የረቢ መካነ ጎልጎታ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የረቢ መካነ ጎልጎታ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት

የረቢ መካነ ጎልጎታ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የረቢ መካነ ጎልጎታ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት, Religious organisation, Addis Ababa.

"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6 በዛሬው ዕለት መስከረም 7 ቀን 2019 ዓ.ም ጋብቻቸውን በሥርዓተ...
17/09/2026

"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6

በዛሬው ዕለት መስከረም 7 ቀን 2019 ዓ.ም ጋብቻቸውን በሥርዓተ ተክሊል በደብራችን ለፈጸሙት የሰንበት ትምሕርት ቤታችን አባል ለሆነችው ለእህታችን ለወ/ት ቅድስት ብርሐኑ እና ለባለቤቷ ለአቶ ኢሳያስ ከፍያለው ትዳራቸው የተባረከ እንዲሆን ሰንበት ትምሕርት ቤታችን መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡

የረቢ መ/ጎ መድኃኔዓለም ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት

"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6 በዛሬው ዕለት መስከረም 3 ቀን 2019 ዓ.ም ጋብቻቸውን በሥርዓተ...
13/09/2026

"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6

በዛሬው ዕለት መስከረም 3 ቀን 2019 ዓ.ም ጋብቻቸውን በሥርዓተ ተክሊል በደብራችን ለፈጸሙት የሰንበት ትምሕርት ቤታችን አባል ለሆነችው ለእህታችን ለወ/ት ሠናይት ፀጋዬ እና ለባለቤቷ ለአቶ አማኑኤል ወ/ሚካኤል ትዳራቸው የተባረከ እንዲሆን ሰንበት ትምሕርት ቤታችን መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡

የረቢ መ/ጎ መድኃኔዓለም ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ ዓውደ ዓመት ዘዕሥ...
10/09/2026

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ ዓውደ ዓመት ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወተስዓቱ ዓመተ ምሕረት፤

በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣
ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣
የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣
በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣
እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፣

በየዓመቱ የይቅርታ እጁን እየዘረጋ የሚመግበን እግዚአብሔር አምላካችን እንኳን ከዘመነ ማርቆስ ሁለት ሺሕ ዓሥራ ስምንት ዓመተ ምሕረት ወደ ዘመነ ሉቃስ ሁለት ሺሕ ዓሥራ ዘጠኝ ዓመተ ምሕረት በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!
“ወይእዜኒ ነስሑ ወተጠመቁ፤ ወይደመሰስ ለክሙ ኃጢኣትክሙ፤ ወይመጽእ ለክሙ መዋዕለ ሣህል እምቅድመ ገጹ ለእግዚአብሔር፤ከጌታ ፊት የመጽናናት ዘመን እንዲመጣላችሁ፣ ኃጢአታችሁም እንዲደመሰስ አሁንም ንስሐ ግቡ ተመለሱም” (የሐ.ሥራ ፫፡፲፱)

የሰው ልጅ በስሑት ስራውና አእምሮው ምክንያት የኃጢአት ማዕበል በሚያናውጠው ባሕረ ዓለም እንደሚኖር ይታወቃል፤ የዓለሙ ባሕር በማዕበሉ በተናጠ ቁጥር በመርከቡ ተሳፍረው የሚጓዙ ሁሉ ጭንቀት ላይ መውደቃቸው የማይቀር ነው፤ በዚህ ጊዜ የሚያጽናና የቊርጥ ቀን ረዳትና ኃይል ያስፈልጋቸዋል፤ ሆኖም ረዳት በፍጥነት እንዲደርስላቸው መጮኽና መጣራት ከነሱ ያስፈልጋል፤ የምንኖርባት ዓለም ወይም ፕላኔት የክፋትና የጭካኔ ማዕበል በእጅጉ እየበረታባት መጥቶአል፤ ዓለማችን በስጋትና በፍርሓት፣ በራስ ወዳድነትና ባለመተማመን ተከባለች፣ በመሆኑም ዓለማችን ከምን ጊዜውም በላይ የመጽናናት ዘመን እንዲመጣላት ትሻለች፤ እግዚአብሔር ለፍጥረቱ የሚያስፈልገውን ሁሉ አሟልቶ የሰጠ አምላክ እንደሆነ በግልጽ የሚታይ ነው፤ ይሁንና እግዚአብሔር ከኛ የሚፈልጋቸው ብዙ ነገሮች እንዳሉ በማያሻማ ሁኔታ አሳውቆአል፤ ከእነሱም መካከል በእውነተኛው መንፈስ ንስሐ መግባት፤ መጸጸትና መመለስ ናቸው፤ የዓለምን ሕዝብ በወሳኝነት ማጽናናት የሚችል እግዚአብሔር ብቻ ነው፤ እኛ ራሳችንን በራሳችን ለማጽናናት እንኳ በቂና ዘላቂ ዓቅም የሌለን ውሱኖች ነን፤ ይህንን እውነት ዓውቀን የእርሱን ርዳታ እንድንሻ እግዚአብሔር ይፈልጋል፤ ይህንንም ከልብ በመጸጸትና ከቀደመው ስሑት ተግባራችን በመመለስ በፊቱ ተንበርክከን መታዘዛችንን በተጨባጭ እንድናሳይ ይፈልጋል፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት!

