Misrak Ye Amlak Kibir MKC Adama/Nazareth

Misrak Ye Amlak Kibir MKC Adama/Nazareth “እነሆም፥ የእስራኤል አምላክ ክብር ከምሥራቅ መንገድ መጣ፤ ድምፁም እንደ ብዙ ውኆች ይተምም ነበር፥ ከክብሩም የተነሣ ምድር ታበራ ነበር።”
***ሕዝቅኤል 43፥2***

እሁድ የካቲት 8/2018 ዓ.ም ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ የአምልኮ ፕሮግራም።በፀሎት እንዲሁም በማስተባበር እህት ሀና ግርማ በአምልኮ ወ/ም በፀጋው ጋር እግዚአብሔርን አ...
19/02/2026

እሁድ የካቲት 8/2018 ዓ.ም ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ የአምልኮ ፕሮግራም።

በፀሎት እንዲሁም በማስተባበር እህት ሀና ግርማ በአምልኮ ወ/ም በፀጋው ጋር እግዚአብሔርን አምልከናል ቃለ እግዚአብሔር በእህት ገነት ተካፍለናል።

ርዕስ:- የሚያመሰግን አይዘገይም!

የመፅሐፍ ክፍል -ዘፍ 24፥ ከቁ1 ጀምሮ

አብርሐም ለልጁ ለይስሐቅ የምትሆን ሚስት ያመጣለት ዘንድ በቤቱ ሁሉ ላይ አስተዳዳሪ የነበረውን ሎሌውን ላከው።

በአብርሐም ሕይወት እግዚአብሔር ምንም እንኳ የዘገየ ቢመስልም: እግዚአብሔር በራሱ ዘመን ይሰራል።

የአብርሃም ሎሌ የእግዚአብሔርን ምሪት ጠየቀ።

1. እግዚአብሔርን ምሪት መጠየቅ!
✨ ሎሌውም
- ተንበርክኮ ፀለየ
- የአብርሃም አምላክ አለ! (የአብርሃምን አምላክ ያውቀው ነበር)

▪️የያዕቆብ ሚስት ራሄል ምንም እንኳን ከያዕቆብ ጋር ብዙ አመት ያሳለፈች ብትሆንም ከአባቷ ቤት ሲወጡ አማልክትን ደብቃ ይዛ ነበር።

▪️እግዚአብሄርን የሚያሳይ ህይወት ጌታ ይሰጠን! ሎሌው የአብርሀምን አምላክ ኤሎሂምን እንዳወቀው ማለት ነው።

2. ለምነን ከተቀበልን በኋላ እግዚአብሔርን ማመስገን ይኖርብናል።

- እንደለመነ ወዲያው ሴቲቱን አገኘ (እግዚአብሔር ወዲያውኑ ይስማን)
- ከዚያም ተንበርክኮ ሰገደ (አመሰገነ)
- ወላጆችዋሞ ከፈቀዱ በኋላም አመሰገነ።

▪️አስሩ ለምፃሞች ከተፈወሱ በኃላ ለምስጋና የተመለሰው አንዱ ብቻ ነበረ: ለምስጋና የተመለሰውን እንሁን!

3. እግዚአብሔር ካቀናው መንገድ የሚያዛገየውን እምቢ ማለት።

- ወላጆችዋ ማታ ፈቅደው ጥዋት 10 ቀን ትቆይ አሉት: እሱን ግን አታዘግዩኝ አላቸው ።

▪️ጳውሎስ ወደ እናንተ ለመምጣት ፈልጌ ነበር ሰይጣን ግን አዘገየኝ አለ: ዳንኤልም 21 ቀን ፀሎቱ እንደዘገየ መልአኩ አሳውቆት ነበረ።

▪️ፀሎታችንን: ነገራችንን: ሥራችንን የሚያዘገይ ይመታል! ያዘገያችሁን እግዚአብሔር ይመታዋል! ትግል ያበቃል!

