06/19/2026
#ሰኔ 12/2018
#የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ
ይሰፍራል ያድናቸዉማል መዝ.33፥7-9
🍁በስመ #አብ _ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን በፆምና በፀሎት ለምናመሰግንበት ለመልአኩ #አፎምያን ከሰይጣን እጅ ላዳነበት #ባህራንን ለተራዳበት ዓመታዊ ክብረ በአል እንኳን አደረሰን
🍁 ይህችም ሴት #እግዚአብሔርን የሚፈራ የአንድ ሰው ሚስት ነበረች ባሏ አስተራኒቆስ በታመመ ጊዜ እያዘነችና እያለቀሰች እንዲህ አለችው ጌታዬ አንድ ነገር ልንገርህ እስኪ ስማኝ ሴት ባሏ የሞተ እንደሆነ ብቸኛ ባይታወር ጦም አዳሪ እንደምትሆን እንጀራዋንም በብዙ ዕንባና ሰቀቀን እንደምትመገብ አንተ ታውቃለህ አንተ ብትሞትና ብትለየኝ ከኀዘኔ የሚያረጋጋኝ ልጅ አባት እናት የለኝም
🍁 አሁንም አንተ ሳለህ የመላእክት አለቃ ሥዕል እንድታሰራልኝ እሻለሁ በመዓልትም በሌሊትም ከሰይጣን ጠላትነት ይጠብቀኝ ዘንድ እኔ በቤቴ ውስጥ አኑሬ እማፀንበታለሁ አስተራኒቆስም አስሎ ሰጣት ባሏም ከሞተ በኋላ ቅድስት አፎምያ ዝክር ታዘክር ነበር ለድሆችም አብዝታ ትረዳ ነበር
🍁 በዚህ ሰይጣን ቀናባት በመነኩሴ ተመስሎ ሊያስታት ሞከረ ስዕል አሳፍራ መለሰችው ከ 3 ወራት በኋላ ሰኔ 12 ቀን ዳግመኛ ቅዱስ ሚካኤል ነኝ ብሎ ሊፈትናት መጣ ሚካኤል ከሆንክ መስቀልህ የት አለ አለችው ከዚህ በኋላ አፉን ከፍቶ አይኑን አጉረጥርጦ አንገቷን አነቃት
🍁 ድረስልኝ ብላ ተጣራች ቅዱስ ሚካኤል ከሰማይ ፈጥኖ ወረደ በበትረ መስቀሉም መታው ጊዜዬ ሳይደርስ አታጥፋኝ ስዕልህ ባለበት ስምህ በተጠራበት ድርሳንህ በሚነበብበት ፈፅሞ አልደርስም ብሎ ማለ ተገዘተ ሸሸም ከዚህ በኋላ ወዳጄ አፎምያ ባንቺ ደስ አለኝ ዋጋሽ በሰማይ ታላቅ ነው ብሎ ባርኳት አርጓል
🍁እንዲሁም በዚህ እለት ባህራንን የተራዳበት የሞቱን ደብዳቤ ወደ ህይወት የቀየረበት የተአምር በዐል ነዉ እንኳን አደረሰን
🍁ከቀድሞ ጀምሮ ቂም የሌለበት ምህረትን የሚለምን እሩሩህ ልመናው ከሲኦል ረግረግ ያድነን ከርጉም ተኩላ አፍም ይሰውረን በከንቱ እንዳንጠፋ ከክፉ የሰይጣን ወጥመድም ያድነን ከሰራዊቱ ሁሉ ጋር በየቀኑ ይታደገን
🍁 ረድኤት በረከታቸዉ ከኛ ጋር ይሁን ጥበቃዉ አይለየን የአባቶቻችን ፀሎት ከኛ ጋር ይሁን"አሜን"