እግዚአብሔር ከታላቅ ቸርነቱ የተነሣ የመታደስ ዘመንን በየዓመቱ ከመስጠት አልተቈጠበም፤ እንደ ሁሉጊዜ አሁንም አዲሱን ዘመን ባርኮ ሰጥቶናል፤ ሆኖም አዲሱ ዘመን የመጽናናት ዓመት እንዲሆንልን የእኛ ተሳትፎ ወሳኝ ሚና እንዳለው መዘንጋት የለብንም፤ ከሁሉ በፊት ያለፈውን ዓመት እንደ ግልም፣ እንደ ማኅበረ ሰብም፣ እንደ ሃገርም፤ እንደ ሃይማኖትም በኅሊናችን ልናስበውና ልንገመግመው ይገባል፤ ያለፈውን ዓመት በንጹህ ኅሊናችን በጥልቀት ስንገመግመው፤ የመጣንበትና ያለፍንበት ስለሆነ ኮለል ብሎ በፊታችን ይታያል፤ ጥቅሙም ሆነ ጉዳቱ በሙሉ ከኛ የራቀ ስለማይሆን ዳኝነት ለመስጠትና ውሳኔ ለመወሰን አንቸገርም፤ በመሆኑም ለፈጸምነው ስሕተት ይቅርታን ከመጠየቅ ባሻገር ድጋሚ ላንደግመው መወሰንና ለተግባራዊነቱ በጽናት መቆም አለብን፤ እኛ በዚህ ደረጃ ከቀደመው ስሕተታችን ተጸጽተን ንስሐ ከገባን እግዚአብሔር ከኛ የሚፈልገውን አግኝቶአል ማለት ነው፤ በመካከላችንም ትክክለኛ መግባባት ተፈጥሮአል ማለት ነው፤ በዚህ ጊዜ እሱም ዘላቂ የሆነ የመጽናናት ዘመን ለኛ ይሰጣል፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት!

በዓለሙ እንዳለው ሁሉ እኛም ወዲያና ወዲህ ከሚያወዛውዝ ፈተና አላመለጥንም ያለፈውን ዓመት በንጹሁ አእምሮአችን ስንመዝነው፤ ጥሩ የሚባል አልነበረም፤ በየአካባቢው ግጭቶች የቀጠሉበት፣ የሰው ደም የፈሰሰበት፣ ዕገታዎች የተፈጸሙበት፣ ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት የተቃጠሉበት፣ ምእመናን የተገደሉበትና የተፈናቀሉበት፣ ስጋት ያየለበት፣ ኑሮም የተወደደበት፣ ሌላም ሌላም ለሰው ልጅ የማይበጁ ነገሮች የተከሠቱበት ዓመት አሳልፈናል፤ ታዲያ አዲሱን ዘመን ስንቀበል እነዚህን ሁሉ እንዳሉ ይዘናቸው እንቀጥል ይሆን? ይህስ ከሆነ ‹‹እንኳን ለአዲሱ ዘመን አደረሳችሁ›› መባባሉ ትርጉም ይኖረው ይሆን? እንዲህስ ልንሆን ፈጽሞ አይገባም፤ ይልቁንም ባለፈው ዓመት የሆኑትን ሁሉ ላንደግማቸው ሁላችንም እንወስን፤ እነሱንም ማስቀረት እንችላለን፤ ምክንያቱም ችግሮቻችን በሙሉ ሰው ሰራሽ እንጂ የተፈጥሮ አይደሉም፤ ሰው ሰራሽ ችግሮች ደግሞ በሰው እንደመጡ ሁሉ በሰው ሊቀሩ የሚችሉ ናቸውና እናስቀራቸው፤ ጦርነቱን፣ ዕገታውን፣ ጥላቻውን፣ ፉክክሩን፣ እልከኝነቱን፣ ጭካኔውን ራስ ወዳድነቱን ግድያውን፣ አብያተ ሃይማኖት ማቃጠሉንና ማፍረሱን እኛው እንዳመጣነው እኛው ማስቀረት እንችላለን፤ ስንተወው እኮ ይቀራል፡፡

