፤ አስተምህር ለእንቲአነ፤ ኢታርምም ወኢትጸመም፨
/ዝክረ ሊቃውንት ገጽ፡፡/

ንቡረ ዕድ በላይ መረሳ #አባታችን ሆይ ለማን ይሆን ጥለውን የሄዱት? #አባታችን ሆይ ወደ ጽዮን ስንሄድ ማን ይሆን የሚቀበለን!! #አባታችን ሆይ ሁሌ ከአፍዎት የማትለየው ኢትዮጵያን፥ ጽዮንን...
22/08/2025

ንቡረ ዕድ በላይ መረሳ
#አባታችን ሆይ ለማን ይሆን ጥለውን የሄዱት?
#አባታችን ሆይ ወደ ጽዮን ስንሄድ ማን ይሆን የሚቀበለን!!
#አባታችን ሆይ ሁሌ ከአፍዎት የማትለየው ኢትዮጵያን፥ ጽዮንን ለማን ይሆን ትተው የሄዱት!!!!
#አባታችን ሆይ በመሃላችን የተፈጠረውን ክፍፍል ሳያሳታርቁን በፍልሰታ እንደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ''ምስለ ፍልሰትኪ ደምርኒ እሙ፡፡'' ብለው የፈለሱት፥ ወደየትስ ነው ትተውን የኮበለሉት?!!

ጽዮንን ባሰብናት ጊዜ አለቀሰን፡፡ መዝ.135፡፡ ምክንያቱም፤
፨ የአኵስም ጽዮን ማርያም መለያ እስከ መሆን የደረሱ፤
፨ የአኵስም ሊቃውንት ጒባኤ ሰብሳቢ፤
፨ የአኵስም መንበረ ያሬድ የድጓ ዋና ምስክር መምህር የሆኑ፥ ዳግማዊ ያሬድ፤
፨ የዝማሬ መዋሥዕት፣ የአቋቋም መምህር፤
፨ የቅኔ፣ የብሉይ እና የሐዲስ፣ የፍትሐ ነገሥት እና የባሕረ ሐሳብ ምሁር፤
፨ ገበዘ አኵስም ጽዮን፤
፨ ዜማን ከታሪክ ጋራ፥ ትሕትናን ከፍቅር ጋራ፥ ጸሎትን ከምግባር ጋራ አስተባብረው የያዙ፤
፨ ወላዴ አእላፍ ሊቃውንት፥ ዐይናማው ሊቅ
፨ የኢትዮጵያ ዋርካ
፨ በክብረ በዓልም ሆነ በአዘቦት ከመላው ዓለም ወደ ጽዮን ማርያም የሄደው ሁሉ በቅጽረ ቤ.ክ የማያጣቸው፤ የሚያስተናግዱ፤ የሚያስተምሩ
ንቡረ ዕድ በላይ መረሳ በዐረፍተ ሥጋ ተለይተውናልና፡፡

፨ ሥርዐተ ግብዓተ መሬታቸው ዕድሜ ዘመናቸውን ባገለገሉበት በርዕሰ ገዳማት ወአድባራት አኵስም ደብረ ጽዮን ማርያም ቅዳሜ ነሐሴ 17 ስለሚካሄድ ወደዚያው እንትመም! ያልቻለ በሐሳብ ይገኝ፡፡
ንፍሑ ቀርነ በጽዮን (በጽዮን መለከትን ንፉ)፡፡

፨ ''ወኢትጸመም ሞቶ ለዘ ተልአከከ ( ያገለገለህን ሰው ሞት ቸል አትበል፡፡'' ሲራክ 38÷16

፨ ኦ መምህርነ በከመ ልማድከ ሰአል በእንቲአነ፤ ኢታርምም ወኢትጸመም፨
፨፨ /ጕባኤ ቃና ቅኔ ከአባ ገብረማርያም/
ከመ ያርሕቅ ያርሕቅ ደዌ እምነ ከኒሳ፤
ተፈነወ ኢትዮጵያዊ ኢሳይያስ መርሳ፨
** እያለቀስን ጻፍንላችሁ፨

የበረከት ሥራ ፩ (የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች!!! ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ አልቆ ለመመረቅ የቀረውን ሞልተን እናስመርቅ)የደብሩ ስም እና መገኛው፤ ሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ደባርቅ ወረዳ፥ ምጣ...
27/05/2025

የበረከት ሥራ ፩ (የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች!!! ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ አልቆ ለመመረቅ የቀረውን ሞልተን እናስመርቅ)
የደብሩ ስም እና መገኛው፤ ሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ደባርቅ ወረዳ፥ ምጣራ ቀበሌ፥ ደብረ ኀይል ጉልትኮ (ንቡ) ቅዱስ ሚካኤል፡፡
የሚያስፈልገው፤
 መስታወት፤ ለ36 መስኮት መስታወት (48 ካሬ ሜትር መስታወት+ setuko+ የሠራተኛ = የ1ካሬ ዋጋ =2500+ የስቱኮ+ የሠራተኛ ~155,000 /አንድ መቶ ሃምሳ አምስት ሺህ ብር/)
 ሲሚንቶ፤ የውስጡን የቤተ ክርስቲያን ግድግዳ ሊሾ ለማድረግ እና ለወለል፡፡ 145-150 ኩንታል (የ1 ኩንታል ዋጋ 1,650፤ አጠቃላይ የ150*1650=247,500 /ሁለት መቶ አርባ ሰባት ሺህ ብር/)
የቤተ ክርስቲያኑ የባንክ አካውንት ቊጥር፤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000360501478 (D/HAIL GULT K/MIKAEL CHURCH)
የቤተ ክርስቲያኑ ሕንፃ አሠሪ ተወካይ፤ ርዕሰ ደብር ቄስ ደንበር ባይነሳኝ (0964 490673)
የቤተ ክርስቲያኑ አጭር ታሪክ፤ ከ382 ዓመታት በፊት በራስ ኒቃሊዎስ የተመሠረተ ሲሆን፤ ቅዱስ ሚካኤል በየዕለቱ ተአምር የሚሠራበት ድንቅ ቦታ ነው፤ ንጽሕ ሳይጠብቅ ወደ መቅደስ የገባውን ካህን አሁንም ድረስ በንብ ነድፎ ያርቀዋል፡፡)

ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
(በቀጣይ በየወሩ በረከት የምናገኝባቸው ገዳማት እና አድባራት ስለሚኖሩ ዐሥራት በኵራት እንዲሁም ስዕለት ሥጦታችሁን እያዘጋጃችሁ ጠብቁ)
/ /
/ /
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

  #ግንቦት ፳፩   #ግንቦት ፳፩ (ከግንቦት፳፩-፳፭)፤  (ሌሎች ያልጠቀስናቸው አብያተ ክርስቲያናት ካሉ አሳውቁን)© ገዳማትና አድባራት Monasteries and Churchesꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ...
27/05/2025


#ግንቦት ፳፩
#ግንቦት ፳፩ (ከግንቦት፳፩-፳፭)፤
(ሌሎች ያልጠቀስናቸው አብያተ ክርስቲያናት ካሉ አሳውቁን)
© ገዳማትና አድባራት Monasteries and Churches
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
፡፡
፩. ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምና ደብረ መድኀኒት መድኀኔዓለም ቤ/ክ፤
አድራሻው፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ ልደታ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ) → ሜክሲኮ → ጦር ኃይሎች፤

፪. ፈረንሳይ ገነተ ኢየሱስና ገነተ ማርያም ቤ/ክ (እናትና ልጇ)፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ፈረንሳይ ሌጋሲዮን፥ 41 ኢየሱስ፤
ታክሲ፤ ከ4ኪሎ (6 ኪሊ) → 41 ኢየሱስ/ፈረንሳይ/

፫. ገዳመ ኢየሱስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፤
ታክሲ፤ ከመርካቶ → ኮልፌ፡፡
ወይም ከጦር ኃይሎች ዊንጌት/አስኮ/ → (በሚል ታክሲ) (በቀለበት መንገድ)

፬. አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኀኔዓለም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ጋራው መድኀኔዓለም፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ) (ለገሀር) (መገናኛ) (ቦሌ) → አቃቂ/ቃሊቲ

፭. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ መካኒሳ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → መካኒሳ

፮. ጃቲ መካነ ሕይወት ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ 08፥ ጃቲ፡፡
ታክሲ፤ ከፒያሳ(ከቦሌ) → ቃሊቲ → ጃቲ (አቃቂ በሚለው ታክሲ)፡፡

፯. የካ ኮተቤ ደብረ ምሕረት ኪዳነ ምሕረትና መድኀኔዓለም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 9፡፡
ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ኮተቤ ወረዳ 9፡፡

፰. ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ ዊንጌት፡፡
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ አቡነ ጴጥሮስ → አስኮ/ዊንጌት/፡፡

፱. ጀሞ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ (ሜክሲኮ) → ጀሞ፡፡
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#፫ ፡፡
፩. መንዝ እመጓ ደብረ ቆጵሮስ ኢየሱስ ወቅዱስ ኡር(ራ)ኤል ደብር፡፡
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ መንዝ ሞላሌ፥ ዕመጓ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከላምበረት መናኸርያ→ መንዝ ሞላሌ →ዕመጓ፡፡
፪. አምቦ ኢየሱስ ቤ/ክ፡፡
አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ አምቦ ከተማ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከአስኮ መናኸርያ→ አምቦ፡፡
፫. መገር ቅዱስ ዐማኑኤል ቤ/ክ፡፡
አድራሻ፤ ጉራጌ ሀገረ ስብከት፥ እነሞርና ኤነር ወረዳ፥ መገር፡፡
ትራንስፖርት፤ ከአስኮ መናኸርያ→ ኤነር፡፡

ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

#ግብጻውያን ክርስቲያኖች ከግንቦት 21 እስከ 25 የእመቤታችንን በዓል (ምሰሶ አቁመው፥ አጎበር ጥለው፥ ድንኳን ተክለው፥ ድባብ ዘርግተው ያከብራሉ፤ እመቤታችንም ከቅዱሳን ጋር በመገኘት ትባርካቸዋለች፡፡)
እነዚህ 5ት ቀናትም #ከእመቤታችን 33ቱ በዓላት 5ቱን ከተ.ቊ 25ኛ እስከ 29ኛ ያለውን ይይዛሉ፡፡
የደብረ ምጥማቅ በዓላት (ከግንቦት 21-25) በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን በግብጽ ተነሥቶ የነበረው ንጉሥ የግብጽ ክርስቲያኖች በዓሉን እንዳያከብሩ በመከልከሉ፤ ኢትዮጵያውያንም ይህንን በዓል ለማክበር ወደ ግብፅ ይሄዱ ነበርና ፤ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ለመጽናኛ እንዲሆን በሃገራችን የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያምን መሠረተ፤ እመቤታችንም ብዙ ቃል ኪዳንን ሰጠችው፤
ይኸው ቃል ኪዳኗ ሳይታጠፍ በጻድቃኔ ማርያም ዛሬ ድረስ ስፍር ቊጥር የሌለው ብዙ ተዓምራትና የምሕረት ሥራ የሚፈጸምባት ቅዱስ ቦታ ኾና ትገኛለች፡፡
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
፡፡

፩. ደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ ምሕረት ማርያም እና ክርስቶስ ሰምራ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ጉርድ ሾላ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ጉርድ ሾላ (በአያት /ሰሚት/ ታክሲ)፡፡

፪. ደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ታቦት ማደርያ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ አውቶቡስ ተራ) → ኮልፌ ታቦት ማደርያ፡፡

