06/18/2026
!
👉 ዛሬ በዘመናችን ያሉ አንዳንድ አገልጋዮች ለየት ያለ ምስጢር ያገኙ እየመሰላቸው፣ ከመጽሐፍ ቅዱስ እውነት ውጭ የሆኑ የፍልስፍና መጻሕፍትን የመንፈሳዊ ትምህርት ምንጭ እያደረጉት ይገኛሉ። ለዚህ ትልቅ ማሳያ የሚሆነው፣ ከ161 ዓመታት በፊት በአፄ ቴዎድሮስ ዘመን በአለቃ (በደብተራ) ዘነበ የተጻፈውና እየተባለ የሚጠራው መጽሐፍ ነው።
👆ይህ መጽሐፍ በታሪክና በሥነ-ጽሑፍ ደረጃ የሚኖረው ቦታ እንዳለ ሆኖ፣ በውስጡ የያዛቸው ሃሳቦች ግን ፈጽሞ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ያልሆኑ፣ የእግዚአብሔርን ቃልና አምላካዊ ማንነት የሚያቃልሉ ፍልስፍናዎች ናቸው። ለምሳሌ በመጽሐፉ ላይ እንዲህ ይላል፦
“እግዚአብሔር ፈሪ ነው፤ እኛ በድለነው ልጁን ልኮ ቀስ ብለህ ተዛምደህ ና ብሎ በልጁ ታረቀን... ሰማይን የሚያህል ሰፊ ሀገር ይዞ አባቱ እዚያ አያበላውም፣ አያጠጣውም፣ አያለብሰውም? ልጁስ ሲቀላውጥ ነውር አይፈራምን?” ይላል።
👆ይህ ንግግር መንፈሳዊ ቅኔና ግጥም ሳይሆን ክርስቶስ ስለ እኛ በምድር ላይ መራቡን፣ መጠማቱንና በመስቀል ላይ የከፈለውን ታላቅ የፍቅር መሥዋዕትነት (ማቴዎስ 25) "ነውርና መቀላወጥ" አድርጎ የሚሳለቅ ስጋዊ ፍልስፍና ነው!
📌ትልቁ አደጋ ግን ይህንን የፌዝና የፍልስፍና ጽሑፍ ዛሬ ያሉ "የወንጌል አገልጋዮች" ነቅሰው በማውጣት፣ እንደ እግዚአብሔር ቃልና እንደ ትልቅ ጥልቅ ጥበብ አድርገው ለትውልዱ ማስተማራቸው ነው። ይህ ፍጹም ስህተትና መንፈሳዊ ውድቀት ነው!
?
📌የአዲስ ኪዳን ቤተክርስቲያን ትምህርቷን፣ ስብከቷንና ራዕይዋን መቅዳት ያለባት ከእውነተኛውና ከሕያው የእግዚአብሔር ቃል፣ ከመንፈስ ቅዱስ መለኮታዊ ብርሃን ብቻ ነው።
📌ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ሲያስተምር የብሉይ ኪዳንን መጻሕፍት እየጠቀሰ (ኦሪትንና ነቢያትን) ነበር።
📌ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስና የጥንቷ ቤተክርስቲያን አገልጋዮች ምስክርነታቸውንና ስብከታቸውን የገነቡት የቅዱሳት መጻሕፍትን አውድ መሠረት አድርገው ነበር።
!
የዘመኑ አገልጋዮች ግን "የዘመኑን ወጣት ለመማረክ"፣ መጽሐፍ ቅዱስን ዘግተው የደብተራዎችን ተረትና የዓለምን ከንቱ ፍልስፍናዎች ይዘው መድረክ ላይ ይወጣሉ። ወጣቱ ትውልድ የሚፈልገው ግን የሰውን ጥበብ ሳይሆን፣ ሕይወትን የሚለውጠውንና ከኃጢአት የሚያድነውን ንጹሑን የወንጌል እውነት ነው። በሰብአዊ ፍልስፍና የተገነባ አገልግሎት ትውልዱን ለውድቀትና ለክህደት አሳልፎ ይሰጣል። ለዘመኑ ወጣት ክርስቶስን መግበው እንጂ ፍልስፍናና ተረት አትመግበው!
!
እኛ አገልጋዮች ስብከታችንንና ትምህርታችንን መቅዳት ያለብን ከጳውሎስና ከአዲስ ኪዳን ሐዋርያዊ እውነት ነው። ሐዋርያው ጳውሎስ ያስጠነቀቀን ማስጠንቀቂያ ዛሬም በቤተክርስቲያናችን ጮሆ ሊሰማ ይገባል፦
“እንደ ክርስቶስ ትምህርት ሳይሆን፥ እንደ ሰው ወግና እንደ ዓለም መጀመሪያ ትምህርት በሰው ጥበብና በከንቱ ማታለል ማንም እንዳይማርካችሁ ተጠንቀቁ።" (ቆላስይስ 2፥8)
:-
ወደ ቃሉ እውነት እንመለስ! የዓለም ፈላስፎች ሐሳብ መድረካችንን አይውረሰው። መድረክ የእግዚአብሔር ሕያው ቃል ብቻ በስልጣን የሚነገርበት ቅዱስ ስፍራ ነው። ለየት ለማለትና ሰውን ደስ ለማኘት ስንል ከንጹሑ ወንጌል ፈቀቅ የምንል ከሆነ፣ ተጠያቂነታችን በእግዚአብሔር ፊት የበረታ ይሆናል። ለዘመኑ ወጣት የዓለምን ፍልስፍናና ተረት ሳይሆን ክርስቶስን መግበው! እርሱ የሕይወት እንጀራ ነው!
የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ!
ጸጋዬ ግርማ