ስለሆነም ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ያላችሁ ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን ሁሉ ኢትዮጵያን እንዳለች የጋራ ዕድልና ሃብት አድርጋችሁ ተቀበሉ፤ ሌላውን ረጅም ጊዜ ሰጥታችሁም ቢሆን በውይይትና በመግባባት እየፈታችሁ በአንድነት ቀጥሉ፤ በይቅርታመንፈስ በአንድነት ተቃቅፎ ከመቀጠል ውጭ ሌላ የተሻለ ዕድል እንደሌለ በውል ተገንዘቡ፤ ለዚህ ሁላችሁም የበኩላችሁን ልባዊ ጥረት ከማድረግ አትቈጠቡ ብለን ከልብ እንመክራለን፡፡

በመጨረሻም፤

ለሁሉም መድኃኒቱ ቀና አእምሮ ነውና በአዲሱ ዓመት እግዚአብሔር ቅንና በጎ አሳቢ አእምሮ እንዲሰጠን በሱም ያሉብንን ጉድለቶች አርመንና አስተካክለን ሰላም የሰፈነበትን የመጽናናት ዘመን ማየት እንችል ዘንድ እግዚአብሔር አምላካችንን እንለምን፤ እኛም በንስሐ እንመለስ እያልን በድጋሚ እንኳን ለአዲሱ ዘመን በሰላም አደረሳችሁ በማለት አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን ፡፡
እግዚአብሔር መልካም አዲስ ዘመን ያድርግልን፡፡
እግዚአብሔር ኣምላካችን ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ኣሜን!!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ
ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣
መስከረም ፩ ቀን ፳፻፲፱ ዓ.ም
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

የሰንበት ትምህርት ቤታችን 48ኛ ዓመታዊ በዓል የመዝጊያ መርሐግብር በዛሬው ዕለት ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም  ከጠዋቱ 3፡30 ጀምሮ በደብራችን ሰ/ት/ቤት እና ስብከተ ወንጌል አዳራሽ  በታላቅ...
30/08/2026

የሰንበት ትምህርት ቤታችን 48ኛ ዓመታዊ በዓል የመዝጊያ መርሐግብር በዛሬው ዕለት ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡30 ጀምሮ በደብራችን ሰ/ት/ቤት እና ስብከተ ወንጌል አዳራሽ በታላቅ ድምቀት ተከናወነ፡።

መርሐግብሩ በደብራችን አስተዳዳሪ መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ገ/መድኅን መሪነት በጸሎተ ወንጌል የተከፈተ ሲሆን በማስከተልም የመክፈቻ መዝሙር በሰ/ት/ቤታችን አባላት ቀርቧል፡፡ በመቀጠልም የሰ/ት/ቤቱ የ2018 ዓ.ም ዋና ዋና የሥራ እንቅስቃሴ ሪፖርት በሰ/ት/ቤ/ቱ ዋና ጸሐፊ የቀረበ ሲሆን ትምህርተ ወንጌል በደብረ አሜን ተክለ ሃይማኖት ቤ/ክ ሰባኬ ወንጌል በመምህር ዲ/ን እስጢፋኖስ ተሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም ኪነ ጥበባዊ ዝግጅቶች እና ወረብ በሰ/ትቤቱ አባላት ቀርበዋል። በመጨረሻም በሰ/ት/ቤ/ቱ ጽ/ቤት በተለያዩ አገልግሎት ለተሳተፉ እና በትምህርታቸው ከፍተኛ ውጤት ላመጡ አባላት እና በበጎ አድራጎት ሥራ እና በልዩ ልዩ ተግባራት የሰ/ት/ቤቱን አገልግሎት ላገዙ አካላት የሽልማት እና የዕውቅና መርሐግብር ተከናውኖ መርሐግሩ በጸሎት ተፈጽሟል፡፡