#እንዲሁም
፫. ርዕሰ አድባራት እንጦጦ መንበረ ፀሐይ ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻው፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ እንጦጦ፤
ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ(4 ኪሎ) → ሽሮ ሜዳ → እንጦጦ ማርያም፤
ወይም ከ4 ኪሎ → እንጦጦ ማርያም፤ (በ122 ቊጥር አውቶቡስ)
፬. መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም (ቀድሞ እንጦንስ ገዳም)
አድራሻው፤ አራዳ ክፍለ ከተማ፥ 5 ኪሎ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → 5 ኪሎ፤
፭. ገነተ ኢየሱስና ገነተ ማርያም ቤ.ክ.፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ፈረንሳይ፥ 41 ኢየሱስ፤
ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ (4ኪሎ) → ፈረንሳይ (41 ኢየሱስ)፡፡
፮. ደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤ (የዮሐንሷ ማርያም)
አድራሻ፤ አራዳ ክፍለ ከተማ፥ አባ ኮራን (ሰባራ ባቡር) (ራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል)፤
ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ (ከአራዳ) → ራስ ደስታ /በአስኮ መስመር/፡፡
፯. ቦሌ ቡልቡላ ፍኖተ ሕይወት ማርያምና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ቦሌ ቡልቡላ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ሳሪስ አቦ → ቦሌ ቡልቡላ ኮንዶሚኒየም (ማርያም)፡፡
፰. ብሔረ ጽጌ መካነ ሰላም ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ አውግስታ ሸሚዝ ፋብሪካ፡፡
ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ አውቶቡስ ተራ) → አውግስታ፡፡
፱. ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ገርጂ፡፡
ታክሲ፤ ከፒያሳ → መገናኛ → ገርጂ፡፡
፲. በሻሌ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም፤
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ በሻሌ፡፡
ታክሲ፤ ከፒያሳ → መገናኛ → በሻሌ፡፡
፲፩. የቃጥላ ደብረ ፀሐይ ቅድሰት ማርያም፤
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ በሻሌ፡፡
ታክሲ፤ ከፒያሳ → መገናኛ → በሻሌ፡፡
፲፪. አውግስታ ደብረ ጽዮን ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ቂሊንጦ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቃሊቲ ወይም በጎሮ መስመር → ቂሊንጦ፡፡
፲፫. ወይብላ ደብረ ጽዮን ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ሮል ሳሙና ፋብሪካ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጦር ኀይሎች → ሮል ሳሙና ፋብሪካ፡፡
፲፬. ፍኖተ ሎዛ ብርጭቆ ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ብርጭቆ ኮንዶሚኒየም፡፡
ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ (አቡነ ጴጥሮስ አደባባይ) → ብርጭቆ፡፡
፲፭. ማኅደረ መለኮት ወይብላ ደብረ ጽዮን ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ የሺ ደበሌ፡፡
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ፡፡
፲፮. ሐመረ ወርቅ ማርያም እና አርሴማ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ወርቁ ሰፈር፡፡
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ፡፡
፲፯. ፉሪ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ፉሪ፡፡
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ፉሪ፡፡
፲፰. አያት ደ/ክ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አያት፡፡
ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → አያት፡
፲፱. ፈጬ ደብረ ገነት ድንግል ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ፈጬ፤
ታክሲ፤ ከመገናኛ → በጎሮ ኮዬ ፈጬ፡፡
፳. ሰርጢ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሰርጢ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → ሰርጢ፡፡
፳፩. አባዶ ጽርሐ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አባዶ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → አባዶ፡፡
፠፨፠ እንዲሁም፤
፳፪. ኮተቤ ሃገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ፥ ቅድስት ማርያምና ቅድስት መግደላዊት ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አንቆርጫ፤
ታክሲ፤ ከአራዳ ጊዮርጊስ (ከ4 ኪሎ) (ከ6 ኪሎ) → ፈረንሳይ→ አንቆርጫ፡፡
፳፫. ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤል፥ 24ቱ ካህናተ ሰማይና ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አባዶ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → አባዶ፡፡
፳፬. ኤረር በር መካነ ሰላም ሚካኤልና ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ጎሮ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ጎሮ/ኤረር በር/፡፡
፳፭. መሪ ቅድስት ሥላሴ፥ ኡራኤል፥ ማርያም፥ ጊዮርጊስና አቡነ አረጋዊ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ መሪ(ሲኤምሲ)፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → መሪ(ሲኤምሲ)፡፡
፳፮. አንቆርጫ ደብረ ብሥራት ገብርኤልና ማርያም ቤ/ከ፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አንቆርጫ፤
ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ (4 ኪሎ) → ፈረንሳይ → አንቆርጫ፡፡
፳፯. ቂሊንጦ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት ድንግል ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ቂሊንጦ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቃሊቲ ወይም በጎሮ መስመር → ቂሊንጦ፡፡
፳፰. ኮተቤ ደብረ ልዑል ዳግማዊ ቁልቢ ቅዱስ ገብርኤልና ኆኅተ ሰማይ ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ኮተቤ መሳለሚያ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ኮተቤ፡፡
፳፱. ፈለገ ዮርዳኖስ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስና ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ ሸዋ ዳቦ ቤት → ጀሞ፡፡
ወይም ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጀሞ፡፡
፴. ጀሞ ፈለገ ኮሬብ ቅድስት ሥላሴና ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ንፋስ ስ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ 3፥ መስታወት ፋብሪካ ጀርባ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ ሸዋ ዳቦ ቤት → ጀሞ፡፡
ወይም ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጀሞ፡፡