8/06/2018 ዓ.ም
📍 ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ

Telegram:- https://t.me/misrak_mkc_adama
Facebook:- https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR
Instagram:- http://Instagram.com/misrak_mkc
TikTok:- https://vm.tiktok.com/ZMA5wBynN/

እሁድ የካቲት 1/2018 ዓ.ም ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ የአምልኮ ፕሮግራም።በፀሎት እንዲሁም በማስተባበር አሸናፊ ቱሉ በአምልኮ በእምነት ታደሰ ጋር በዝማሬ አገልግሎት ...
12/02/2026

እሁድ የካቲት 1/2018 ዓ.ም ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ የአምልኮ ፕሮግራም።

በፀሎት እንዲሁም በማስተባበር አሸናፊ ቱሉ በአምልኮ በእምነት ታደሰ ጋር በዝማሬ አገልግሎት ከቤተ ክርስትያናችን ርኆቦት መዘምራን ህብረት ጋር እግዚአብሔርን ከፍ አድርገናል፤ እግዚአብሔርን አምልከናል ቃለ እግዚአብሔር በወንድም ባዩ ተካፍለናል።

✨እግዚአብሔር በመጀመሪያ ወንጌል የሰበከው ለአብርሀም ነበር።

“መጽሐፍም እግዚአብሔር አሕዛብን በእምነት እንዲያጸድቅ አስቀድሞ አይቶ፦ በአንተ አሕዛብ ሁሉ ይባረካሉ ብሎ ወንጌልን ለአብርሃም አስቀድሞ ሰበከ።”
— ገላትያ 3፥8

ርዕስ :- "ስለ ወንጌል ሁሉን አደርጋለሁ"

1ኛ ቆሮንቶስ 9÷19-23

▪️ሀዋርያው ጳውሎስ ስለወንጌል ✨ራሱን ምን ምን አደረገ!
- ራሱን ባሪያ አድርጓል
- ለአይሁድ እንደ አይሁድ
- ህግ ለሌላቸው ህግ እንደሌለው
- ለደካሞች እንደ ደካም ሆንኩ

▪️ጳውሎስ መብቱን ነው የተወው
ለምን? ሌላውን እጠቅም ዘንድ

እኛ ብዙውን ጊዜ የምንለው ኑ ነው ጌታ ግ ያለው ሂዱ ነው።

“እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።”
— ማቴዎስ 28፥19-20

ጳውሎስ ለሌሎች ሲል በእጆቹ ይደክም ነበር። ሐዋርያት 20÷33-34

“በሥጋ ዘመዶቼ ስለ ሆኑ ስለ ወንድሞቼ ከክርስቶስ ተለይቼ እኔ ራሴ የተረገምሁ እንድሆን እጸልይ ነበርና።”
— ሮሜ 9፥3

▪️ጳውሎስ ወንጌልን ሲሰብክ በሰዎቹ አውድ ነበር የሚያደርገው ወደ አይሁድ ሲሄድ ጢሞቴዎስን ይገርዝ ነበር መገረዝ ባያድንም ለሰዎቹ ሲል ግን ገረዘው ወደ አህዛብ ሲሄድ ደግም ቲቶ ይዞ ይሄድ ነበር።

▪️ጌታ ኢየሱስ ወደ ሰማሪያ የወረደው ያቺ ሴትን ያድን ዘንድ ነበር። ስለዚህ አማኞች ወንጌልን ለማስቀጠል ምን እናድርግ?
- ወደ ቃሉ እንመለስ
- ወደ ጸሎት እንመለስ
- ትህትናን እንጨምር
- መብታችንን ስለሌላው እንተው
- ወንጌልን በገንዘባችን እናገልግል
1000008060855 (MKC mission)

1/06/2018 ዓ.ም
📍 ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ

እሁድ ጥር 24/2018 ዓ.ም ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ የአምልኮ ፕሮግራም።በፀሎት እንዲሁም በማስተባበር ገሊላ ጉዲሳ አምልኮ ከቤተ ክርስትያናችን ይዲድያ የአምልኮ ህብረ...
03/02/2026

እሁድ ጥር 24/2018 ዓ.ም ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ የአምልኮ ፕሮግራም።

በፀሎት እንዲሁም በማስተባበር ገሊላ ጉዲሳ አምልኮ ከቤተ ክርስትያናችን ይዲድያ የአምልኮ ህብረት ጋር እግዚአብሔርን አምልከናል ቃለ እግዚአብሔር በመጋቢ አለማየሁ ተካፍለናል።

ርእስ፦ መስጠት

መስጠት በክርስቲያን ሕይወት ውስጥ አስፈላጊ ክፍል ነው።

▪️እግዚአብሔር ያለንን ለምን ሰጠን?
እግዚአብሔር ያለንን የሰጠን ምክንያት
- ለሌሎች እንድንካፈልና (1ኛጢሞ 6፥17-19, ኤፌ 4፥8, 2ቆሮ 8፥14)
- በመስጠት ደስታ እንድንሞላ ነው።