የ48ኛ ዓመታዊ በዓል መርሐግብሩን የደብራችን አገልጋይ ካህናት ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና በርካታ ቁጥር ያለው ምዕመናን ታድሞታል፡፡

የረቢ መድኃኔዓለም ሰንበት ት/ቤት  ከተመሰረተ 48 ዓመት ሞላውእንኳን ለ48ኛው ዓመት ከብረ በዓል አደረሰን! 48ኛ የምስረታ በዓላችን የመዝጊያ መርሐግብር ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም ከ3:00...
26/08/2026

የረቢ መድኃኔዓለም ሰንበት ት/ቤት ከተመሰረተ 48 ዓመት ሞላው

እንኳን ለ48ኛው ዓመት ከብረ በዓል አደረሰን!

48ኛ የምስረታ በዓላችን የመዝጊያ መርሐግብር
ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም ከ3:00 ጀምሮ ይከናወናል

በዓላችንን በአንድነት እንድናከብር በአክብሮት ጠርተናችኋል

የ2018 ዓ.ም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዕርገት በዓል አስመልክቶ በሰንበት ትምህርት ቤታችን ልማት እና በጎ አድራጎት  ክፍል አስተባባሪነት በአጥቢያችን የሚገኙ ነዳያንን ወገኖቻች...
23/08/2026

የ2018 ዓ.ም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዕርገት በዓል አስመልክቶ በሰንበት ትምህርት ቤታችን ልማት እና በጎ አድራጎት ክፍል አስተባባሪነት በአጥቢያችን የሚገኙ ነዳያንን ወገኖቻችን ጾም የማስፈሰክ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ተከናወነ። ይህ ዓይነቱ መርሐግብር በጌታችን ልደትና ትንሣኤ በዓልም የሚከናወን ሲሆን በተጨማሪም ሰንበት ትምህርት ቤታችን በስሩ ለሚገኙ ነዳያን በቋሚነት ምገባ ያደርጋል።

+++እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ+++አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ነሐሴ ዐሥራ ስድስት በዚች ቀን አምላክን የወለደች...
21/08/2026

+++እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ+++

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ነሐሴ ዐሥራ ስድስት በዚች ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ድንግል ማርያም ሥጋዋ ወደ ሰማይ ያረገበት መታሰቢያዋ ሆነ፡፡

ከዕረፍቷም በኋላ ከእርሳቸው ስለመለየቷ ሐዋርያት ፈጽሞ እያዘኑ ነበር፡፡

ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ተገለጠላቸው እርሷን በሥጋ ያዩ ዘንድ እንዳላቸውም ተስፋ ሰጣቸው፡፡

ወንጌላዊ ዮሐንስም እስያ በሚባል አገር እያስተማረ ሳለ በነሐሴ ወር ዐሥራ ስድተኛ ቀን ተድላ ደስታ ወደአለባት ገነት በመንፈስ ቅዱስ ተነጠቀ፡፡ የክብር ባለቤት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን የእመቤታችን ማርያም ሥጋዋ ካለበት ከዕፀ ሕይወት ዘንድ ተቀምጦ አየው፡፡ የንጽሕት እናቱንም ሥጋ ታወጣ ዘንድ ምድርን እንዲጠሩዋት ሰባቱን የመላእክት አለቆች አዘዛቸው እነርሱም የንጽሕት እናቱን ሥጋ ታወጪ ዘንድ እግዚአብሔር አዞሻል አሏት፡፡