፠፨፠ እንዲሁም፤
፴፩. የካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በድርብነት ትከብራለች)
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ሾላ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → መገናኛ (ሾላ)፡፡
፴፪. ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑር(ራ)ኤል ቤ/ክ፤ (በድርብነት ትከብራለች)
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ካዛንቺስ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ካዛንቺስ፡፡
፴፫. ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ፤ (በድርብነት ትከብራለች)
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ መስቀል አደባባይ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ→ መስቀል አደባባይ (በቦሌ ታክሲ)፡፡
፴፬. ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምና ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ፤ (በድርብነት ትከብራለች)
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ልደታ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ልደታ (በጦር ኀይሎች ታክሲ)፡፡
፴፭. ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ/ክ፤ (በድርብነት ትከብራለች)
አድራሻ፤ ቂርቆስ ከተማ ክፍለ ከተማ፥ መስቀል ፍላወር /አጎና ሲኒማ/፤
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ → መስቀል ፋላወር /አጎና ሲኒማ/ /ጎተራ/ (ሳሪስ በሚል ታክሲ)፡፡
፴፮. ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤ/ክ፤ (በድርብነት ትከብራለች)
አድራሻ፤ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ፥ ሎሚ ተራ፤
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ → አውቶቡስ ተራ/ኮልፌ/ → ሎሚ ተራ (ፊልጶስ)፡፡
፴፯. አፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በድርብነት ትከብራለች)
አድራሻ፤ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ፥ አፍሪካ ኅብረት(ቡልጋርያ)፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → በቄራ መስመር /ቡልጋርያ(አፍሪካ ኅብረት)/፡፡
፴፰. ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል፥ ቅድስት አርሴማና አቡነ አዳም ቤ/ክ፤ (በድርብነት ትከብራለች)
አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ጀርመን አደባባይ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲካ → ጀርመን አደባባይ፡፡
ወይም ከፒያሳ አራዳ ሸዋ ዳቦ ቤት → ጀሞ በሚለው መስመር (ጀርመን አደባባይ)
፴፱. ቃሊቲ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤልና ቊስቋም ማርያም ቤ/ክ፤ (በድርብነት ትከብራለች)
አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ → ሰፈረ ገነት፡፡
፵. አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኀኔዓለም ቤ/ክ፤(ጋራው መድኀኔ ዓለም) (በድርብነት ትከብራለች)
አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ → አቃቂ፡፡
፵፩. መዝገበ ምሕረት ቅዱስ ፋኑኤል ቤ/ክ፤ (በድርብነት ትከብራለች)
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ፋኑኤል ሰፈር፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → ፋኑኤል ሰፈር፡፡
፵፪. ካራ ቆሬ ደብረ ገነት ቅዱስ እስጢፋኖስ፥ ቅዱስ ሚካኤልና ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤ (በድርብነት ትከብራለች)
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ጥላሁን ሜዳ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ካራ ቆሬ፡፡
፵፫. ኮተቤ ደብረ ልዑል ዳግማዊ ቁልቢ ቅዱስ ገብርኤልና ኆኅተ ሰማይ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ኮተቤ መሳለሚያ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ኮተቤ፡፡
፵፬. ፉሪ መካነ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በድርብነት ትከብራለች)
አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ለቡ፥ ፉሪ፤
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ለቡ(ፉሪ)፡፡
፵፭. ዋሻ ደብረ መንክራት አቡነ ተክለ ሃይማኖት እና አብርሀ ወአጽብሀ ፍልፍል ገዳም፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አንቆርጫ (የድሮ የካ ሚካኤል)፤
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ → ሾላ (ኮተቤ መስመር በአዲሱ መንገድ)፡፡
፵፮. ብርሃናተ ዓለም ጴሮስ ወጳውሎስ ወገብርኤል ቤ/ክ፤
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ (ጴጥሮስ ዐደባባይ)→ ጴጥሮስ (አስኮ መስመር)፡፡
፵፯. ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል (ብሥራተ ገብርኤል)፤
አድራሻው፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ብሥራተ ገብርኤል፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ(መርካቶ) → ሜክሲኮ → ብሥራተ ገብርኤል፤
© ገዳማትና አድባራት Monasteries and Churches
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#፭ ፡፡
፩.
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ሞላሌ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ጉርድ ሾላ → ጻድቃኔ፡፡

፪. ጎንደር ሐመረ ብርሃን ደብረ ምጥማቅ ማርያም ወቅዱስ እስጢፋኖስ ወአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ ቀበሌ 06፤
ታክሲ፤ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር ከተማ → ቀበሌ 06፡፡

፫. ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አዲስ ዓለም ደብረ ጽዮን ማርያም፤ (በዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ ተመሠረተች) (ክብሯና አገልግሎቷ እንደ አኵስም ጽዮን ሆና የተመሠረተች)
አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ አዲስ ዓለም ከተማ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → አዲስ አለም፡፡

፬. ወሊሶ ግዮን ቤተ ሳይዳ ደብረ ምጥማቅ ማርያም ገዳም፡፡
፭. ጂንካ ኔሪ ደብረ ምጥማቅ ማርያም፡፡
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
(ሌሎች ያልጠቀስናቸው ገዳማት ካሉ አሳውቁን)
/ /
/ /
© ገዳማትና አድባራት Monasteries and Churches
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

 #ግንቦትት ፲፱፤  ፡፡ +፩ እና    ፡፡   #፪  ፡፡፩. ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል (ብሥራተ ገብርኤል)፤አድራሻው፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ብሥራተ ገብርኤል፤ታክሲ፤ ከፒያሳ(መርካቶ...
26/05/2025

#ግንቦትት ፲፱፤ ፡፡
+፩ እና ፡፡

#፪ ፡፡
፩. ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል (ብሥራተ ገብርኤል)፤
አድራሻው፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ብሥራተ ገብርኤል፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ(መርካቶ) → ሜክሲኮ → ብሥራተ ገብርኤል፤

፪. ኤረር ጎሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክ፤
(የአቡነ ዐቢየ እግዚእ ክብረ በዓል እና የኤረር ጎሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ ቅዳሴ ቤቱ)
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ጎሮ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ጎሮ፡፡

፫. ፉሪ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል ወአቡነ ዐቢየ እግዚእ (ጀሞ ባቡር ጣቢያ ፉሪ ገብርኤል) ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ፉሪ ጀሞ ባቡር ጣቢያ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጀሞ 3 ((ብረት ድልድይ) → ፉሪ ገብርኤል (ባቡር ጣቢያ)

፬. አንቆርጫ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ማርያም ቤ/ክ፤ ((ቅዳሴ ቤቱ))
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አንቆርጫ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ (4(6) ኪሎ) → አንቆርጫ፡፡

ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#፪ ፡፡
፩. ጎንደር ደብረ መድኃኒት ዐቢየ እግዚእ ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክ፡፡
አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር ከተማ → አራዳ (ቀበሌ 16)፡፡

፪. ተንቤን መረታ ዐቢየ እግዚእ ገዳም፤
አድራሻ፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ተንቤን፥ መረታ፤
ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መቀለ → ተንቤን፡፡
ወይም፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር → በአዲዓርቃይ (በዳንሻ ሁመራ) → ሽረ → አኵስም → ተንቤን፡፡
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#ግንቦትት ፲፱፤ ፡፡
አቡነ ዮሴፍ በወሎ ላስታ ሰውን እና ዝንጀሮን በቃል ኪዳን ያስተሳሰሩና ፤ እመቤታችን ዕጣን የሰጠቻቸው ናቸው፡፡

#፩ ፡፡
(ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ ጨምሩበት፡፡)

፩. አቡነ ዮሴፍ ገዳም፡፡
አድራሻ፤ ላስታ ላሊበላ ሃገረ ስብከት፥ ጂፋት፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ → አቡነ ዮሴፍ (ጂፋት)፡፡
ወይም በእግር ከቅዱስ ላሊበላ ከተማ በአሸተን ተራራ አናት ላይ የ4 ሰዐት የእግር መንገድ
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
(ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ አሳውቁን)
/ /
/ /
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

ናዝሬት (አዳማ) ደብረ ገነት ኪዳነ ምሕረት፨
23/05/2025

ናዝሬት (አዳማ) ደብረ ገነት ኪዳነ ምሕረት፨

ዳግመኛ የማይገኝ ጥሪ።፨ግንቦት 15 እና 16 2017 ዓ.ም. እግሮች ሁሉ ወደ አዲስ አበባ አያት ጌቴሴማኒ ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን፨፨ታላቅ የቤተ ክርስቲያን የምርቃት ጥሪ         ...
23/05/2025

ዳግመኛ የማይገኝ ጥሪ።፨
ግንቦት 15 እና 16 2017 ዓ.ም. እግሮች ሁሉ ወደ አዲስ አበባ አያት ጌቴሴማኒ ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን፨፨
ታላቅ የቤተ ክርስቲያን የምርቃት ጥሪ
እንኳን ደስ አለን
የአዲስ አበባ አያት ጌቴ ሴማኒ ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ግንባታው ተጠናቆ ለፍጻሜ ደርሶ ግንቦት 15 እና 16 2017 ዓ.ም. ትመርቃለች።
ኑ እና እንመርቅ፨
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ሰሚት፡፡
ታክሲ፤ ከፒያሳ(ከገመናኛ) → አያት፡፡

ሕንፄሃ አዳም ሕንፄሃ ለጌቴሴማን፤
ሐመልማለ ወርቅ ገበዋቲሃ ሐመልማለ ወርቅ፨
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
© ገዳማትና አድባራት Monasteries and Churches

ዳግመኛ የማይገኝ ጥሪ።፨ግንቦት 15 እና 16 2017 ዓ.ም. እግሮች ሁሉ ወደ ናዝሬት(አዳማ) ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን፨፨ታላቅ የቤተ ክርስቲያን የምርቃት ጥሪ    ...
23/05/2025

ዳግመኛ የማይገኝ ጥሪ።፨
ግንቦት 15 እና 16 2017 ዓ.ም. እግሮች ሁሉ ወደ ናዝሬት(አዳማ) ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን፨፨
ታላቅ የቤተ ክርስቲያን የምርቃት ጥሪ
እንኳን ደስ አለን
የአዳማ(ናዝሬት ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ግንባታው ተጠናቆ ለፍጻሜ ደርሶ ግንቦት 15 እና 16 2017 ዓ.ም. ትመርቃለች።
ኑ እና እንመርቅ፨

ላልሰማ አሰሙ፡፡ ላልደረሰው አዳርሱ፡፡ከእዚህ በኋላ ጸበል የምንጠመቀው በጸበል ቦታዎች ሳይሆን መንግሥት በሚሰጠን በመንደር በሞተር እየተሣበ ይሆናል ማለት ነው!!!፡፡ይህ የጸበል ፈረሳ በአዲ...
08/05/2025

ላልሰማ አሰሙ፡፡ ላልደረሰው አዳርሱ፡፡
ከእዚህ በኋላ ጸበል የምንጠመቀው በጸበል ቦታዎች ሳይሆን መንግሥት በሚሰጠን በመንደር በሞተር እየተሣበ ይሆናል ማለት ነው!!!፡፡
ይህ የጸበል ፈረሳ በአዲስ አበባ ቀጨኔ መድኃኔ ዓለም (የቅዱስ እግዚአብሔር፣ የዮርዳኖስ፣ የቅዱስ ገብርኤል፣ የቅዱስ ሚካኤል፣ የቅድስት ኪዳነ ምሕረት ወአቡዬ ወአርሴማ ወጊዮርጊስ ጸበል) ብቻ እንዳይመስላችሁ!!! በቀጣይም በፈረንሳይ ወይብላ፣ …….. በሌሎችም የሚቀጥል ይሆናል፡፡
የምታዩት ፎቶና ቪዲዮ የቀጨኔ መድሀኔያለም የቤተ ክርስቲያኑ ኃላፊዎች በጸበሉ ቦታ ምትክ ሌላ ቦታ ለመቀበል እና በሚሰጣቸው መንደር ላይ ጠበሉን በፓንፕ (በሞተር) በጎማ በቧንባ ለማስወሰድ ተስማምተው ማስፈረስ የጀመሩት ነው፡፡
የሚገርመው ነገር ግን የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳደር በግቢ ውስጥ የሚገኘውን መካነ መቃብር ምንም ላይሠሩበት አፍርሰው 3 ዓመት አለፈው፡፡ በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲት በትልቅ ተጋድሎ የተሠራውን የቤተ ክርስቲያኑን ግንብ አጥር ደግሞ አፍርሰው ፉካ (ለመሸጥ ለማከራየት) እየሠሩበት ይገኛሉ፡፡
እኛ የተኛን እንነሣ፡፡

