ሎጎስ ዲጂታል መጽሔት Logos Digital Magazine

 #ሎጎስ  ቅጽ ፬ " "የሴትነት ነገረ መለኮትበሔዋን በኩል -ያዘነች፣ የተሰበረች፣ ምስኪን ምስል ሆናበኤልዛቤል በኩል- አመጸኛ፣ ዘማ፣ አመንዝራ ምስል ይዞ - በሥጋዋ የምትመካ፣ በሥጋዋ ኃይ...
16/12/2025

#ሎጎስ

ቅጽ ፬ " "

የሴትነት ነገረ መለኮት
በሔዋን በኩል -ያዘነች፣ የተሰበረች፣ ምስኪን ምስል ሆና
በኤልዛቤል በኩል- አመጸኛ፣ ዘማ፣ አመንዝራ ምስል ይዞ - በሥጋዋ የምትመካ፣ በሥጋዋ ኃይል ዙፋን እዘረጋለሁ ብላ የምታሰላ
በማርያም በኩል - በትሕትና፣ በንጽሕና፣ በእናትነት አዳኝ፣ ታዳጊ ሲሆን
እናያለን።
ጦር ሜዳ የሆነው አጀንዳ፣ አወዛጋቢው ጉዳይ፣ ሙግቱ በሚዛን ይቀርብበታል።
ውበት በረከት መሆን ሲችል ለምን ቀውስ ይጋብዛል? ለምን ጉዳት ይፈጠራል?
ሴትነት ጥበብ፣ ሕይወት፣ ምስጢራዊ ኃይል የሚሆነው እንዴት ነው?

"ሴትነት በክርስትና"

ሎጎስ ቅጽ 04

እስከዚያው ለሌሎች ሊንኩን እናጋራ። እነሆ ሊንክ
https://t.me/sabasagal

 መጽሔታችን  #ሎጎስ ሦስተኛ ቅጽ መጥታለች። ከታች ባለው ማስፈንጠሪያ ገብተው ያገኟታል።  #ይወዳጁን  ።https://t.me/sabasagal
01/11/2025



መጽሔታችን #ሎጎስ ሦስተኛ ቅጽ መጥታለች። ከታች ባለው ማስፈንጠሪያ ገብተው ያገኟታል።
#ይወዳጁን ።
https://t.me/sabasagal

ጰንጠቈስቴበዓለ ርደተ መንፈስ ቅዱስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በታላቅ ፍቅር ከሚከበሩት ፱ጠኙ የጌታ በዓላት መካከል አንዱ ነው።ቤተክርስቲያን አምላካችን ለሐዋርያት በገባው ኪዳን መ...
07/06/2025

ጰንጠቈስቴ

በዓለ ርደተ መንፈስ ቅዱስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በታላቅ ፍቅር ከሚከበሩት ፱ጠኙ የጌታ በዓላት መካከል አንዱ ነው።

ቤተክርስቲያን አምላካችን ለሐዋርያት በገባው ኪዳን መሠረት መንፈስቅዲስ የወረደበትን ዕለት በዓለ ጰራቅሊጦስ ብላ ታስባለች።

ይህም በዓል በሦስት ስያሜ የሚጠራ ሲሆን ከሦስቱ ስያሜዎች ሁለቱ በቋንቋ ቢለያዩም በትርጉም ግን አንድ ናቸው ።በዓለ ሃምሳ የግዕዝ ቋንቋ ሲሆን ጰንጠቆስጤ የግሪክ ቋንቋ ነው።

እነዚህንም ስንተረጉማቸው የ፶ኛው ቀን በዓል የሚል ትርጉም የሚሰጡ ሲሆኑ ምስጢሩም ጌታ ከሙታን ተለይቶ በተነሣ በ፶ኛው ቀን መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት መውረዱን የሚያሳይ ነው።

ሌላኛው ስያሜው በዓለ ጰራቅሊጦስ የሚባል ሲሆን ትርጉሙም ከሦስቱ አካል አንዱ አካል መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት መውረዱን የሚያሳይ ነው።

በወንጌል ጌታ ለሐዋርያት እፌኑ ለክሙ ጰራቅሊጦስ ካልዐ - ከእኔ በስም በግብር በአካል ልዩ የሆነ መንፈስቅዱስን ወደ እናንተ እልካለሁ። እርሱም ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል።

ብሎ እንደ ተናገረ ደግሞም መንፈስቅዱስ ካልመጣ ጽናት እንደ ሌላቸው እና እርሱን መጠበቅ እንዳለባቸው ነግሮአቸው ካረገ በኋላ እነርሱም በቢታንያ - አንተ አቡነ ወአንተ እምነ - አባታችን አንተ ነህ አናታችንም አንተ ነህ ብለው የተከተሉት ጌታን ወደ ሰማይ ሲያርግ አይተው ከተመለሱ በኋላ