ያን ጊዜም ከዕፀ ሕይወት በታች ካለ መቃብር የእመቤታችን ማርያም ሥጋዋ ወጣ፡፡

የክብር ባለቤት ጌታችንም እንዲህ እያለ አረጋጋት፤ የተወደድሽ የወለድሽኝ እናቴ ሆይ ዘላለማዊ ወደ ሆነ መንግሥተ ሰማያት አሳርግሽ ዘንድ ነዪ፡፡

ያን ጊዜም በገነት ያሉ ዕፅዋት ሁሉም አዘነበሉ፤ መላእክት፤ የመላእክት አለቆች ጻድቃን ሰማዕታትም እየሰገዱላትና ፈጽሞ እያመሰገኗት አሳረጓት፡፡

አባቷ ዳዊትም ንግሥት እመቤታችን ወረቀ ዘቦ ለብሳ ደርባ ደራርባ በቀኝህ ትቀመጣለች እያለ በበገና አመሰገናት፡፡

በኪሩቤል ሠረገላ ተቀምጣ ከዐረገች በኃላ በልጆችዋና በፈጣሪዋ ቀኝ በታላቅ ክብር ተቀመጠች፡፡

ወንጌላዊ ዮሐንስም ከእርሷ በረከትን ተቀብሎ ሰግዶላት ተመልሶ ከሰማይ ወረደ፤ ሐዋርያትን ተሰብስበው ስለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ ፈጽሞ ሲያዝኑና ሲተክዙ አገኛቸው፡፡ እርሱም እንዳየ እንደሰማ ሥጋዋንም በታላቅ ክብር በምስጋና እንዳሳረጓት ነገራቸው፡፡

ሐዋርያትም በሰሙ ጊዜ ዮሐንስ እንዳየና እንደሰማ ባለማየታቸውና ባለመስማታቸው እጅግ አዘኑ፡፡

ከዚህም በኋላ እያዘኑ ሳሉ እነሆ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠላቸውና የፍቅር የአንድነት ልጆች ሰላም ይሁንላችሁ ስለ እናቴ ማርያም ሥጋ ለምን ታዝናላችሁ፡፡ እነሆ እኔ እርስዋን በሥጋ ላሳያችሁ ልባችሁም ደስ ሊለው ይገባዋል አላቸው፡፡ ይህንንም ብሎ ከእርሳቸው ዘንድ ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡

ሐዋርያትም ዓመት ሙሉ ቆዩ የነሐሴም ወር በባተ ቀን ለሐዋርያት ዮሐንስ እንዲህ አላቸው፡፡ አምላክን የወለደች የእመቤታችንን ሥጋዋን ለማየት የተዘጋጀን አድርጎ ያሳየን ዘንድ ኑ ይህን ሁለት ሱባዔ በጾም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እንለምነው በልጅዋ በወዳጅዋ ቀኝ ተቀምጣ አይተን በእርሷ ደስ እንዲለን፡፡

በዚያን ጊዜም ዮሐንስ እንዳላቸው በጾም በጸሎት ሱባዔ ያዙ፤ የነሐሴ ወር እንደዛሬ ዐሥራ ስድስተኛ ቀን በሆነ ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉንም ሐዋርያት ወደ ሰማይ አወጣቸው፡፡ በታላቅ ክብር በተወደደ ልጅዋ ቀኝ ተቀምጣ ከሥጋዋ ተዋሕዳ ተነሥታ እመቤታችን ማርያምን አዩዋት፡፡ እጆቿንም ዘርግታ የከበሩ ሐዋርያትን እያንዳንዳቸውን ባረከቻቸው በልባቸውም እጅግ ደስ አላቸው፡፡

የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በከበረ ሥጋውና ደሙ ላይ ሠራዔ ካህን ሆነ፡፡ እስጢፋኖስም አዘጋጀ፤ ዮሐንስም በመፍራት ቁሙ አለ፡፡ ሁሉም ሐዋርያት በመሰዊያው ዙሪያ ቆሙ፤ በዚያን ጊዜ ከቶ እንደርሱ ሆኖ የማያውቅ ታላቅ ደስታ ሆነ፡፡