ላልሰማ አሰሙ
ላልደረሰው አዳርሱ፡፡

 #ሚያዝያ ፴፤  ፨   #፯  ፡፡(ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ ጨምሩበት፡፡)ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ   #፩  ፡፡፩. መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ፡፡አድራሻ፤ ...
07/05/2025

#ሚያዝያ ፴፤ ፨
#፯ ፡፡
(ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ ጨምሩበት፡፡)
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#፩ ፡፡
፩. መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ፡፡
አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ 6 ኪሎ አደባባይ፤
ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ → 6 ኪሎ (ማርቆስ)፡፡

ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#፭ #ጥንታውያን ፡፡
፩. ደብረ ማርቆስ መልዕልተ አድባራት ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ማርቆስ፡፡
አድራሻ፤ ምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት፥ ደብረ ማርቆስ፤
ትራንስፖርት፤ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ማርቆስ፡፡

፪. ሰላ ድንጋይ ደብረ ኅሩያን ቅዱስ ማርቆስ፡፡ (በ1875 ዓ.ም. በዐፄ ምኒልክ የተመሠረተ)፤ (እምነቱ ማር የሆነ)
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ተጉለት፥ ሰላ ድንጋይ (ጻድቃኔ ማርያም አጠገብ)፤
ትራንስፖርት፤ ከላምበረት አውቶቡስ ተራ → ሰላ ድንጋይ፡፡

፫. መናገሻ መንበረ መንገሥት ቅዱስ ማርቆስ፤ (በዐፄ ምኒልክ ዘመን የአቡን ቤት የነበረ)
አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ መናገሻ፤
ትራንስፖርት፤ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ → መናገሻ፡፡

፬. ባቢሌ ቅዱስ ማርቆስ፤
አድራሻ፤ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት፥ ባቢሌ፤
ትራንስፖርት፤ ከቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ባቢሌ፡፡

፭. ባሕር ዳር ይባብ ቅዱስ ማርቆስ ወያሬድ፤
አድራሻ፤ ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት፥ ይባብ፤
ትራንስፖርት፤ ከባሕር ዳር ከተማ → ድባንቄ /ይባብ/፡፡
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#፩ ፡፡
፩. ግብጽ መንበረ ማርቆስ ቤ/ክ፤ (ግብጽ)
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
(ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ በውስጥ አሳውቁን)
/ /
/ /
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

 #ሚያዝያ ፳፫፤  ፡፡ በአዲስ አበባ በኢትዮጵያና በመላው ዓለም ክብረ በዓሉ የሚከበርባቸው  #፷፬  ፡፡(ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ አሳውቁን)© ገዳማትና አድባራት Monasteries and C...
30/04/2025

#ሚያዝያ ፳፫፤ ፡፡
በአዲስ አበባ በኢትዮጵያና በመላው ዓለም ክብረ በዓሉ የሚከበርባቸው #፷፬ ፡፡
(ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ አሳውቁን)
© ገዳማትና አድባራት Monasteries and Churches
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#፴፫ ፡፡
፩. ሣሎ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ (ከ186 ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው)
አድራሻው፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሣሎ፥ በቶታል ገባ ብሎ፤
ታክሲ፤ ከመገናኛ(ከፒያሳ) → ሳሪስ /ቃሊቲ/ → ሣሎ፤

፪. መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻው፤ አራዳ ክፍለ ከተማ፥ ፒያሳ፥ ዳግማዊ ምኒልክ አደባባይ፤
ታክሲ፤ ከማንኛውም አዲስ አበባ አቅጣጫ → ፒያሳ /ጊዮርጊስ/፤

፫. (ቤተል) ደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ቤተል፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ ሸዋ ዳቦ ቤት (ጦር ኀይሎች) → ቤቴል፡

፬. ፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ብረት ድልድይ፤
ታክሲ፤ ከአራዳ ጊዮርጊስ (ከ4 ኪሎ) (ከ6 ኪሎ) → ፈረንሳይ→ ብረት ድልድይ፡፡

፭. ኮተቤ ሃገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ፥ ቅድስት ማርያምና ቅድስት መግደላዊት ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አንቆርጫ፤
ታክሲ፤ ከአራዳ ጊዮርጊስ (ከ4 ኪሎ) (ከ6 ኪሎ) → ፈረንሳይ→ አንቆርጫ፡፡

፮. ኮተቤ ደብረ ልዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅድስት ኪዳነ ምሕረትና አቡነ ሀብተ ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አባዶ፥ ካራ፤
ታክሲ፤ ከመገናኛ → ኮተቤ/አባዶ/ካራ፡፡

፯. ቦሌ ገርጂ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ፤ (በ2012ዓ.ም. የ24ት ሰፈር ወጣቶች ሰማዕት ኾኑት በክብር ያረፉበት ደብር)
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ገርጂ፤
ታክሲ፤ ከመገናኛ → ገርጂ፡፡

፰. ቦሌ አየር ማረፊያ መንበረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ አየር ማረፊያ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → (መገናኛ ንግድ ባኩ ጋራ) → ቦሌ አየር ማረፊያ (ቡልቡላ ማርያም በሚለው ታክሲ)፡፡

፱. ቦሌ ሰሚት ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ሰሚት ኮንዶሚኒየም፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → መገናኛ → ሰሚት ኮንዶሚኒየም፡፡

፲. ቦሌ አራብሳ ዋሻ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ አራብሳ፥ ዐደባባዩ ጋራ፥ ወንዙን ተሻግሮ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → መገናኛ → አራብሳ (ኮንዶሚንየም /ዐደባባዩ ጋራ/)፡፡

፲፩. ቦሌ ቡልቡላ ምዕራፈ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስና ኪዳነ ምሕረት አንድነት ገዳም፤
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ቦሌ ቡልቡላ ኮንዶሚኒየም፥ ቡልቡላ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ጋራ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → /መገናኛ/ → ሳሪስ → ቦሌ ቡልቡላ፡፡