በተሰጣቸው ኪዳን መሠረት በኢየሩሳሌም አጽናኝ የሆነውን መንፈስቅዱስን ለመቀበል ለ፲ቀን ያህል ጠብቀዋል። በዚህም ወቅት ሐዋርያት የአጽናኙን መምጣት ይጠባበቁ እና ተስፋ የደርጉ ነበር ።

ከዚህ በኋላ ግን በ፲ኛው ቀን ሁሉም በአንድ ልብ ሁነው ሳለ መንፈስቅዱስ እንደ ሚነጥቅ አውሎ ነፋስ ወደ እነርሱ ወረደ እንደ እሳት የተከፋፈሉ ልሳናትም ታዩአቸው።

በተሰጣቸውም ጸጋ በሀገሩ ሁሉ ቋንቋ ተናገሩ ደካሞች የነበሩት በረቱ ጸኑ ያንጊዜ በክርስቶስ ደም የተመሠረተችን ቤተክርስቲያንን ለዓለም ለመስበክ ታላቁን ተልዕኮ ለመፈጸም ተነሱ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው የክርስቶስን ወንጌል ሰበኩ። ይህ ሁሉ የሆነው መንፈስ ቅዱስ ከመውረዱ የተነሣ ነበር።

መንፈስ ቅዱስ ለምን ወረደ

ሐዋርያትን ለማጽናት

ደጋግመን እንደ ተማርነው ምንም ስንኳ ሐዋርያት ከጌታ ለዓመታት የክርስቶስን ልደቱን ሞቱን ትንሣኤውንንና ዕርገቱ እየ ተማሩ የቆዩ ቢሆንም ምስጢሩን የመረዳት ነገር ግን በእጅጉ ይከብዳቸው ነበር።

ከዚህም የተነሣ ጌታ አሁን የምነግራችሁን ዛሬ መረዳት አትችሉም። መንፈስቅዱስ ወደ እናንተ በመጣ ጊዜ ግን አሁን የነገርኳችሁን ሁሉ ያስረዳችኋል።

ከእኔ የሰማችሁትን ሁሉ ያስታውሳችኋል።እያለ በጊዜው ያልተ ረዱትን ኋላ መንፈስቅዱስ በወረደላቸው ጊዜ እንደሚረዱት ደጋግሞ ነግሯቸው ነበር።

ሐዋርያትም ምንም እንኳን የክርስቶስ መያዙም ስቅለቱም ሞቱም ትንሣኤውም በነገራቸው መሠረት የተከናወነ ቢሆንም እነርሱን ግን የሆነው ሁሉ ያስደነግጣቸው ነበር።

ከክርስቶስ ትንሣኤ በኋላ እንኳ ማመን አቅቷቸው በፍርኀት ተጨንቀው ነበር።ክርስቶስ ደጋግሞ ቢገለጥላቸውም አእምሮ አቸው ግን ከእርጅና መታደስ አቅቶት ይታወክ ነበር።

ስለዚህ ለቤተክርስቲያን ቀጣይ ሕይወት የሐዋርያት ጽኑዐ አእምሮ መሆን የግድ አስፈላጊ ስለሆነ መንፈስ ቅዱስ ሐዋርያትን ለማጽናት ከብልየታቸው ለማደስ ወርዷል።

መንፈስ ቅዱስም በወረደ ጊዜ ያ ሁሉ ፍርኀት ተወግዶ ፈርተው በራቸውን ዘግተው ይኖሩ የነበሩት ሐዋርያት ወደ አደባባይ ወጥተው ለጌታቸው ምስክር ለመሆን በቅተዋል።

በመንፈስ ቅዱስ ከመታደሱ አስቀድሞ በፍርኀት ምክንያት ጌታን አላውቀውም ብሎ የነበረው ደግሞም ሐዋርያትን በትኖ ጠፍቶ የነበረው ሐዋርያው ጴጥሮስ መንፈስ ቅዲስን በተቀበለ ጊዜ ማንንም ሣይፈራ ለአምላኩ ምስክር ሁኗል።

ይህም መንፈስቅዱስ ያላደረበት ሰውነት ምንም ይሁን ምን መንፈሳዊ ድፍረት ሊኖረው እንደ ማይችል ያስረዳናል።

ጌታ መንፈስ ቅዱስ ወደ እናንተ በመጣ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ በኢየሩሳሌምም እስከ ምድር ዳርቻ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ ያለው የጌታ ቃል ተፈጽሟል።የ ሐ ሥ 1:18