▪️እኛ ለምን እንሰጣለን?
እኛ የምንሰጥበት ምክንያት
- እግዚአብሔር ስለሚባርከን (ሉቃ 6፥38, 2ኛ ቆሮ 9፥ 6, 10, ምሳ 4፥14
ፊሊጲ 4፥19)፣
- እርሱን ደስ ስለሚያሰኝ (ፊሊ 4፥18, 2ኛ ቆሮ 9፥7)፣
- የሌሎችን ጉድለት ስለምንሞላ (2ኛ ቆሮ 9፥ 12)
- ስሙን ስለምንከብር ነው (2 ኛ ቆሮ 9፥12-13)።

▪️ እንዴት እንስጥ?
- በመስጠታችን ደስ እያለን (2ኛቆሮ 9፥7, 2ቆሮ 8፥4)፣
- ያለ ግብዝነት (ማቴ 6-4) እና
- ከራሳችን ጉድለት ቢሆንም በታማኝነት መሆን አለበት (2ኛቆሮ 8፥2, ማር 12፡ 44)።

✨ እውነተኛ መስጠት እግዚአብሔርን የሚያከብር እና በቤተ ክርስቲያንና በማህበረሰብ ውስጥ ፍቅርና አንድነት የሚያበዛ ነው።

24/05/2018 ዓ.ም
📍 ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ

🌟ፍቅር ተወለደ🌟“ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።”                 ***** ኢሳይያስ ...
03/01/2026

🌟ፍቅር ተወለደ🌟
“ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።”
***** ኢሳይያስ 7፥14 ******
የጌታችን እና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት ምክንያት በማድረግ ልዩ የሆነ የበዓል ፕሮግራም ተዘጋጅቷል ። በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ!
ታህሣሥ 27/2018 ዓ.ም
🕰 ከ10:00 ጀምሮ
📍ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ አዳማ

🌟 የአምልኮ ድግስ🌟“ጌታም ከክፉ ነገር ሁሉ ያድነኛል ለሰማያዊውም መንግሥት ይጠብቀኛል፤ ለእርሱ ከዘላለም እስከ ዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።”                  * 2ኛ ጢሞቴዎስ 4...
26/12/2025

🌟 የአምልኮ ድግስ🌟

“ጌታም ከክፉ ነገር ሁሉ ያድነኛል ለሰማያዊውም መንግሥት ይጠብቀኛል፤ ለእርሱ ከዘላለም እስከ ዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።”
* 2ኛ ጢሞቴዎስ 4፥18 *

✨ የፊታችን እሁድ 19/04/2018 ዓ.ም ከ11 ሠዓት ጀምሮ በወጣት ለክርስቶስ የተዘጋጀ የአምልኮ ፕሮግራም ይኖረናል በዚያም ከቤተክርስቲያናችን ይዲድያ የአምልኮ ህብረት ጋር እግዚአብሔርን እናመልካለን እንዲሁም ከወንድማችን ያቡ ጋር የእግዚአብሔርን ቃል እንካፈላለን።

✨ ሁላችንም በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ እንሁን።
ተባረኩ!

📍ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ

እሁድ ታህሣሥ 12/2018 ዓ.ም ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ የአምልኮ ፕሮግራምበዝማሬ ከ ፊሶን መኮንን ጋር እግዚአብሔርን አምልከናል እንዲሁም በኳየሮ አገልግሎት እጅግ ከ...
25/12/2025

እሁድ ታህሣሥ 12/2018 ዓ.ም ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ የአምልኮ ፕሮግራም

በዝማሬ ከ ፊሶን መኮንን ጋር እግዚአብሔርን አምልከናል እንዲሁም በኳየሮ አገልግሎት እጅግ ከተወደዱ ከናዝሬት ልደት መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ መዘምራን ጋር አምልከናል።

ርእስ፦ መለኮታዊ ጣልቃ ገብነት በአማኞች ህይወት ውስጥ።

መነሻ ጥቅስ:- ማር 5፡25፤34
ከአሥራ ሁለት ዓመቷ ጀምሮ ደም ሲፈሳት የነበረች ሴት መፍትሔም ፍለጋም በብዙ ስትባዝን ቆይታ የኢየሱስን ወሬ በመስማት "ልብሱን ብቻ የዳሰስሁ እንደ ሆነ እድናለሁ" በማለት አምና በእምነቷም ምክንያት እንደ ተፈወሰች እና ኢየሱስም "ልጄ ሆይ፥ እምነትሽ አድኖሻል ፤ በሰላም ሂጂ ከሥቃይሽም ተፈወሽ" በማለት በእምነቷ ምክንያት እግዚአብሔር በሕይወቷ እንዴት ጣልቃ እንደገባ እንመለከታለን።