፲፪. ቱሉ ዲምቱ ደብረ ሰላም ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ አቃቂ/ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ኬላ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → ቱሉ ዲምቱ፡፡
ወይም፤ ከመገናኛ → ቱሉ ዲምቱ (በ… መንገድ)፡፡

፲፫. አያት 49 ጀልዱ ቅዱስ ጊዮርጊስና ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ አያት ጠበል (አያት 49)፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → መገናኛ → አያት ጠበል → አያት 49፡፡

፲፬. ደብረ መዊዕ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ሐና፥ ማንጎ ሰፈር፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ሐና /ማንጎ ሰፈር/፡፡

፲፭. ላፍቶ ደብረ መንክራት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ በላይ ሀኮማል ሪል እስቴት አጠገብ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → በላይ ሀኮማል ሪል እስቴት፡፡

፲፮. አስኮ ደብረ መንክራት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አስኮ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ(ዊንጌት) → አስኮ፡፡

፲፯. ፉሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ ሁለት ኮንዶሚኒየም፥ ንብ ባንክ ፉሪ ቅርንጫፍ ገባ ብሎ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ /ጀሞ/፡፡

፲፰. አስኮ ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለምና ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አስኮ አዲስ ሰፈር፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ(ዊንጌት) → አስኮ አዲስ ሰፈር፡፡

፲፱. ፔፕሲ ፍል ውሃ ደብረ መዊዕ ጊዮርጊስ እና አርሴማ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ማንጎ ፍል ውሃ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ማንጎ ፍል ውሃ፡፡

ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#፠፨፠ ፤
፳. ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ፥ መስቀል ዐደባባይ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቦሌ፡፡

፳፩. መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ ሽርሜዳ፤
ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ(መገናኛ) → ሽርሜዳ → ቊስቋም፡፡

፳፪. ለቡ ደብረ ታቦር በዓለ ወልድና አበ ብዙኃን አብርሃም ገዳም፤
አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ለቡ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ለቡ፡፡

፳፫. ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ ወቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ፥ ጄነራል ዊንጌት ት/ቤት፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ(ከመርካቶ) → አስኮ/ዊንጌት/፡፡

፳፬. ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ፥ መስቀል ፍላወር (ጎተራ) (አጎና ሲኒማ)፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጎተራ ሳሪስ፡፡

፳፭. ኮተቤ ደብረ ልዑል ዳግማዊ ቁልቢ ቅዱስ ገብርኤልና ኆኅተ ሰማይ ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ኮተቤ፥ መሳለሚያ፤
ታክሲ፤ ከመገናኛ → ኮተቤ መሳለሚያ፡፡

፳፮. ጎፋ ቤዛ ብዙኃን ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጎፋ ካምፕ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጎፋ ካምፕ፡፡

፳፯. ቀበና ምሥራቀ ፀሐይ መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ አራዳ ክፍለ ከተማ፥ ቀበና፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቀበና (በመገናኛ ታክሲ)፡፡

፳፰. መሪ አያት ምሥራቀ ፀሐይ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ መሪ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → መሪ/አያት/፡፡

፳፱. ፈለገ ዮርዳኖስ ዮሐንስ መጥምቅና ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ 3፥ መስታወት ፋብሪ ጀርባ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ(ሜክሲኮ) → ጀሞ 3፡፡

፴. ቃላቲ ደብረ ገነት ሚካኤል እና ደብረ ቋስቋም ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ ሰፈረ ገነት፡፡

፴፩. ሐመረ ወርቅ ማርያም እና አርሴማ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ወርቁ ሰፈር፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ ወርቁ ሰፈር፡፡

፴፪. ጀሞ ፈለገ ኮቦር ሥላሴ እና ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ አለም ባንክ አንፎ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ ሸዋ ዳቦ ቤት → አለም ባንክ፡፡

፴፫. ላምበረት ደብረ ፀሐይ አቡነ አረጋዊ ወገብረ መንፈስ ቅዱስ ወአርሴማ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ላምበረት፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → መገናኛ → ላምበረት፡፡

ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
© ገዳማትና አድባራት Monasteries and Churches
#፳፯ #ጥንታውያን ፡፡
(በዘመነ አስተርእዮ የሚወጡ ታቦታት በአንዳንድ የሃገራችን ክፍሎች እንደ ጥምቀት በዓል ታቦታቱ ወደ ትምቀተ ባሕር በመውረድ ነው የሚያከብሩት)
፩. ብልባላ ጊዮርጊስ፤ (ከ1500 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያለው/ላሊበላ ከማነጹ 600 ዓመታት በፊት የታነጸ፥ ከ485 ዓ.ም እስከ 536 ዓ.ም. በንጉሥ አፄ ካሌብ ከአንድ ቋጥኝ ተፈልፍሎ የታነጸ)፡፡
አድራሻ፤ ላስታ ላሊበላ ሃገረ ስብከት፥ ብልባላ ወረዳ፥ ብልባላ ከተማ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ → ብልባላ (በሰቆጣ መስመር) (ከላሊበላ 30 ኪ.ሜ.)፡፡

፪. ደብረ ሮሐ ቅዱስ ላሊበላ ቤተ ጊዮርጊስ፤
አድራሻ፤ ላስታ ላሊበላ ሃገረ ስብከት፥ ላሊበላ ከተማ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ፡፡

፫. መሎጥ አምባ ጊዮርጊስ (አንድ መግቢያ እና መውጫ ያለው፤ ዐፄ ይኵኖ አምላክ ከመንገሡ በፊት በአያቱ መሐሪዉ አምላክ በግዞት የታሰረበት፤)
አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ዋድላ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ዋድላ፡፡

፬. ደብረ ድማኅ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም፤
(በሚያዝያ ጊዮርጊስ ዕፁብ ለሰሚ የሚል በዋሻ ታቦተ ሕጉ ተአምር የሚሠራበት)
አድራሻ፤ ምሥራቅ ጎጃም ሃገረ ስብከት፥ ደብረ ድማኅ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር መንገድ (በሞጣ መስመር) → ደብረ ድማኅ፡፡