ሐዋርያት ያንን ከሚያህል ታላቅ ፍርኀት ወጥተው ስለ ክርስቶስ ለመመስከር የበቁት ሕይወታቸው ፍርኀትን ሁሉ አርቆ በድፍረት ለአመኑት አምላክ ለመመስክር መዘጋጀታቸው ሰብአዊ ለውጥ አልነበረም።

በዚህ ቁመና እንዲገኙ ያደረጋቸው በተነገረው መሠረትልቡናን የሚያጸነ ብልየትን የሚያድስ ከፍርኀት አውጥቶ ወደ ጥብአት ከብልት ለይቶ ወደ ተሐድሶ የሚያሸጋግሩ የአብ የወልድ ሕይወት ተብሎ የሚጠራ መንፈስ ቅዱስ በእነርሱ ስላደረ ነበር።

የተወደዳችሁ አንባብያን ዛሬም የትኛውንም መንፈሳዊ ሥራ ለመሥራት እንደ ማነቆ የያዘን ነገር ብዙ ነው።

ከዚህ ወጥተን እውነተኛ አገልግሎትን ለማገልገል ያለ ፍርኀት ስለ ክርስቶስ በእውነት ለመመስከር መንፈስ ቅዱስ ሊያድርብን ይገባል።

ደግሞ መንፈስቅዲስ በእኛ እንዲያድር ልቡናችንን ታቦት አድርገን አንድነትን ጠብቀን ተዘጋጅተን ልንጠብቅ ይገባናል።
ወመንፈሰከ ቅዱሰ ኢታውጽዕ እምላዕሌየ

ለክርስቶስ ምስክር ለመሆን

ከላይ እንደ ተመለከትነው አምላካቸችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለራሱ ብዙ ቢመሰክርም ፍጹም አምላክነቱን መረዳት ለተሣናቸው ሐዋርያት ስለ እርሱ የሚመሰክር ሌላ ምስክር እንደ ሚመጣ ያም ምስክር የክርስቶስን እውነተኛ የባሕርይ አምላክ መሆን ሞቱን ትንሣኤውን እና ዳግም ምጽአቱን ለዓለም ሁሉ የሚሰብክ እና የሰውን ልብ በክርስቶስ ፍቅር እንደሚያነሣሣ አስቀድሞ ለሐዋርያት አስተምሮአቸው ነበር።

በዮሐንስ ወንጌል 15:26 ተጽፎ እንደምናነበው
እኔ ከአብ ዘንድ የምልክላችሁ ጰራቅሊጦስ በመጣ ጊዙ እርሱ የእውነት መንፈስ ስለእኔ ይመሰክራል።

ይህም ከአብ ወጥቶ ሕይወተ አብ ሕይወተ ወልድ የተባለ የሆነ መንፈስ ቅዱስ ስለ ክርስቶስ ትምህርት እና ሕይወት በሚገባ እንደ ሚመሰክር ያስረዳበት የወንጌል ክፍል ነው።

በዚህ በዓል የተረጋገጠው ክርስቶስ ከማረጉ አስቀድሞ ለደቀ መዛሙርቱ የመሰከረው እውነት ነው።

ሐዋርያት መንፈስ ቅዲስን ከተቀበሉ በኋላ ጌታ ከማረጉ በፊት የነገራቸውን ሁሉ በአደባባይ የሚመሰክሩ ሁነዋል።

ቅዱስ ጴጥሮስ ይህ የምታዩት ክስተት ስካር አይደለም እናንተ የሰቀላችሁት ኋላም ሞትን ድል አድርጎ የተነሣው ክርስቶስ በነቢያት ያናገረው እርሱ ሰው ሁኖ የመሰከረው እውነት መሆኑ ይታወቅ ዘንድ ዘንድ በመንፈስቅዱስ የተከናወነ ድንቅ ክንውን ነው ብሎ መሥክሯል።

መንፈስ ቅዱስ ከወረደ በኋላ የክርስቶስ እውነተኛ ትምህርቱ መንፈስ ቅዱስ ከወረደበት ጀምሮ ለዓለም ተገልጧል።

ይህም ኢየሱስ ክርስቶስ በአግባቡ ለመረዳት የመንፈስ ቅዱስ እግዛ እንደሚያስፈልግ ያስረዳናል።

የቤተክርስቲያን እወነት ለመግለጥ

የቤተክርስቲያን ሊቃውንት ደጋግመው እንደ ነገሩን የመንፈስ ቅዱስ መውረድ የቤተክርስቲያን ልደት ይባላል።

ይኸውም ቤተክርስቲያን መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ላይ ከወረደ ጀምሮ የክርስቶስ ሕያው አካል መሆኗን በመንፈስ ቅዱስ እየተመራች እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ከመንፈስ ቅዲስ ሳትለይ እያደገች እየሰፋች የምትሄድ እና ሕያውነቷ የሚረጋገጠው በመንፈስ ቅዱስ ስለሆነ ነው።