ይህቺ ሴት የነበራት ጥያቄዎች
▪️በሕይወት የመኖር ጥያቄ
▪️የገንዘብ ጥያቄ
▪️የማህበራዊ ሕይወት ጥያቄ ነበረባት።

- በዚህች ሴት ሕይወት ውስጥ የነበረው ጥያቄ መፍትሔ የሚያገኘው በሰው ሣይሆን በእግዚአብሔር መለኮታዊ ጣልቃ ገብነት ብቻ ነበር።
▪️የኢየሱስን ወሬ ሰማች ለዚህች ሴት መፍትሔ ያመጣላት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነበረ።

ዘፍ 15 ላይ እግዚአብሔር ለአብርሃም በፈራበት ጉዳይ ላይ (ልጅ ስለሌለው ኤሊዔዘር ይወርሰኛል በማለት በፍርሀት ውስጥ ሳለ) የተናገረውን ስንመለከት “እነሆም፥ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል መጣለት፦ ይህ አይወርስህም፤ ነገር ግን ከጉልበትህ የሚወጣው ይወርስሃል።” ዘፍጥረት 15፥4 በማለት በሕይወቱ እንዴት ጣልቃ እንደገባም እናያለን።

አሁንም እግዚአብሔር በእኛ ሕይወት ጣልቃ ይገባል!

▪️“እግዚአብሔር አምላክ የሚናገረውን እሰማለሁ፤ ሰላምን ለሕዝቡና ለቅዱሳኑ ልባቸውንም ወደ እርሱ ለሚመልሱ ይናገራልና።” መዝሙር 85፥8

▪️የሰማችውን አምና ነበር።
- ትንሽ እምነት ትልቅ ችግርን ይፈታል!

▪️ያለችበት ሁኔት ወደ እርሱ የሚያስቀርብ እንኳ ባይሆን ነገር ግን እርሷ መቅረብን መረጠች ስለዚህ በምንም ሁኔታ ውስጥ ብንሆንም ወደ እርሱ እንቅረብ እግዚአብሔር በሕይወታችን ጣልቃ ይገባል።

ወንጌላዊት ምሥራቅ አደመ
12/04/2018 ዓ.ም
📍ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ

ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክእሁድ ታህሳስ 5/2018 ዓ.ምየአምልኮ ፕሮግራም ርዕስ:- የማንም ሰው ልብ አይውደቅ!“ዳዊትም ሳኦልን፦ ስለ እርሱ የማንም ልብ አይውደቅ፤ እኔ ...
15/12/2025

ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ
እሁድ ታህሳስ 5/2018 ዓ.ም
የአምልኮ ፕሮግራም

ርዕስ:- የማንም ሰው ልብ አይውደቅ!

“ዳዊትም ሳኦልን፦ ስለ እርሱ የማንም ልብ አይውደቅ፤ እኔ ባሪያህ ሄጄ ያንን ፍልስጥኤማዊ እወጋዋለሁ አለው።”
***1ኛ ሳሙኤል 17፥32

▪️ሳኦል የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ከተላለፈ በኃላ በእግዚአብሔር ዘንድ የተናቀ ሆነ። ስለዚህም የእሴይ ልጅ ዳዊት በእግዚአብሔር ተቀባ: ነገር ግን ከተቀባ በኃላ ሰልፍ ነበረ።
▪️ከቅባት በኃላ ሰልፍ አለ!

የጌት ሰው ፍልስጥኤማዊው ጎልያድ ለአርባ ቀናት እስራኤላውያን በጠዋት በጠዋት እየወጣ የሚገጥመኝ ካለ በማለት ያስጨንቃቸው ነበር።

▪️በጠዋት በጠዋት እየወጣ በማስጨነቅ ሙሉ ቀናቸውን ይገዛ ነበር

▪️ከግጥሚያው ቀድሞ ጎልያድ በሚያደርገው ነገር እስራኤላውያን የተሸነፈ ስነ-ልቦና ተላብሰው ነበረ። በእግዚአብሔር የተቀባው ዳዊትም ለወንድሞቹም ምግብ ለማድረስ በሚሄድበት ጊዜ (ድንገት በሚመስል ሁኔታ) ስላለው ሁኔታ በመረዳት ሳይገጥመው እንደሚያሸንፈው ተረድቶ ነበር ምክንያቱም ውጊያው በእስራኤል አምላክ እንዳለ ይታወቅ ዘንድ ነው።

▪️ሳኦልም ዳዊትን ከጎልያድ አንፃር እያነፃፀረ ያወራ ነበር። ለዳዊት የራሱን የጦር ልብስ ሰጠው ነገር ግን ዳዊት እግዚአብሔር እራሱ ባለማመደው መንገድ እንደሚወጣ ነገረው።
▪️ክብሩን እግዚአብሔር ብቻውን እንዲወስድ (እንዲህ ወይም እንዲያ ስለሆነ ነው እንዳይባል)
▪️ዳዊት በእጁ የያዛት ወንጭፍ እንኳን መጠቀሚያ ናት እንጂ ወደ ጎልያድ የወጣው በጭፍሮች አምላክ በእግዚአብሔር ስም እመጣብሃለሁ በማለት ነበር።

ዋናው ይመታል ጭፍሮቹ ይበተናሉ!