፭. ሞጣ ጊዮርጊስ፤
አድራሻ፤ ምሥራቅ ጎጃም ሃገረ ስብከት፥ ሞጣ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር መንገድ (በሞጣ መስመር) → ሞጣ፡፡

፮. መሐል ዘጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ፤
አድራሻ፤ ምዕራብ ጎጃም (ባህር ዳር) ሃገረ ስብከት፥ ባሕር ዳር ከተማ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር፡፡

፯. ባሕር ዳር ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ፤
አድራሻ፤ ምዕራብ ጎጃም (ባሕር ዳር) ሃገረ ስብከት፥ ባሕር ዳር ከተማ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር፡፡

፰. ዋሻ ነጎድጓድ ጊዮርጊስ ገዳም፤ (በ16ኛው ክ/ዘመን በዐፄ ልብነ ድንግል ዘመን የተመሠረተ፤ ፈዋሽ ጠበል ያለበት)
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ ላሎ ምድር፤ (ከአ.አ. 293 ኪ.ሜ.)
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መንዝ ላሎ → ወገሬ ከተማ → ዝንዝ (ጦጥ) (ዘብር)፡፡

፱. ጎንደር እልፍኝ ጊዮርጊስ፤ (ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ)
አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፤ ፋሲለደስ ቤተ መንግሥት፡፡

፲. ጎንደር ቀዳሜ አድባራት አበራ ጊዮርጊስ፤ (ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ) (በጎንደር ከተማ ታቦቱ ወደ ጥምቀተ ባሕር ወርዶ የሚከበርበት)
አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፥ ኮሌጅ፡፡

፲፩. ደሴ ጊዮርጊስ፤
አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ደሴ ከተማ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ፡፡

፲፪. ወራኢሉ ጊዮርጊስ፤
አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ወራኢሉ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ወራኢሉ፡፡

፲፫. ግሸን ጊዮርጊስ ፤
አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ አምባሰል ወረዳ፥ ግሸን፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ግሸን፡፡

፲፬. ዐድዋ ደብረ ጽጌ ሰሎዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን፤ (የካቲት 23 አባቶቻችን ለዐድዋ ጦርነት ዕለት ቅዳሴ ያስቀደሱበት ገዳም)
አድራሻ፤ ጋሞ ጎፋ ሃገረ ስብከት፥ ካምቦ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና አውቶቡስ ተራ → ጋሞ ጎፋ (አርባ ምንጭ) → ካምቦ፡፡

፲፭. ጅሩ ገርባ ጊዮርጊስ ገዳም፤
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ጅሩ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት (መርካቶ) አውቶቡስ ተራ → ጅሩ፡፡

፲፮. ጋሞ ጎፋ ካምባ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ጋሞ ጎፋ ሃገረ ስብከት፥ ካምቦ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና አውቶቡስ ተራ → ጋሞ ጎፋ (አርባ ምንጭ) → ካምቦ፡፡

፲፯. ቆላድባ ኳሬና ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን፤
አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ደምቢያ ወረዳ (ማሩ ቀመስ)፥ ቆላ ድባ ከተማ ፤ (ከጎንደር ከተማ 35 ኪ.ሜ.)
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር አዘዞ አውቶቡስ ተራ → ቆላድባ፡፡

፲፰. ደብረ ታቦር ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ደብረ ታቦር
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ታቦር፡፡
ወይም፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር → ወረታ → ደብረ ታቦር፡፡

፲፱. አገው ምድር ሳሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ አዊ ዞን ሃገረ ስብከት፥ አገው ምድር (አዊ) (ምዕራብ ጎጃም)
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → አዊ (በቡሬ፥ ባሕር ዳር መስመር)፡፡

፳. ድሬዳዋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ድሬደዋ ሃገረ ስብከት፥ ድሬደዋ ከተማ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ድሬደዋ፡፡

፳፩. ደብረ ሲና ጉርጅ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ሲያ ደብር፥ ዋዩ ወረዳ
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ሆለታ/ኢንጪኒ/፡፡

፳፪. ኢንጭኒ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ኢንጪኒ፤ (ከአ.አ. በሆለታ 65 ኪ.ሜ.)
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን → ደነባ → ሲያ ደብር → በእግር፡፡

፳፫. ኢንጭኒ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ኢንጪኒ፤ (ከአ.አ. በሆለታ 65 ኪ.ሜ.)
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን → ደነባ → ሲያ ደብር → በእግር፡፡

፳፬. ቆሪቻ ኮቲቻ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ጮቢ ወረዳ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → በአምቦ መስመር (ጊንጪ) → ጮቢ → ቆሪቻ ኮቲቻ፡፡

፳፭. ጊዶሌ የጋርዱላው (የዐድዋው) ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
፳፮. ደብረ መንክራት አንዳሳ ቅዱስ ጊዮርጊስ፡፡
(አንዳሣ፤ ሙት አንሣ፡፡ የተባለለት ለሆድ ሕመምና ለሥራይ ፍቱን ፈዋሽ የሆነ፤ ከዐባይ ወንዝ መሃል ላይ በሚደንቅ ተአምር የሚፈልቅ አምቦ ጠበል ያለበት)
፳፯. ሸቆል ወለባ ጊዮርጊስና ማርያም ቤ/ን (ደላንታ)
፳፰. ያበደማን ጊዮርጊስ ቤ/ን፤
፳፱. ደንደገብ ጊዮርጊስ ቤ/ን፤
፴. አትርፎ ጊዮርጊስ ቤ/ን፤

ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#፩ ፡፡
፩. ራስ አኬልዳማ ደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ/ክ፤ (ዱባይ)
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
© ገዳማትና አድባራት Monasteries and Churches
(ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ በውስጥ አሳውቁን)
/ /
/ /
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

Address

Addis Ababa
26909CODE1000

Telephone

+251907909192

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ገዳማትና አድባራት Monasteries and Churches posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share