በዚህም በዓል አንዲት ቤተክርስቲያን ዓለምን ሁሉ በክርስቶስ አንድ የምታደርግበትን ኃይል የተቀበለችበት በዓል ነው

ይህም ይታወቅ ዘንድ በኃጢአት ምክንያት ተበትኖ የነበረውን የሰው ቋንቋ በሐዋርያት ዘንድ መነገሩ እና የሰውን ሁሉ የነገዱን ሁሉ ቋንቋ መስማታቸው።መንፈስ ቅዱስ አንዲቱን የክርስቶስ ቤተክርስቲያን መሠረት አድርጎ ዓለምን ሊሰበስብ የቤተክርስቲያንን አድነት ሊመሠክር እንደ ወረደ ያሳያል።

የመንፈስ ቅዱስም ተግባሩ ቤተክርስቲያን ከዓለም ሁሉ ተለይታ የክርስቶስን እውነት እንድትገልጥ መምራት እና ማገዝ ነው።

👇
# #ቤተክርስቲያን አትለወጥም ማለት የተቻለው የሚመራት መንፈስ ቅዱስ የማይለወጥ ስለሆነ ነው። # #

► ስለዚህ በዘመነ ሐዋርያት የነበረችው ቤተክርስቲያንና ዛሬ ባለችው ቤተክርስቲያን መካከል የአስተምህሮ ለውጥ የለም።

ለምን .? ► ክርስቶስ የተናገረው ቃል። መንፈስቅዱስ ከሚመሰክረው የተለየ ስላልሆነ። ደግሞም የማይለያት መንፈስ ቅዱስ ትላት የተናገረውን ዛሬ የሚለውጥ ስላልሆነ ነው።

ስለዚህ ዛሬ ምንም እንኳ ቤተክርስቲያን ነኝ የሚለው ቢበዛ መታወቂያዋ ግን ከመንፈስ ቅዱስ ጋር መሆኗ ነው።

መንፈስቅዱስ ከእርሷ ጋር መኖሩ የሚታወቀው ከክርስቶስ የተለየ ትምህርት ባለ ማስተማሯ ነው።

ክርስቶስ ያመነ የተጠመቀ ይድናል ብሎ ነበር ለሐዋርያት የወረደው መንፈስ ቅዱስ ይህንን የክርስቶስን ቃል ሐዋርያት ከተረዱት በላይ እንዲረዱት በማድረግ ሐዋርያት እንዲ ተገብሩት አደረገ እንጅ አዲስ ትምህርት አላመጣም። የሐዋ.ሥራ.2፥38

ጌታ ለድኅነት ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን መቀበል የግድ እንደ ሆነ ዮሐ 6-58 ላይ በማይለወጥ ቃሉ ተናግሮ ነበር መንፈስ ቅዱስ ያደረባቸው ሐዋርያትም ይህንን ሳይለውጡ ከቅዱስ ሥጋው ከክቡር ደሙ በፍርኀት እና ሰውነትን ንጹሕ በማድረግ መቀበል እንደሚገባ ለተከታዮቻቸው ያስተምሩ ነበር።

ዛሬ መንፈስ ቅዱስ እውነትነቷን የመሰከረላት ቤተ ክርስቲያን የትኛዋ ናት? ተብሎ ቢጠየቅ መልሱ ክርስቶስ ከመሠረታት ጀምሮ ሳትለወጥ እዚህ የደረሰች ክርስቶስ ሰው ይድንበታል ብሎ ያስተማረውን የድኅነት ትምህርት ሃይማኖትን እምነትን ምግባርን እና ምስጢራትን መፈጸምን የምታስተምር እራሷ ክርስቶስ ራስ ሆኖላት መንፈስ ቅዱስ የሚመራት እንደ ጊዜው የማትለዋወጥ አንዲት ቤተክርስቲያን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብቻ መሆኗን እንረዳለን

ለዚህም ቀድሞ ክርስቶስ የተናገረው መንፈስቅዱስም በወረደ ጊዜ ያጸናውን ሐዋርያት ኋላ የመሠከሩትን የድኅነት መንገድ ይዛ በመገኘቷ ነው ማር.16፥16 1ቆሮ.11፥1 ዮሐ.6፥50

ማጠቃለያ

ይህ በዓል ለዓለሙ ሁሉ እውነትን ይመሰክር ዘንድ መንፈስ ቅዱስ የወረደበት የክርስቶስ እውነተኛ የባሕርይ አምላክ መሆነ በሐዋርያት የተመሠከረበት ድንቅ በዓል ነው።