ጌታችንም የቅዳሴውን ሥርዓት በፈጸመ ጊዜ ሥጋውንና ደሙን አቀበላቸው፡፡

ከዚያም በኪሩቤልና በሱራፌል ሠረገላ ተቀምጣ በምታርግ ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱን እመቤታችን ማርያምን እንዲህ ብሎ ተናገራት፡፡ በዚች ቀን የሆነ የዕርገትሽን መታሰቢያ በዓለም ውስጥ እንዲሰበኩ ልጆችሽ ሐዋርያትን እዘዣቸው፡፡ መታሰቢያሽን የሚያደርገውን ሁሉ ተጠብቆም በዚች ቀን ቅዱስ ቁርባን የሚቀበለውን ኃጢአቱን እደመስስለታለሁ፡፡ የእሳትን ሥቃይ ከቶ አያያትም መታሰቢያሽን ለሚያደርግ ሁሉ በዚች ቀን ለድኆች በስምሽ ለሚመጸውት ቸርነቴ ትገናኘዋለች ይህም ሥጋሽ ወደ ሰማይ ያረገበት ነው፡፡

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ክብር ይግባውና ጌታችንን እንዲህ አለቸው ልጄ ሆይ እነሆ በዓይኖቻቸውም አዩ፤ በጆሮዎቻቸውም ሰሙ፤ በእጆቻቸው ያዙ ሌሎችም ታላላቅ ድንቆች ሥራዎችን አዩ፡፡

እመቤታችንም ይህን ስትናገር ጌታችን ሰላምታ ሰጥቷቸው በታላቅ ደስታ ወደ ደብረ ዘይት ተመለሱ፡፡

የተወደዳችሁ ወንድሞች ሆይ በፍጹም ደስታ መታሰቢያዋን እናደርግ ዘንድ ይገባናል፡፡ እርሷ ስለ እኛ ወደተወደደ ልጅዋ ሁልጊዜ ትማልዳለች፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት ይማረን፡፡ በረከቷም ሐዋርያት በሰበሰበዋት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች ከሁላችን ጋር ይሁን ለዘላለሙ አሜን፡፡

ምንጭ፡-ስንክሳር ዘወርኀ ነሐሴ

የቀዳማይ ክፍል ተማሪዎች ምዝገባ ተጀመረ በሰ/ትቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረትከነሐሴ 17 - መስከረም 17/2019 ዓ.ም
21/08/2026

የቀዳማይ ክፍል ተማሪዎች ምዝገባ ተጀመረ

በሰ/ትቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት

ከነሐሴ 17 - መስከረም 17/2019 ዓ.ም

እንኳን አደረሳችሁ✞ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምሥጢረ መለኮቱን ለገለጠበት ለበዓለ ደብረ  ታቦር እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን ✞''ታቦር ወአርሞንዔም በስመ ዚአከ ይትፌሥሑ፥ ወይሴ...
18/08/2026

እንኳን አደረሳችሁ

✞ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምሥጢረ መለኮቱን ለገለጠበት ለበዓለ ደብረ ታቦር እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን ✞

''ታቦር ወአርሞንዔም በስመ ዚአከ ይትፌሥሑ፥ ወይሴብሑ ለስምከ፥ መዝራዕትከ ምስለ ኀይል''

ትርጉም፦
ታቦር እና አርሞንዔም በስምህ ደስ ይላቸዋል ስምህንም ያመሰግናሉ ክንድክ ከኃይልክ ጋር ነው።
መዝ 88፥12–14

እንኳን ለሰንበት ትምህርት ቤታችን 48ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!የሰ/ት/ቤታችን 48ተኛ ዓመታዊ በዓል ዋናው የመዝጊያ መርሐግብር ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ ...
17/08/2026

እንኳን ለሰንበት ትምህርት ቤታችን 48ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!

የሰ/ት/ቤታችን 48ተኛ ዓመታዊ በዓል ዋናው የመዝጊያ መርሐግብር ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ ይካሄዳል

እርስዎም በዚህ መርሐግብር ይታደሙ ዘንድ በልዑል እግዚአብሔር ስም ጠርተንዎታል።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የረቢ መካነ ጎልጎታ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share