ለምንድነው ልባችን የማይወድቀው?!

1. እግዚአብሔር ከጠላቶቻችን እጅ ስለሚያድነን።
“ዳዊትም፦ ከአንበሳና ከድብ እጅ ያስጣለኝ እግዚአብሔር ከዚህ ፍልስጥኤማዊ እጅ ያስጥለኛል አለ። ሳኦልም ዳዊትን፦ ሂድ፥ እግዚአብሔርም ከአንተ ጋር ይሆናል አለው።”
1ኛ ሳሙኤል 17፥37

2. ጠላቶቻችንን እግዚአብሔር አሳልፎ ስለሚሰጠን።
“እግዚአብሔር ዛሬ አንተን በእጄ አሳልፎ ይሰጣል፤ እመታህማለሁ፥ ራስህንም ከአንተ አነሣዋለሁ፤ የፍልስጥኤማውያንንም ሠራዊት ሬሶች ለሰማይ ወፎችና ለምድር አራዊት ዛሬ እሰጣለሁ። ይኸውም ምድር ሁሉ በእስራኤል ዘንድ አምላክ እንዳለ ታውቅ ዘንድ፤”
1ኛ ሳሙኤል 17፥46

3. ለሞት የሚፈልገን እራሱ ስለሚሞት።
“ዳዊትም ሮጦ በፍልስጥኤማዊው ላይ ቆመ፤ ሰይፉንም ይዞ ከሰገባው መዘዘው፥ ገደለውም፥ ራሱንም ቈረጠው። ፍልስጥኤማውያንም ዋናቸው እንደ ሞተ ባዩ ጊዜ ሸሹ።”
1ኛ ሳሙኤል 17፥51

4. ሀዘንን ወደ ደስታ ስለሚቀይር።
“የእስራኤልና የይሁዳ ሰዎች ተነሥተው እልል አሉ፥ ፍልስጥኤማውያንንም እስከ ጌትና እስከ አስቀሎና በርድረስ አሳደዱአቸው። ፍልስጥኤማውያንም ከሸዓራይም ጀምሮ እስከ ጌትና እስከ አቃሮን ድረስ በመንገድ ላይ የተመቱት ወደቁ።”
1ኛ ሳሙኤል 17፥52

አፅናኑ ህዝቤን አፅናኙ!

እግዚአብሔር ከጠላቶቻችን እጅ ስለሚያድነን፥ጠላቶቻችንን እግዚአብሔር አሳልፎ ስለሚሰጠን፥ለሞት የሚፈልገን እራሱ ስለሚሞት፥ሀዘንን ወደ ደስታ ስለሚቀይር ልባችን በፍጹም እንዳይወድቅ።

መጋቢ ጌታሁን ሹሚ
5/04/2018
📍ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ አዳማ

“ዳሩ ግን እኔ ከአብ ዘንድ የምልክላችሁ አጽናኝ እርሱም ከአብ የሚወጣ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ፥ እርሱ ስለ እኔ ይመሰክራል፤”             ****ዮሐንስ 15፥26****
27/11/2025

“ዳሩ ግን እኔ ከአብ ዘንድ የምልክላችሁ አጽናኝ እርሱም ከአብ የሚወጣ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ፥ እርሱ ስለ እኔ ይመሰክራል፤”
****ዮሐንስ 15፥26****

"አንተ መልካም ነህ፤ የምታደርገው መልካም ነው፤..."                 ***መዝ 119:68***ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክየአምልኮ እና የፈውስ ፕሮግራም ለተከታታ...
15/10/2025

"አንተ መልካም ነህ፤ የምታደርገው መልካም ነው፤..."
***መዝ 119:68***
ምሥራቅ የአምላክ ክብር መሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ
የአምልኮ እና የፈውስ ፕሮግራም
ለተከታታይ አርብ ከ ጥቅምት 7 ጀምሮ
11:00 🕰L.T
📍ሚጊራ መነሀሪያ ሳይደርሱ

Address

Adama
0000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Misrak Ye Amlak Kibir MKC Adama/Nazareth posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category