በተለይም ኦርቶዶክሳውያን ይህንን በዓል ስናከብር ያ ለሐዋርያት በእሳት አምሳል የተገለጠው መንፈስ ቅዱስ ዛሬም ከእኛ ያልተለየ እና ቤተክርስቲያን በብርሃኑ የምትመራበት በመሆኑ ይህንን በዓል ስናከብር ደስታችን ወደር የለውም።

ስለዚህ በክርስቶስ ተመስርታ በርደተ መንፈስ ቅዱስ የተገለጠች አሐቲ ቤተክርስቲያናችን ከመንፈስ ቅዱስ ያገኘችውን ሁሉ ይዛ እንድትቀጥል ሁላችንም የምንችለውን ሁሉ በማድረግ በእኛ ዘመን የተገኘችውን ቤተክርስቲያን በማገዝ ይህንን በዓል ልናስብ ይገባናል።

30/09/2017 ዓ.ም
ደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም ጉባኤ ቤት
© የንታ ነቢየ ልዑል አዳሙ

29/05/2025

🔴አዲስ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም መዝሙር

አስተያየታችሁን በቻናላችን አስተያየት መስጫ ቦታ እንዲሁም በዚህ በፌስቡክ ፔጃችን ያኑሩልን።

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምልጃና ጸሎት አይለየን🤲🤲🤲

እስከ መጨረሻ ይስሙት። ሙሉ ቪዲዮውን ለማግኘት ከሥር የሚገኘውን ማስፈንጠሪ ይጠቀሙ🙏🙏
[http://www.youtube.com/]

🌹 New Spiritual Song Dedicated to St. Mary (Kidist Mariam) 🌹

We just uploaded a beautiful Ethiopian Orthodox Tewahedo Church song that honors the holiness and purity of St. Mary.

May this song bring peace to your heart and strengthen your faith. 🙏

🔗 Watch the full video on YouTube → [http://www.youtube.com/]

💬 Please share with others and let me know how this touched your heart in the comments.

@

23/02/2025

እንኳን ለጾመ ክርስቶስ በሰላም አደረሰን+++
ዘወረደ /ዘመነ አዳም/
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት ዘወረደ ይባላል፡፡ ዘወረደ ማለት፣ ከላይ የመጣ፣ የወረደ ማለት ነው፡፡ ይህም የአምላካችን ሰው መሆን ያመለክታል፡፡ ከሰማይ ከወረደው በቀር ወደሰማይ የወጣ የለም ካለው ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ቃል በመነሳት ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በዚህ ዕለት ምስባክ “ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ በቃሉ” በማለት በጾመ ድጓው መጀመሪያ ላይ ገልጾት ይገኛል፡፡
አዳምን ለማዳን ከሰማይ የወረደውን አይሁድ ሰቀሉት፣ የሰማይን ሥልጣን ያለው የሁሉ ጌታ እንደሆነም ምንም አላወቁም ብሎ ተናግሮ ነበር፡፡ ይህም ድርሰት በቤተ ክርስቲያናችን የጾም መጀመሪያ የሆነው ዕለተ ሰንበት ዋዜማ፣ መግቢያ፣ /መሐትው/ ሆኖ ከዋዜማ በፊት ምንጊዜም በየዓመቱ ይቆማል፡፡ ይዘመራል፡፡ ይመሰገናል ማለት ነው፡፡
ስለዚህ የሳምንቱ ስያሜ ከዚህ የተወሰደ ነው፡፡ እንዲሁም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራውን የጀመረው፤ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ሰው በመሆን ፣ በዮርዳኖስ ተጠምቆ በማስተማር እንደሆነ ሁሉ የመጀሪያው ሳምንት ዘወረደ ይባላል፡፡
በዚህ ሳምንት በተለይም እሑድና ሰኞ የሚነገሩት ውዳሴያት ከመጻሕፍተ ኦሪትና ነቢያት የተወሰዱ ናቸው፡፡ ሁለተኛም ሙሴኒ በመባል ይታወቃል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ አዳምን ለማዳን ከሰማይ መውረዱንና በመስቀል መሰቀሉን ስለሚያወሳ ነው፡፡
የቤተ ክርስቲያናችን ታሉቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ፣ በዘወረደ ጾመ ድጓው ሰንበት ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን፣ ሕይወት ላለው ነገር ሁሉ ጸጥታና ሰላም የሰፈነባት የዕረፍት ቀን ስለመሆኗ “አዘዞ እግዚአብሔር ለሙሴ ወይቤሎ ሰብዕከ ወላህምከ ወኲሉ ቤትከ ያዕርፍ በሰንበት” ዘፀ.20፥10፣23፣12፣ ጾመ ድጓ፣ እግዚአብሔር ሙሴን ሕዝብህ የከብትህ መንጋህ ቤተሰብህ ሀሉ በሰንበት ቀን ከድካማቸው ይረፉ በማለት አዘዘው ይላል፡፡ በዚህም ዘመነ ጾም፣ ወይም ጾመ ሙሴ ይባላል፡፡
በጾመ ድጓው ዘወረደ እየተባለ የሚታወቀው፣ በጾመ አርባው ወቅት በተለይም በመጀመሪያው ሳምንት የሚገኘው ያሬዳዊ ድርሰት በነግህ በሠለስት፣ በቀትርና በሠርክ እንዲሁም ቅዳሜና እሑድ በሌሊት የሚዘመር ነው፡፡ በውስጡም የያዘው ፍሬ አሳብ፣ የጾምን፣ የጸሎትን፣ የምጽዋትንና የፍቅርን ጠቃሚነት አጉልቶ የሚያስተምር ነው፡፡
በዚህ በጾም ወቅት በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት በአብዛኛው ከቅዱስ ያሬድ ድርሰቶች ውስጥ የሚዘመረው ምዕራፍ የተባለው ነው፡፡ ምዕራፍ የተባለበት ምክንያትም በየመዝሙራቱ መሀል ሃሌታና ድጓ እያስገባ ለመዝሙሩ ማረፊያ ስላበጀለት በዚህ ምክንያት ምዕራፍ የሚል ስያሜ ሊያገኝ ችሏል፡፡ ይህ የዜማ መጽሐፍ በሁለት ታላላቅ ክፍሎች ይከፈላል፡፡ ይኸውም የዘወትር ምዕራፍና የጾም ምዕራፍ በመባል ይታወቃል፡፡የዘውትር ምዕራፍ የሚባለው በዓመቱ ውስጥ ባሉት ቀናት ውስጥ ሳምንታትና በዓላት ሁልጊዜ በአገልግሎት ላይ የሚውል ሲሆን፣ የጾም ምዕራፍ የሚባለው ደግሞ በጾመ አርባ ብቻ ለአገልግሎት የሚውል ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በዐሥሩ ምህላት አርዕስተ ምህላ በዚሁ ክፍል ይካተታል፡፡ የምዕራፍ ቅንብር ከመዝሙረ ዳዊት፣ ከድጓና ከጾመ ድጓ ጋር የተቀናጀ ነው፡፡ የትምህርት አሰጣጡም እንደ ድጓው ወይም እንደ ዝማሬ መዋሥዕቱ መጽሐፍ ተዘርግቶ ሳይሆን በቃል የሚጠናና የሚወሰን ነው፡፡ ስለሆነም ምዕራፍን ለመማር 150 መዝሙረ ዳዊትን፣ ከነቢያት 15 ምዕራፎችንና 5 መኃልያተ ሰሎሞንን በቃል ሸምድዶ መያዝ ይጠበቅበታል፡፡ ወይም ግድ ነው፡፡
ጾምን መጾም የፈቃድ ብቻ ሳይሆን የትእዛዝም ነው፡፡ በዘመነ ብሉይ ነቢዩ ኢዩኤል “ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ” ጾምን ያዙ አጽኑ ምሕላንም ዐውጁ ሸማግሌዎቹን ከፈጣሪያችን ቤት ሰብስባችሁ በአንድነት ሁናችሁ ወደ እግዚአብሔር ጩሁ /ለምኑ/ ብሏል፡፡ ኢዮ.ምዕ.1፥11፣ 2፣12፣15-16 ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ወኲኑ ላዕካነ፣ ለእግዚአብሔር በጾም ወበንጽሕ፡፡ በጾም፣ በንጽሐና ተወስናችሁ እግዚአብሔርን አገልግሉ ብሏል 2ቆሮ.6፥4-6፡፡
ጾም ከሌለ ወይም ተገቢ ካልሆነ ጌታችን በምትጾሙበት ጊዜ እንደ ግብዞች አትሁኑ ስለ ጽድቅ የሚራቡ የሚጠሙ ንዑዳን ክብራን ናቸው ለምን አለ? ማቴ.5፥፣6፣16፡፡ ነቢዩ ዳዊትም ሰውነቴን በጾም አሳመምኳት በቀጠና፣ በሰልት አደከምኳት ለምን አለ መዝ.34፥68፣ ት.ዳን. 9፥3-4፣ 14፥5
ነብዩ ሚኪያስ ሐዋርያት ሙሸራውን ከነሱ ለይተው የሚወስዱበት ጊዜ ይመጣል ያን ጊዜ ይጾማሉ ያለውን የጌታን ቃል መሠረት በማድረግ ክርስቶስ በሞት ከተለያቸው በኋላ ጾመዋል፡፡ ጾምንም ሠርተዋል የሐዋ.ሥራ 13፥3፡፡ ሠለስቱ ምዕትም ሐዋርያት የጾሙትንና እንዲጾም የወሰኑትን መጾም ይገባል ብለው ቤተ ክርስቲያን የተቀበለቻቸውን አጽዋማት እንዲጾሙ መወሰናቸው ይህን የጌታ ቃል መሠረት በማድረግ ስለሆነ፣ የትእዛዝ መሆኑን ተገንዝበን መጾም አለብን፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሠራዔ ሕግ እንደመሆኑ አርባ ቀን አርቦ ሌሊት ጾመ እንጂ እርሱ ሳይጾም ጾሙ አላለንም ማቴ.4፥2፡፡
ሠናይ መዋዕለ ጾም፡፡

ወልድ ይመጣል ከአእላፍ መላእክት ጋራዲ/ን ታዴዎስ ግርማ ቁ.3 መዝሙር
06/09/2024

ወልድ ይመጣል ከአእላፍ መላእክት ጋራ

ዲ/ን ታዴዎስ ግርማ ቁ.3 መዝሙር

ወልድ ይመጣል ከአእላፍ መላእክት ጋራዲ/ን ታዴዎስ ግርማ ቁ.3 መዝሙርD/n. Tadewos Girma Wold Yimetal አመ ይመጽእ ወልድኪምስለ አእላፍ መላእክቲሁትርዕድ ምድር እምግርማሁ ሰኣሊ ለነ ማርያም በቅድሜ....

ጻድቃን ሰማዕታት በሙሉበዓምደ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት ጻድቃን ሰማዕታት በሙሉበአካለ ስጋና በአካለ ነፍስበአካለ ነፍስ ያሉከፈጣሪ አማልደው እኛን ያስምራሉየእግዚአብሔር ዓይኖቹ ጻድቃንን ከማየትጆሮ...
30/08/2024

ጻድቃን ሰማዕታት በሙሉ
በዓምደ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት

ጻድቃን ሰማዕታት በሙሉ
በአካለ ስጋና በአካለ ነፍስ
በአካለ ነፍስ ያሉ
ከፈጣሪ አማልደው እኛን ያስምራሉ

የእግዚአብሔር ዓይኖቹ ጻድቃንን ከማየት
ጆሮቹም አይርቁም እነሱን ከመስማት
የጻድቅ ሰው ጸሎት ኃይልን ታደረጋለች
በምልጃቸው እንመን አናመታ በአንዳች

ኃጥኡ ነዌ እንኩአን በሰዖል እያለ
ስለ ወንድሞቹ ምሕረት ከለመነ
እናተማ ጻድቃን በገነት ያላችሁ
ምንኛ ትረዱን አምነን ስንጠራችሁ

ጊዜያዊ መከራ ሳያሰቃያቸው
እሳት እና ስለት ሳያስፈራራቸው
ሰማያዊይ ተስፋ ስለሚታያቸው
በመከራው ሁሉ ጸኑ በእምነታቸው

ቀዝቃዛ ውኃ እንኳን በጻድቅ ሰው ስም
የሚያጠጣ በኖር ዋጋው አይጠፋም
ብሎ እንዳስተማር ጌታ በወንጌል
አምነን እንፈፅመው ዋጋ ያሰጣል

ጻድቃን ሰማዕታት በሙሉበዓምደ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት ጻድቃን ሰማዕታት በሙሉበአካለ ስጋና በአካለ ነፍስበአካለ ነፍስ ያሉከፈጣሪ አማልደው እኛን ያስምራሉየእግዚአብሔር ዓይኖቹ ጻድቃን.....

ኦ ማርያም እለምንሻለሁ ባርያሽእስቲ አንድ ጊዜ ስሚኝቀርበሽ ካጠገቤ ሆነሽብርቱ ጉዳይ አለኝ ላንቺ ምነግሽኦ ቸሪት ተመላለሺ ለሊት በሕልሜ ልገሪኝ ቀርበሽአደራሽን እጄን በእጅሽ ያዢው እንዳልባ...
08/08/2024

ኦ ማርያም እለምንሻለሁ ባርያሽ
እስቲ አንድ ጊዜ ስሚኝ
ቀርበሽ ካጠገቤ ሆነሽ
ብርቱ ጉዳይ አለኝ ላንቺ ምነግሽ
ኦ ቸሪት
ተመላለሺ ለሊት በሕልሜ ልገሪኝ ቀርበሽ
አደራሽን እጄን በእጅሽ ያዢው እንዳልባንን
ሰላም ሰጊድ
ከሁሉ ሁሉ ጤፍ ታንሳለች
ከጭቃ ወድቃ ትነሣለች
ከዚያች ጤፍ የአዳም ልጅ ሁሉ አትስነፍ
የአዳም ልጅ ሁሉ ሰነፈና
የኑሮ ቤቱን ረሳና
ተው አትርሳ ተሰርቶልሃል የእሳት አልጋ
ያን የእሳት አልጋ የእሳት ባሕር
እንደምን ብዬው ልሻገር
ተሻገሩት አሉ የሰሩት ምግባር
እኔ ባርያሽ ወዴት ልደር
ሰላም ሰጊድ

አድርሽን ¦ ኦ ማርያም ተመላለሺ ሌሊት በሕልሜ ¦ ከሁሉ ሁሉ ጤፍ ታንሳለች #ፍልሰታ ኦ ማርያም እለምንሻለሁ ባርያሽእስቲ አንድ ጊዜ ስሚኝቀርበሽ ካጠገቤ ሆነሽብርቱ ጉዳይ አለኝ ላንቺ ምነ...

"ወፌ ሰንብታ መጣች ለፍልሰታ" እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላም አደረሳችሁ። መልካም መዋዕለ ጾም🤲
05/08/2024

"ወፌ ሰንብታ መጣች ለፍልሰታ" እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላም አደረሳችሁ። መልካም መዋዕለ ጾም🤲

ወፌ ሰንብታ መጣች ለፍልሰታ" እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላም አደረሳችሁ። መልካም መዋዕለ ጾም🤲🤲''ወፌ ሰንብታ መጣች ለፍልሰታ አገርሽ የት ነው ኤፍራታ አሳድሪኝ ማታ ይናፍቀኛል ሌሊት .....

ለንስሃ ሞት አብቃኝበሄሶጵ እርጨኝ እጠበኝእንደበረዶም አንጻኝአመጻዬ በዛ ኃጢአትን ጨመርኩኝልቤም ደነደነ ክፋትን ፈጸምኩኝእንደፈርኦን ልቤ እንዳጸናብኝአድነኝ እንደ ኖኅ አምላክ እራራልኝአድነኝ...
29/07/2024

ለንስሃ ሞት አብቃኝ
በሄሶጵ እርጨኝ እጠበኝ
እንደበረዶም አንጻኝ

አመጻዬ በዛ ኃጢአትን ጨመርኩኝ
ልቤም ደነደነ ክፋትን ፈጸምኩኝ
እንደፈርኦን ልቤ እንዳጸናብኝ
አድነኝ እንደ ኖኅ አምላክ እራራልኝ

አድነኝ
ስለድንግል ብለህ
አድነኝ
ስለጻድቃን ብለህ አድነኝ

ኃጢአቴም በረታ ሰለጠነብኝ
ከቃልህ አስወጣኝ ሕግህን ጣስኩኝ
እንደ ነነዌ ሕዝብ ንስሃ ስጠኝ
ምሕረትህን ልከህ ልቤን ስበርልኝ

አድነኝ እንደቸርነትህ አድነኝ
አድነኝ እንደ ምሕረትህ አድነኝ

ያደፈው ገላዬን አንተው አጥራልኝ
ከሰዶም ገሞራ እንዳይብስብኝ
መንገድና ሕይወት አንተው ነህ ምራኝ
የቅዱስ ጴጥሮስን ንስሃ ስጠኝ

አድነኝ እንደቸርነትህ አድነኝ
አድነኝ ስለ እናትህ ብለህ አድነኝ
ስለጻድቃን ብለህ አድነኝ

ለንስሃ ሞት አብቃኝ Lensiha Mot Abikagn ምክሐ ደናግል ማርያም ሰ/ት/ቤት ቁ.2 ካሴት #ለንስሃ ሞት አብቃኝ mot Abkagn አቤቱ እንደቸርነት ብዛት ማረኝ ይቅር በ...

የጠሩሽ አንቺን ተማጽነው የዳኑብሽ የበላዔ ሰብእ እመቤት የአምላክ እናትድንግል አዛኝቱ ማርያም ቅድስትበተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት
08/07/2024

የጠሩሽ አንቺን ተማጽነው የዳኑብሽ
የበላዔ ሰብእ እመቤት የአምላክ እናት
ድንግል አዛኝቱ ማርያም ቅድስት

በተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት

የጠሩሽ አንቺን ተማጽነው የዳኑብሽ በተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤትየጠሩሽ አንቺን ተማጽነው የዳኑብሽ የበላዔ ሰብእ እመቤት የአምላክ እናትድንግል አዛኝቱ ማርያም ቅድስትበቃልኪዳንሽ ብዙ....

Address

Addis Ababa
Ababa
33873

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሎጎስ ዲጂታል መጽሔት Logos Digital Magazine posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ሎጎስ ዲጂታል መጽሔት Logos Digital Magazine:

Share